TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
PHOTO : የ2022 የቤል ግሬድ የአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና እየተካሄደ ይገኛል። ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል። ትላንት ለሊት ላይ በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያዊያን🇪🇹 አትሌቶቻችን ከአንድ እስከ ሶስት ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል። በ1500 ሜትር ሴቶች ውድድር ፦ 1ኛ. አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ወርቅ ለሀገራችን ስታስገኝ ፤ 2ኛ. አክሱማዊት እምባዬ ለሀገራችን የብር ሜዳሊያ አገኝታለች፡ 3ኛ. ሂሩት…
ፎቶ ፦ ሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 የደመቀችበት የቤልግሬድ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ቀጥሎ የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን አስመዝግባለች።

ዛሬ በተካሄደ የ3000 ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ እና ለሜቻ ግርማ ተከታትለው በመግባት የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።

የቤልግሬድ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ፍፃሜውን ያገኛል።

ሁሉንም የስፖርታዊ ጉዳዮችን በ @tikvahethsport ይከታተሉ።
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍 የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ያናሷቸው ጥያቄዎች ምንድናቸው ? የካማሺ ዞን ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ዓለሙ በሽር  ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደተናገሩት ታጣቂዎቹ በእስር ላይ ያሉ አባሎቻቸው እንዲፈቱ ጠይቀዋል። የዞኑ አስተዳደሮች ይሄ ጥያቄ በዞኑ የሚመለስ እንዳልሆነ አስረድተው፣ በጉዳዩ ላይ ከበላይ አካላት ጋር ንግግር በማድረግ መልስ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።…
#Update

#BenishangulGumuz , #Kamashi📍

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በጫካ ያሉ ታጣቂዎች ፤ ትጥቃቸውን በሚፈቱበት አካሄድ ላይ ከተወካዮቻቸው ጋር ውይይት ሊደረግ መሆኑ ታውቋል።

የክልሉ መንግስት የተሃድሶ ስልጠና ሃሳቡን ያቀረበው፤ ከጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ታጣቂዎች ጋር ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 10 ቀን 2014 በይፋ ዕርቅ መፈጸሙን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።

በጉሙዝ ባህል መሰረት የተከናወነው የዕርቅ ስነ ስርዓት የተካሄደው በካማሺ ዞን፤ ካማሺ ከተማ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽና በካማሺ ወንዝ ዳርቻ ነው።

በዕርቅ ስነ ስርዓቱ ላይ የምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ የክልሉ ም/ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ አለምነሽ ይባስ እና የጉህዴን ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ ተገኝተው ነበር።

በካማሺ ከተማ የስብሰባ አዳራሽ በተከናወነው ዕርቅ ለአራት ሰዓታት የዘለቀ ነበር።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት እና በጉህዴን አመራሮች መካከል ዕርቅ መውረድ ተከትሎ፤ በጫካ የነበሩ አማጽያን ከእነ ትጥቃቸው ወደ ካማሺ ከተማ ሲገቡ መመልከታቸውን አንድ የከተማውን ነዋሪዎች ዋቢ አድርጎ ድረገፁ አስነብቧል።

የታጣቂዎቹን ወደ ከተማ መግባት የካማሺ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ቦካ አቦሴም አረጋግጠዋል።

ታጣቂዎቹ ለጊዜው የካማሺ ዞን ባዘጋጀላቸው ማረፊያ እንደሚቆዩ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው ገልፀው ፤ በየትኛው የከተማው አካባቢ እንደሚቆዩ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

ያንብቡ ፦ telegra.ph/Ethiopia-Insider-03-20

Credit - Ethiopia Insder

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍 የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ያናሷቸው ጥያቄዎች ምንድናቸው ? የካማሺ ዞን ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ዓለሙ በሽር  ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደተናገሩት ታጣቂዎቹ በእስር ላይ ያሉ አባሎቻቸው እንዲፈቱ ጠይቀዋል። የዞኑ አስተዳደሮች ይሄ ጥያቄ በዞኑ የሚመለስ እንዳልሆነ አስረድተው፣ በጉዳዩ ላይ ከበላይ አካላት ጋር ንግግር በማድረግ መልስ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።…
#Kasmashi📍

የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ከዚህ በፊት እርቅ ለመፈፀም ካስቀመጡት ቅድመ ሁኔታዎች የትኞቹ ተሟሉ ?

👉 የታሰሩ ጉህዴን አመራሮች እንዲፈቱ ጠይቀው፤ በርካታ የታጠቂው ኃይሎች ከእስር ተፈተዋል፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፌደራል መንግስት ጋር በመነጋገር የታሰሩ የጉህዴን አመራሮች የካቲት 17 እንዲፈቱ አድርጓል። ከነዚህ ውስጥ የጉህዴን ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ የሚገኙበት ሲሆን ከ20 ቀናት ገደማ በፊት ነው የተፈቱት። ባለፉት 2 ሳምንታት 400 ገደማ የፓርቲው አባላትም ከእስር መፈታታቸውን ጉህዴን አረጋግጧል።

👉 የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እና ለሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆኑ ጠይቀው፤ አካባቢው ሰላም ከሆነ የክልሉ መንግስት ነዋሪዎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስና በየትኛውም ቦታ እርዳታ ማቅረብ እንደሚችል ለታጣቂዎቹ ገልጿል።

👉 በካማሺ እና መተከል ዞን ያሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንዲሁም የሌሎች ክልል ልዩ ኃይሎች አካባቢዎቹን ለቅቀው እንዲወጡ ጠይቀው፤ ክልሉ የተጠቀሱት የጸጥታ ኃይሎች እንዲወጡ በቅድሚያ ሰላም መምጣት እንዳለበት ከብዙ ውይይት በኋላ ስምምነት ላይ መደረሱን አመልክቷል፤ ጉህዴን ግን በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም አይነት ውይይት አላደረግንም ብሏል፤ ከዕርቁ በኋላ በጉዳዩ ላይ ወይይት እንደሚደረግበት ገልጿል።

🔹 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ታጥቀው በየጫካው ያሉ ታጣቂዎች፤ ትጥቃቸውን ፈትተው የተሃድሶ ስልጠና የሚያገኙበት ሁኔታ ላይ መምከር ከዕርቁ በኋላ የሚኖረው አንዱ ዋነኛ ጉዳይ ነው ብሏል። ጉህዴን በተመሳሳይ ከዕርቁ በኋላ ከክልሉ መንግስት ጋር የሚደረግ ውይይት አለ ያለ ሲሆን ታጣቂዎቹ ትጥቅ መቼ እንደሚፈቱ የሚወሰነው በውይይት ነው ብሏል። እስከዛ ግን ታጥቀው እንደሚቆዩ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አብን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ዶ/ር በለጠ ሞላን በድጋሚ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ። አቶ መልካሙ ሹምዬ ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል። የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጣሂር መሐመድ ፤ ፓርቲው ለ3 ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ሲያካሂድ እንደቆየና የሥራ አስፈፃሚ አባላቱን በአዲስ በማደራጀት ማጠናቀቁን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት፦ 👉 ዶ/ር…
" አብን በጠቅላላ ጉባዔው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንደመረጠ ተደርጎ የሚሰራጭ መረጃ ሐሰት ነው " - አቶ ጣሂር መሐመድ

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ባለፉት ሁለት ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን አካሂዷል።

ዛሬ ደግሞ ሦስተኛ ድርጅታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን እያካሄደ ነው።

የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጣሂር መሐመድ ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሰጡት ቃል ፤ ትናንት በነበረው #የማዕከላዊ_ኮሚቴ_ስብሰባ በተወሰነ መልኩ የአመራር ሽግሽግ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች እልባት መሰጠቱን ገልፀዋል።

" ነገር ግን የፓርቲውን መመሪያ እና ደንብ በውል ካለመረዳት #በጠቅላላ_ጉባዔው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንደተመረጠ የሚናፈሰው ወሬ ትክክል አይደለም " ሲሉ አብራርተዋል።

አቶ ጣሂር ጠቅላላ ጉባዔው የሚመርጠው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ነው ያሉ ሲሆን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የአገልግሎት ዘመን የሚጠናቀቅበት ጊዜ ደግሞ አልደረሰም ብለዋል።

በዚህም በማዕከላዊ ኮሚቴ የተላለፈ ውሳኔ በጠቅላላ ጉባዔ እንደተሻረ ተደርጎ በተለይ በማኅበራዊ የመገናኛ አውታር የሚንሸራሸረው መረጃ መሰረተ ቢስ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ አቶ ጣሂር መሐመድ በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ በጠቅላላ ጉባዔው ምንም አይነት የምርጫ ሂደት እየተደረገ እንዳልሆነ ከሰዓታት በፊት ገልፀዋል።

" ትላንት በተጠናቀቀው የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባችን የአመራር መተካካቶችን አድርገናል። " ያሉት አቶ ጣሂር " አሁን ላይ የጠቅላላ ጉባዔያችን በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 የደመቀችበት የቤልግሬድ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ቀጥሎ የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን አስመዝግባለች። ዛሬ በተካሄደ የ3000 ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ እና ለሜቻ ግርማ ተከታትለው በመግባት የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል። የቤልግሬድ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ፍፃሜውን ያገኛል። ሁሉንም የስፖርታዊ ጉዳዮችን በ @tikvahethsport…
#ETHIOPIA

ኢትዮጵያ ከዓለም #1ኛ ሆና አጠናቀቀች።

ሀገራችን #ኢትዮጵያ በቤልግሬድ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮን ከዓለም አንደኛ ሆና አጠናቀቀች።

#አሜሪካ ሁለተኛ ፤ #ቤልጂየም ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።

በቤልግሬድ 2022 የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያ ፦

🥇4 ወርቅ፣
🥈3 ብር፣
🥉2 ነሃስ፣ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎች ማግኘት ችላለች።

እንኳን ደስ አላችሁ !

@tikvahethiopia
#አዲስ_የልብ_ህክምና

የልብዎ ጤንነት ያለበት ሁኔታ ያውቃሉ?
ሙሉ የልብ ምርመራ በማድረግ የልብዎ ጤንነት ያለበትን ደረጃ ይወቁ። ይሄን ጥቅል በመግዛት ለወዳጅ ዘመዶ ያበርክቱ

ዛሬዉኑ ደዉለዉ ቀጠሮ ያስይዙ
0952343434

Telegram 👉:https://publielectoral.lat/addiscardiachospitalplc

ለልብዎ ከልብ እንሰራለን
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ኢትዮጵያ ከዓለም #1ኛ ሆና አጠናቀቀች። ሀገራችን #ኢትዮጵያ በቤልግሬድ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮን ከዓለም አንደኛ ሆና አጠናቀቀች። #አሜሪካ ሁለተኛ ፤ #ቤልጂየም ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በቤልግሬድ 2022 የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያ ፦ 🥇4 ወርቅ፣ 🥈3 ብር፣ 🥉2 ነሃስ፣ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎች ማግኘት ችላለች። እንኳን ደስ አላችሁ…
#USA

አሜሪካ ለኢትዮጵያውያን አትሌቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች።

አሜሪካ እዚህ አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲዋ በኩል ፤ በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና አስደናቂ ብቃትን ላሳዩ መላው የኢትዮጵያ አትሌቶች " እንኳን ደስ አላችሁ " መልዕክት አስተላልፋለች።

ሀገራችን #ኢትዮጵያ በቤልግሬድ የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮን ከዓለም #አንደኛ ሆና ማጠናቀቋ ይታወቃል።

አሜሪካ ከኢትዮጵያ በመቀጠል ከዓለም ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ነው የጨረሰችው።

@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ምንድነው ያሉት ?

#ብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት አንድ ተቀማጭነቱን ውጭ ሀገር ላደረገ የቴሌቪዥን ጣቢያ ከሰሞኑን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈፀመውን የሰው ልጆችን በእሳት የማቃጠል ድርጊት " አረመኔያዊ " ሲሉ በማውገዝ የተሰማቸውን ከባድ ሀዘን ገልፀዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዚህ ንግግራቸው ድርጊቱ " አለምን ያሳዘነ ፤ የአረመኔነት ድርጊት ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

ብፁዕነታቸው " ባለፈው 2013 ዓ/ም ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ያላየነው ያልሰማነው " የለም ያሉ ሲሆን " በትግራይ ህዝብ ላይ የደረሰው መከራ እጅግ የሚያሳዝን እጅግ የሚያስለቅስ ነው፤ መፈጠረን ሁሉ የሚያስጠላ ድርጊት ተፈፅሟል " ብለዋል።

ነገር ግን የአሁኑ ድርጊት ከሁሉ የባሰ ነው ብለውታል።

ከሰሞኑን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተፈፀመው ድርጊት በተጨማሪ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ተፈፅሟል ያሏቸውን የጭካኔ ተግባራት ዘርዝረዋል።

" በትግራይ ክሊኒኮች፣ ሆስፒታሎች ፣ ት/ቤቶች ፣ መድሃኒት ቤቶች ፋብሪካዎች በጠቅላላ ወድመዋል፣ የቀረ ነገር የለም አሁን ደግሞ እንደገና ህፃናት በእናቶች እቅፍ ሆነው፣ ምግብ አጥተው እያለቀሱ እንደቅጠል ደርቀው በምግብ እጦት በእናቶቻቸው እቅፍ ሲሞቱ ፤ እናቶቻቸው እያለቀሱ ጡት እንዳያጠቧቸው እነሱም እራሳቸው በረሃብ ስለደረቁ ወተት የለም እንደዚህ ያለውን ሁኔታ እያየን ነው " ብለዋል።

ብፁዕነታቸው እከዛሬ የሆነው ሆኗል ፣ የጠፋው ጠፍቷል፣ የሞተው ሞቷል፣ ያለቀው አልቋል፤ አሁን ግን ቢበቃ ሲሉ ተደምጠዋል።

" ሀዘናቸው እጅግ ከባድ " መሆኑን የገለፁት ብፁዕነታቸው " ይሄ የሁሉም የኢትዮጵያዊያን በተለይም የትግራይ ህዝብ ሀዘን ነው እና መከራው ግን በሁሉም ደርሷል ቀስ እያለ እየተስፋፋ በመላ ኢትዮጵያ ደርሷልና በቃው ከእንግዲህ ወዲህ ምናለ ለተረፈው ህዝብ ይቅርታ ቢደረግለት ወይም ደግሞ ቢያሳዝነን ለምን እንዲህ አይነት ችግር ይፈጠራል ፤ ይብቃ " ሲሉ ተናግረዋል።

ብፁዕነታቸው ፤ በትግራይ ክልል ስላለው ሁኔታ ለመናገር እስካሁን እድል እንዳላገኙ በመግለፅ ፤ ከዚህ በፊት ሾልኮ የወጣውን ቪድዮ ላይ ሁኔታውን ለመግለፅ ከሞከሩበት ውጭ ሌላ እድል አግኝተው እንደማያውቁ አስረድተዋል።

ከዚህ በፊት ሾልኮ በወጣ ቪድዮ ላይ ብፁዕ አቡነ ማትያስ በትግራይ ያለውን ሁኔታ ከተናገሩ በኃላ በወቅቱ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም።

ቅዱስ ፓትርያርኩ መነጋገሪያ ሆኖ በነበረው ቪድዮ ትግራይ ክልል ውስጥ ይሰራል ያሉት አረመኒያዊ ስራ እንዲቆም ያቀረቡት ጥይቄ አለመሳካቱን ፤ ፍቃድም እንዳልተሰጠ ገልፀው ሚናገሩት ሁሉ በተደጋጋሚ እንደሚመለስና ፍቃድ እንዳላገኙ ተናግረው ነበር።

ከዚህ በኃላም የቤክርስትያኒቱ ሲኖዶስ ዋና ፀሀፊው ብጹዕ አቡነ ዮሴፍ ሰጥተው በነበረው መግለጫ ፤ የትኛውም መልዕክት ከመተላለፉ በፊት በሲኖዶስ በሚደረግ ስብሰባ ውሳኔ ሊሰጠው እንደሚገባና አቡነ ማትያስ ያስተላለፉት የግል አቋም እንጂ የሲኖዶሱ ውሳኔ እንዳልሆነ አሳውቀው ነበር።

የቅዱስ ፓትርያርኩ ፤ የሰሞኑ ንግግር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሚወክል ስለመሆን ፤ አለመሆኑ ቅዱስ ፓትርያርኩ በግልፅ አልተናገሩም ፤ አልያም ከዚህ ቀደም እንደነበረው በሲኖዶስ በኩል የተገለፀ ነገር እስካሁን የለም።

ቅዱስ ፓትርያርኩ የተናገሩትን ሙሉውን ያንብቡ 👇

https://telegra.ph/Holiness-Abune-Mathias-03-20
TIKVAH-ETHIOPIA
" .. የዩኒቨርስቲ መግቢያ ጊዜው ይራዘምልን " - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ጊዜው እንዲራዘም ጠየቀ። ቢሮው የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ እጅግ በጣም ሰፊ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎቻችን ውጤታቸው እንደገና እንዲፈተሸላቸው እያመለከቱ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪ…
" ከ13, 862 ተፈታኞች 3,006 ተማሪዎች ብቻ ናቸው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የመግቢያ ዉጤት ያስመዘገቡት " - የአዊ ብሔ/አሰ ትምህርት መምሪያ

በአማራ ክልል፤ የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ከ13 ሺ 862 ተፈታኞች 3 ሺህ 6 ተማሪዎች ብቻ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የመግቢያ ዉጤት ማስመዝገባቸዉን አሰታወቀ።

የመምሪያዉ ኃላፊ አቶ አለሙ ክህነት ፤ በ2013ዓ.ም በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ29 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ 13 ሺህ 862 ተማሪዎች ሀገርአቀፋ ፈተና መፈተናቸውን ገልጸዋል።

ከነዚህም ዉስጥ በብሄረሰቡ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ 3 ሺህ 6 ተማሪዎች ብቻ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የመግቢያ ዉጤት ማምጣታቸውን ነዉ ሀላፊዉ የተናገሩት።

አጠቃላይ የማለፋ ምጣኔም 21.7% ብቻ መሆኑ ተገልጿል።

ከተፈተኑት የተፈጥሮ ሳይንስ 5 ሺህ 745 ተማሪዋች መካከል 1 ሺህ 943 የመግቢያ ዉጤት አምጥተዋል። በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ከተፈተኑት 8 ሺህ 117 ተማሪዎች ዉስጥ 1 ሺህ 63 ወደ የመግቢያ ዉጤት ያመጡ መሆናቸዉን ተገልጿል።

የእርማት ጥራት ችግር ማሳያ 140 ያመጣ ተማሪ እንደገና ሲፈተሸ 601 ፣ የሲቪክስ ት/ት ፈተና ችግር በሌለበት አካባቢ መሰረዝ እና የፈተና አስተዳደር ስርዓቱ በአግባቡ የተመሩ ባለመሆናቸዉ ለተመዘገበዉ ዝቅተኛ ዉጤት ተጠቃሽ ሞክንያቶች መሆኑን ትምህርት መምሪያው ገልጿል።

የፈተና ስርዓቱ ስለመታወኩ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ቼክ ተደርጎ እንደገና መፈተሽ እንዳለበት ከሚመለከተው ጋር እየሰራ መሆኑን መምሪያው አሳውቋል።

እስከአሁንም መምሪያዉ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ጋር የፈተና ሂደቱ እንደገና እንዲታይ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች እና የተማሪ ቤተሰቦች በትግስት እንዲጠብቁ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#NewsAlert

ቻይና ውስጥ 133 መንገደኞችን አሳፍሮ ሲበር የነበረ ቦይንግ 737 አውሮፕላን መከስከሱን የቻይና መገናኛ ብዙኃንን ዋቢ አድርጎ ቢቢሲ ዘግቧል።

የቻይና ኢስተርን አየር መንገድ ንበረት የሆነው ይህ ቦይን 737 ወድቆ መከስከሱ የተነገረው ጓንግዡ ግዛት ውስጥ ነው።

አስካሁን በአደጋው ጉዳት ስለደረሰባቸው ሰዎች የታወቀ ነገር የለም።

የአገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት አውሮፕላኑ ወድቆ የተከሰከሰው በተራራማ አካባቢ ሲሆን በስፍራው ባለ ጫካ ላይ እሳት ተነስቷል።

ይህ ቦይንግ 737 አውሮፕላን በበረራ ቁጥር ኤምዩ5735 በቻይና የሰዓት አቆጣጠር ከእኩለ ቀን በኋላ ከኩንሚንግ ተነስቶ ወደ ጓንግዡ እያመራ ነበር ተብሏል።

የነፍስ አድን ሠራተኞች ወደ የአደጋው ስፍራ መሰማራታቸውን የቻይና ብሄራዊ ቴሌቪዝን መዘገቡን ቢቢሲ ፅፏል።

@tikvahethiopia