TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ALERT🚨

በሀገራችን ኢትዮጵያ በቀን 2,323 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 10,016 የላብራቶሪ ምርመራ 2,323 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት ውስጥ የ5 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

በሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 2,992 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 10,828 የላብራቶሪ ምርመራ 2,992 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ3 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ወረርሽኙን ለመከላከል የምታደርጉትን ጥንቃቄ እርምጃ ከመቼውም ጊዜ በላይ ታጠናክሩ ዘንድ አደራ እንላለን።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

በሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 3,793 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 13,147 የላብራቶሪ ምርመራ 3,793 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ5 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

በሌላ በኩል ፤ ኦሚክሮን የተሰኘው የኮቪድ-19 አዲሱ ዝርያ ኢትዮጵያ ውስጥ መከሰት አለመከሰቱን ለማረጋገጥ ናሙና በመውሰድ ምርምር እየተካሄደ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ዛሬ አስታውቀዋል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

በሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 4,573 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 12,348 የላብራቶሪ ምርመራ 4,573 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ3 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

በሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 5,013 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 14,027 የላብራቶሪ ምርመራ 5,013 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ6 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

193 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

#ከፍተኛ_ጥንቃቄ

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 6,262 የላብራቶሪ ምርመራ 1,864 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ6 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

210 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

በሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 5,185 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 13,280 የላብራቶሪ ምርመራ 5,185 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ7 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

የፅኑ ታማሚዎች ቁጥር በእጅጉ የጨመረ ሲሆን አሁን ላይ 232 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 14,035 የላብራቶሪ ምርመራ 4,998 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ10 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

260 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 13,409 የላብራቶሪ ምርመራ 4,899 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ11 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 10,861
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,269
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 24
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 1,416
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 443

ዛሬ እና ትላንት በድምሩ የ48 ሰዎች ህይወት አልፏል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 10,073
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,131
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 19
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 835
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 433

ዛሬ እና ትላንት በድምሩ የ43 የሰዎች ህይወት አልፏል።

@tikvahethiopia
#Alert

የጤና ሚኒስቴር የትዊተር አካውንት ተጠለፈ።

ከ204 ሺ በላይ ተከታዮች ያሉት የሚኒስቴሩ የትዊተር አካውንት ተጠልፏል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጤና ሚኒስቴር ይፋዊ የትዊተር አካውንቱ #FMoHealth ዛሬ መጋቢት 24 መጠለፉን (ሃክ መደረጉን) አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ በትዊተር ገጹ ላይ የሚለቀቁ ማንኛውም መረጃዎች እንደማይወክሉት ገልጿል።

@tikvahethiopia
#Alert🚨

በራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ላይ የተነሳውን እሳት መቆጣጠር አልተቻለም።

በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 016 ቀበሌ በተለምዶ ራስ ጠቆሮ እየተባለ በሚጠራ ጥብቅ ደን ላይ ሰኔ 6/2014 ሌሊት ጀምሮ የተከሰተው የእሳት አደጋን እስካሁን ድረስ መቆጣጠር አልተቻለም።

በጥብቅ ደኑ ውስጥ ወይራ፣ ጥድ፣ ኮሶ፣ ዝግባና ሌሎች የደን ሐብቶች እንዲሁም የተለያዩ እንሰሳትና አዕዋፋት እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

ከመልክዓ ምድራዊ አቀማመጡ አመቺ አለመሆን እና በደኑ ውስጥ ተቀጣጣይ ሳር ከመብዛቱ ጋር ተያይዞም የእሳት አደጋውን ለማጥፋት የሚደረገውን ጥረት ሥራውን ፈታኝ እንዳደረገው ተገልጿል።

የአደጋው መንስኤ በተመለከተ እሳቱ ከግለሰብ ማሳ ተነስቶ ወደ ደኑ እንደተዛመተ የአምባሰል ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

" ሰባ ሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም "

ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ በከባድ ድርቅ መመታቱ ተገልጿል።

በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ስር ያለው ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ 13 ቀበሌዎች አሉት።

ወረዳው የ2015/2016 የምርት ዘመን #ድርቅ ክፉኛ መትቶታል።

ወረዳው በከፊል አርብቶ አድር የሚታወቅ ሲሆን ከማሳው በሚያገኛት ጥቂት ኩንታል እህል በይበልጥ ለገለባው ዋጋ ሰጥቶ በእንሰሳቱ ኑሮውን የሚገፈ አርሶና አርብቶ አደር አካባቢ ነው።

በወረዳው ከፍተኛ የእንስሳት ሀብትም ይገኛል።

ጠቅላላ ካለው የእንስሳት ሀብት የዳልጋ ከብት 104,430፣ የጋማ ከብት 22,121 በግ እና ፍየል 465,428 ይገኙበታል።

ከዚህ ውስጥ ለድርቅ የተጋለጡ የዳልጋ ከብት 92,430፣ የጋማ ከብት 16,121፣ በግ እና ፍየል 396,760 ናቸው።

ወደአጎራባች ዞን የተሰደዱ የዳልጋ ከብት 20,328 ፣ በግ እና ፍየል 116,900 ሲሆኑ እስካሁን በድርቅ ምክንያት የሞተ የዳልጋ ከብት 1320 ፣ የጋማ ከብት 71 በግ እና ፍየል 2457 ናቸው።

በወረዳው ከ52 ሺህ በላይ ህዝብ የሚኖርበት ሲሆን 46ሺ የሚሆነው አፋጣኝ እርዳታ ካለገኘ አደጋ ውስጥ እንደሆነ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ብሩ ተናግረዋል።

አቶ ሲሳይ፤ " ምንም እንኳን ድርቅ ቢሆንም ከዚህ በፊት ለእንስሳት የሚሆን ሳር አይጠፋም ነበር። ዛሬ ግን የተቃጠለ መሬት ብቻ ነው የሚታየው፤ ለጥርስ ስጋ ማውጫ የሚሆን የሳር ስንጥር እንኳን አይታይም፤ የወረዳው ነዋሪዎች እንደነገሩን እንደ ወረዳችን እንዲህ አይነት ድርቅ አይተን አናውቅም፤ ሰባሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም " በማለት የድርቁን አስከፊነት ገልጸዋል።

በወረዳው የአርሶ አደሩ ማሳ ርቃኑን ቀርቷል፣ እንስሳት ቆዳቸው ከስጋቸው መጣበቅ ብቻ ሳይሆን ነፍሳቸው በጣዕረሞት ላይ ናት፣  ህጻናት፣ እናቶችና አረጋውያን በርሀብ ተገርፈው ነፍሳቸው ከጉንጫቸው ተጣብቃ ይዛቸው ልትጠፋ አፋፍ ላይ ነች። ተሎ መድረስ ካልተቻለ አሳዛኝ ክስተት በሰሀላ ሰዬምት ወረዳ ሊከሰት ይቻላል።

የአስተዳደሩ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ጉዞ አዘጋጅቶ የነበረ ሲሆን የብሄረሰቡ ከፍተኛ አመራሮችና አንዳንድ ግብረሰናይ ድርጅቶች በወረዳው ተገኝተው ቀበሌዎቹን ጎብኝተው ከነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገው ነበር።

የቀበሌው ማህበረሰብ በውይይቱ ላይ " ከእግዚአብሄር በታች መንግስት ነበር ለሰው ልጅ ዋስትና፣ ዛሬ ግን መንግስትም ፊቱን አዞረብን " ብለዋል።

" በዚህ ሳምንት ውስጥ የሚበላ ካልቀረበ ልጆቻችን አናገኛቸውም ፤ አሁንም ቢሆን አንዲት እንጀራ ለ10 ሰው ነው የምንሻማው፤ ከዛ ውጭ ግን ጨው በውሀ በጥብጠን ነው የምንጠጣው " ብለዋል።

እስካሁንም በወረዳው በርሀብ ምክኒያት የ2  ሰዎች ሂይወት አልፏል ሲሉ አሳውቀዋል።

እንስሳትን በተመለከተ " በወረዳችን ትንሽ እህል ካገኘን እንሰሳ ስለምናረባ ከብት እና ፍየሎቻችንን ሸጠን እህል ስለምንሸምት ብዙም አያሳስበንም ነበር፤ ዘንድሮ ግን ለከብቶችም ሆነ ለፍየሎችና በጎች የሚሆን የሚጋጥ ሳር ስለሌለ ተስፋ አስቆርጦናል " ብለዋል።

የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ምህረት መላኩ፤ የተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ቃል ከመግባት የዘለለ በመንግስት በኩልም ምንም የቀረበ ነገር የለም።

ለክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ሪፖርት ከማድረግ ባለፈ የችግሩን አሳሳቢነት ብንገልጽም እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም ብለዋል።

መረጃው ከዋግኽምራ ኮሚኒኬሽን ነው የደረሰን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ALERT🚨 " ሰባ ሰባት እንኳን አንዲህ አልነበረም " ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ በከባድ ድርቅ መመታቱ ተገልጿል። በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ስር ያለው ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ 13 ቀበሌዎች አሉት። ወረዳው የ2015/2016 የምርት ዘመን #ድርቅ ክፉኛ መትቶታል። ወረዳው በከፊል አርብቶ አድር የሚታወቅ ሲሆን ከማሳው በሚያገኛት ጥቂት ኩንታል እህል በይበልጥ ለገለባው ዋጋ ሰጥቶ በእንሰሳቱ ኑሮውን…
#ALERT🚨

አንድ አንጀራ ለ10 ተሻምተው የሚበሉ ወገኖቻችን እንዳሉ እናውቅ ይሆን ?

በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ስር ያለው ሰሀላ ሰዬምት ወረዳ በከፍተኛ ድርቅ ተመቷል።

ነዋሪው ችግር ላይ ወድቋል።

ሰው በረሃብ #ሞቷል ፣ እንስሳት ሞተዋል ፣ ተሰደዋል።

ወገኖቻችን በቂ ምግብ አጥተው 1 እንጀራ ለአስር እየተሻሙ እየበሉ ነው። ካዛ ውጭ ጨው በውሃ በጥብጠው ነው የሚጠጡት።

" በዚህ ሳምንት የሚበላ ካልቀረበ ልጆቻችንን አናገኛቸውም " ብለዋል።

የግብረሰናይ ድርጅቶች ቃል መግባት እንጂ ጠብ የሚል ነገር አላደረጉም። መንግሥትም ለገዛ ዜጎቹ እየደረሰ አይደለም።

ከፈጣሪ በታች ለህዝቡ ዋስትና ነው የሚባለው መንግሥት ፊቱን እንዳዞረባቸው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ሁኔታው ከሰባ ሰባቱም የከፋ ነው።

via @BirlikEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ይህ በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ የተከሰተ የመሬት መንሸራተት ነው። ትላንት ቀን 10:30 በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 1 ሰው ሲሞት ፣ 1 ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። 8 የአከባቢው ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። በተከሰተው ናዳ አደጋ ህይወቷ ያለፈው የ11 ዓመት ሴት ልጅ ናት። አብራት የነበረችው ወላጅ እናቷ ደግሞ ከአደጋው…
#Alert🚨

" እስካሁን የ11 ሰዎች አክስሬን ተገኝቷል " - የካዎ ኮይሻ ወረዳ

በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ ዛሬ ረፋድ 5 ሠዓት አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

በተከሰተው አደጋ እስካሁን በተደረገ ፍለጋ የ11 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል።

የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳደር አሳውቋል።

ከቀናት በፊት በዚሁ አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ 1 ሰው ህይወቱ ማለፉ እና 1 ሰው ከባድ ጉዳት እንደረሰበት ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከወረዳው ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
#Alert🚨

የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል።

ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ውስጥ የተያዘ ሰው #አለመኖሩን የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ አመልክቷል።

በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት እና ሞያሌን ጨምሮ በሌሎች የመግቢያ ቦታ ላይ የቁጥጥርና ማጣራት ስራ እየተሰራ ነው።

በሽታው እስካሁን በ13 የአፍሪካ ሀገራት መከሰቱን እንዲሁም፣ 2,863 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው እና 517 ለህልፈት መዳረጋቸዉ መረጋገጡን የአፍሪካ ሲዲሲ መረጃ ያሳያል።

@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ። የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል። ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ…
#Alert🚨

ከተ.መ.ድ የጤና ኤጀንሲ እንደተገኘው መረጃ በቅርቡ ኤምፖክስ (Mpox) ለመጀመሪያ ጊዜ በ4 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ፦
- በጎረቤታችን ኬንያ ፣
- በቡሩንዲ ፣
- በሩዋንዳ
- በኡጋንዳ ተገኝቷል። ሀገራቱም ሪፖርት አድርገዋል። በነዚህ ሀገራት ውስጥ የታየው በሽታ በኮንጎ ካለው ጋር የተገናኘ ነው።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወይም Mpox በሽታ የሚከሰተው በቫይረስ አማካኝነት ነው።

ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል። በወሲባዊ ግንኙነት ፣ በቆዳ ንክኪ ፣ በቅርብ ርቀት ሆኖ ማውራት/ መተንፈስ ፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ባለ የቅርብ ግንኙነት ይተላለፋል።

አሁን ላይ #ዋነኛዎቹ ናቸው የሚባሉት ሁለቱ የቫይረሱ ዝርያዎች Clade 1 - በማእከላዊ አፍሪካ ውስጥ ያለ ፤  Clade 1b - እጅግ በጣም አደገኛ የሆነው አዲስ የቫይረሱ ዝርያ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Omo የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው። ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ከተለመደውና ከታሰበው ውጭ መሆኑን ተከትሎ ግን ለዞኑ መንግስትም ሆነ ለግብረሰናይ ድርጅቶች ሁኔታው ከባድ ሆኖባቸዋል። የወንዙ ሙላት ከባድ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ አርብቶ አደሩን በአራት ጊዜያዊ…
#ALERT🚨

⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች

🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር

የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል ስንል ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል።

ይሁንና አሁን ላይ የኦሞ ወንዝ ከአቅም በላይ በመሙላቱና የአካባቢዉ መሬት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መተኛቱን ተከትሎ የወረዳዉ ዋና ከተማ የሆነችዉን ኦሞራቴን ደሴት ሲያደርጋት ህዝቡም መዉጫ በማጣት ጭንቀት ውስጦ መግባቱን ሰምተናል።

የድረሱልን ጥሪያቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረሱት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ለአመታት በወንዙ ሙላት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና አሁን ግን ከርቀት ወደምትገኘው ኦሞራቴ ከተማ በእጅጉ መጠጋቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ ከመዋጣቸው በፊት የሚመለከተዉ አካል እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።
 
በአካባቢው የነበሩት አርብቶ አደሮች በበኩላቸው ሙሉ በሙሉ የግጦሽ መሬቶች በወንዙ ተቆርሶ መወሰዱንና ከብቶቻቸው ማለቃቸውን ገልጸዉ አሁን ላይ የተጠለሉባቸው ጊዜያዊ መጠለያዎች በውሀው እየተጥለቀለቁ በመሆኑ ህይወታቸዉ አደጋ ላይ መውደቁን አስተድተዋል።

ስለሁኔታዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ " የዉሀዉ አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው " ብለዋል።

ማህበረሰቡ አፈር በማዳበሪያ እየቋጠረ ግድብ መስራቱ ውሀውን ስላላስቆመው የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ብለዋል።

" አሁን ላይ የኦሞራቴ ከተማ ከጊዜያዊ መጠለያዎችም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ለመገናኘትም ሆነ ለመሸሽ ቱርሚን የሚያገናኘዉ ድልድይ በመሰበሩና ወደኬኒያ የሚወስደዉ ዋና መንገድ በውሀው ክራክ በማድረጉ ደሴት ሆናል " ሲሉ ገልጸዋል።

በመሆኑም " የኦሞራቴ ህዝብ የከፋ ችግር ላይ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ " ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM