TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የሰላም ዋጋው ስንት ነው?
#PEACE

ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት ነው፡፡ ለዚህም ነው ሰዎች ሲገናኙ ቅድሚያ ስለ ሰላማቸው ሁኔታ የሚጠያየቁት፡፡ ጠዋት ከእንቅላፋቸው ተነስተው “በሳላም አውለኝ”፤ ማታ ሲተኙም “በሰላም ያዋልከኝ በሰላም አሳድረኝ” ብለው ምስጋናቸውን የሚገልጹትም የሰላምን ትልቅ ዋጋ በመረዳት ነው፡፡ እናም ሁሉም ሰው ሊባል በሚችል መልኩ ሰላም በህይወቱ ላይ ትልቅ ውድ ዋጋ ያለው ነገር መሆኑን ይገነዘባል፤ ለሰላሙም ዘብ ይቆማል፡፡

ሆኖም ከብዙዎች #በተቃራኒ ሰላም ለማደፍረስ የሚተጉ ኃይሎችም አሉ፡፡ በእነዚህ አይነት ሰዎች የተነሳ በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚገኙ ህዝቦች ሰላምና መረጋጋት እንዲርቃቸውና በአንጻሩ ጦርነት፣ የእርስ በርስ ግጭት፣ ሽብርተኝነትና ወንጀል ተንሰራፍተው የሰዎችን ዕለታዊ ኑሮ እንዲታወክ ምክንያት ይሆናሉ፡፡

በሰላም እጦት ምክንያት የሚሊዮኖች ህይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት ተከስቷል፤ እየተከሰተም ነው፡፡ የ2017 Global Peace Index እንደሚያሳየው በአለም አቀፍ ደረጃ በሰላም እጦት ምክንያት በየዓመቱ 13 ነጥብ 6 ትሪሊየን ዶላር ኪሳራ እየተስተናገደ ነው፡፡ በግለሰብ ደረጃ በእያንዳንዱ ቀን አንድ ሰው ማግኘት ከሚገባው ውስጥ 5 ዶላር ያጣል ማለት ነው፡፡

ሶሪያ፣ የመን፣ ኢራቅና ደቡብ ሱዳን በሰላም #እጦት ምክንያት እየተናጡ ከሚገኙ ሀገራት ውስጥ ቀዳሚውን ስፍራ ይዘው ይገኛሉ፡፡ በተለይም ሶሪያና የመን በእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት ወደ ፍርስራሽነት እየተቀየሩ ነው፡፡ የዓለም የስልጣኔ ቁንጮ የነበረችው ሀገረ ኢራቅም በአሸባሪ ቡድኖች ምክንያት ታላላቅ የስልጣኔ አሻራዎቿን ለመገበር ከመገደዷም በላይ ህዝቡ ለሞትና ለስደት ተዳርጓ፤ በከፍተኛ ስነ ልቦና ጫና ውስጥ ወድቋል፡፡

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-08-20-8
የሰላም ዋጋ ስንት ነው?

#የባህርዳር_ወጣቶች ያዘጋጁት የምዕራፍ ሁለት የጎዳና ላይ የሰላም ጉባኤ ተካሂዷል። #PEACE #ሰላም #ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሶሪያ #PEACE😢ከአመታት በፊት ይህቺ ምድር ማንም እንዲህ ወደ ፍርስራሽነት ትቀየራለች ብሎ አልገመተም፤ግን ሆነ! ሶሪያ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቿን አጣች፤ በሚሊዮኖች ተወልደው ካደጉበት ሀገር ተሰደዱ!! ጦርነቱ ዛሬም አላባራም ዛሬም ሰው ይሞታል!! #ያሳዝናል! #ልብ_ይሰብራል! ሶሪያውያን ይህ ከመሆኑ በፊት ከስሜታዊነት ወጥተው፤ በሰከነ መንገድ ተረጋግተው ተነጋግረው ቢሆን ኖሮ ይህ ሁሉ ሰቆቃ ባልመጣ ነበር። ማስተዋልን የመሰለ #ጥበብ ከየት ይመጣ ይሆን?

መገንባት እንደማፍረስ ቀላል አይደለም!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#PEACE | የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደቡብ ኢትዮጵያ ወጣቶች ማህበር የተመሰረተበትን 11ኛ ዓመት በዓልና የ2012 ዓመታዊ ጉባኤ አካሂዷል። በጉኤው ላይ ወጣቶች የአገሪቷ ሰላም እንዳይደፈርስ በአንድነት፣ በመተባበርና በመቻቻል ጠንክረው መጓዝ እንደሚገባቸው ተገልጿል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት #በሰላማዊ_መንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ። በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ። ዶ/ር…
#Peace

የተደራዳሪ ቡድኑ !

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #በሰላም_ድርድር እንዲፈታ ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት በፌዴራል መንግሥት በኩል የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙ ተረጋግጧል።

የቡድኑ አባላት ፦

1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን ➡️ ሰብሳቢ
2ኛ. ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ ➡️ አባል
3ኛ. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ➡️ አባል
4ኛ. አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር ➡️ አባል
5ኛ. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ➡️ አባል
6ኛ. ሌ/ል ጀኔራል ብርሀኑ በቀለ ➡️ አባል
7ኛ. ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር ➡️ አባል መሆናቸውን የኢፕድ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የጀግኖቹ_ወላጆች ❤️ የኢትዮጵያን ስም በዓለም ላይ ከፍ እያደረጉ ካሉት አትሌቶቻችን መካከል ቤተሰቦቻቸው የግንኙነት መስመር ከዓመት በላይ በተቋረጠበት ትግራይ ክልል ውስጥ ይኖራሉ። እነሱን ጨምሮ ሁሉም የትግራይ ህዝብ የኢንተርኔት ግንኙነት ባለመኖሩ ስሜቱን እንደኛ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለማጋራት አልታደለም። ከከተሞች ወጣ ባሉ የትግራይ ክልል ክፍል የሚኖሩ የአትሌቶች ቤተሰቦችም የልጆቻቸውን ድል…
#ሰላም #Peace

የጎተይቶም የሰላም ምኞት !

ጎተይቶም ገብረስላሰ የሴቶች ማራቶን #የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ፦

" ... ምኞቴ ሰላም ነው። ሰላም በምንም ነገር አይገኝም።

እኛ በጣም ነው ሰላምን የምንፈልገው። ዓመት ከስምንት ወር ሆኖብናል የወላጅ ናፍቆት ቀላል አይደለም።

እናቴ እንዳለችው እኔ ናፍቆት አልችልም። ማይቻል ነገር ግን የለም። ችለን እዚህ ደረስን እንጂ እኔ ናፍቆት አልችም ነበር።

አንድ ቀን ሳልደውልላት አልተኛም። አባት፣ እናቴን በጣም እወዳለሁ፤ አባቴን በጣም ነው የምወደው በዛ የተነሳ ስልክ ሳልደውልላቸው አልተኛም ነበር።

ማይቻል ነገር የለም ብላዋለች እናቴ ናፍቆትን አትችልም እሷ ይሄን ሁሉ ተቋቁማ እዚህ መድረሷ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ነው ያለችው ትክልል ነው ማይቻል ነገር የለም ችዬዋለሁ።

እግዚአብሔር ሰላም አምጥቶ እንዲያገናኘን ነው ምኞቴ። "

ጎተይቶም ገብረስላሰ የኢትዮጵያን ህዝብ ስሜት በተመለከተ፦

" .. እያየሁ ነበር የነበረውን ድባብ፣ የነበረውን ደስታ እንደዚህ ስንሆን ነው የሚያምርብን ፤ ሁሉን ነገር ትተን #ለሰላም ስንቆም ነው።

ለካ ይሄንን ያህል በህዝቡ ልብ ውስጥ አለን ብዬ ነበር ለራሴ ፤ ደጋግሜ እያየሁ ነበር።

እርግጥ ውድድሩ አጓጊና እልህ አስጨራሽ ነበር በጣም ፤ በዛ የተነሳ ሰው ስሜታዊ ሆኖ ነበር በጣም ነው የማመሰግነው። በፀሎትም፣ በሞራልም የደገፉኝ ሰዎች በጣም ነው የማመሰግነው።

ሁለተኛ ትልቅ ደስታ ነው የፈጠረብኝ። ይሄን ያህል ህዝብ ነበር ለካ የሚከታተለው ብዬ ለራሴ ውስጤን እንድጠይቅ ነው ያደረገኝ "

(አትሌት ጎተይቶም ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጠችው ቃለምልልስ)

@tikvahethiopia
#Peace

የአፍሪካ ኅብረት #የሰላም_ንግግሩን የሚመሩ አካላትን፤ ቀንና ስፍራን አሳውቆ የሰላም ውይይቱ እንዲጀመር ኦፊሴላዊ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።

ይኸው በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ የቀረበው ጥሪ እንደሚያሳየው፦

- የውይይት ቦታ 👉 ደቡብ አፍሪካ

- የውይይቱ ቀን 👉 ከፊታችን ጥቅምት 8/2022 ጀምሮ

- የሰላም ውይይቱ የሚመራው 👉 በቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንትና በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ

- የሰላም ሂደቱ ፓናሊስት ሆነው የሚያገለግሉ 👉 የቀድሞ የኬንያ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፉምዚሌ ምላምቦ ንጉካ ናቸው።

የአፍሪካ ኅብረት ግብዣውን ለኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እንዲሁም ለህወሓት ነው ያቀረበው።

የአፍሪካ ህብረትን ግብዣ የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት #መቀበሉን በይፋ አሳውቋል። ነገር ግን የውይይቱን መሪዎች፣ ቀንና ቦታ በዝርዝር አልገለፀም።

መንግስት " የአፍሪካ ኅብረት ግብዣ መንግሥት ከዚህ በፊት ያቀረባቸውን አቋሞች የጠበቀ ሆኖ ተገኝቷል " ብሏል።

" ንግግሩ በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ብቻ እንዲሆንና ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲደረግ መንግሥት አቋሙን ሲገልጥ መቆይቷል " ሲልም አስታውሷል።

" ግጭቱን ለመፍታት ሁሉንም ዓይነት የመፍትሔ ርምጃዎች ለመውሰድ ስንቀሳቀስ ቆያቻለው " ያለው የፌዴራል መንግስት " ይህንኑ አጠናክሬ እቀጥላለሁ " ብሏል። 

እስካሁን ድረስ በህወሓት በኩል ለዚሁ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ንግግር ግብዣ ይፋዊ ምላሽ አልተሰጠም።

NB. ከላይ የተያያዘው በሙሳ ፋኪ የተፈረመው ደብዳቤ ለፌዴራል መንግስት እና ለህወሓት የተላከ መሆኑን ሮይተርስ ከዲፕሎማቲክ ምንጮች ማረጋገጡ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#Peace

የኢፌዴሪ ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ እንደሚቋጭ እና ሰላምም እንደሚሰፍን ተናገሩ።

ይህንን የተናገሩት በቡራዩ ከተማ የተገነባ የልዩ ተሰጥኦ ማበልፅጊያ ኢንስቲትዩት በመረቁበት ወቅት ባሰሙት ንግግር ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው " በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ነገር ይቋጫል፤ ኢትዮጵያም ሰላም ትሆናለች " ብለዋል።

" እንዲሁ እንደተዋጋን አንቀጥልም ያሉት " ጠቅላይ ሚኒስትሩ "በሰላም፣ በልማት የትግራይ ወንድሞቻችንን ለማልማት በጋራ የምንቆምበት ጊዜ ቅርብ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ" ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ በንግግራቸው ላይ የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት መቋጫ ስለሚያገኝበት እና ሰላም ስለሚሰፍንበት መንገድ በዝርዝር አልተናገሩም።

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከተጀመረ የፊታችን ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ/ም ሁለት ዓመት የሚደፍን ሲሆን ጦርነቱ በተለያየ ጊዜ የተለያየ ክስተት እያስተናገደ ዛሬ ላይ ደርሷል።

ይኸው ጦርነት የበርካታ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን ሚሊዮኖችን ከቀያቸው አፈናቅሏል፣ ለችግርም ጥሏል።

ጦርነቱ ባመጣው መዘዝ ባለፉት በርካታ ወራት የትግራይ ክልል ነዋሪዎች እና ከትግራይ ክልል አዋሳኝ በሆኑ የአማራ እና አፋር ክልል አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች መሰረታዊ አገልግሎት ለማግኘት አዳጋች ሆኖባቸዋል።

ጦርነቱ እንዲቋጭ የተለያዩ የሰላም ጥረቶች እየተደረጉ ሲሆን የፊታችን ሰኞም በአፍሪካ ህብረት መሪነት በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል በደቡብ አፍሪካ የሰላም ንግግር ይጀመራል ተብሎ ቀን ተቆርጧል። በዚሁ የሰላም ንግግር ላይ ለመሳተፍ መንግስት ቁርጠኛ ነኝ ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሰላም ስምምነት ዛሬ በፕሪቶሪያ ይፈረማል። ነገር ግን የስምምነቱ ትግበራ " ወሳኝ ይሆናል " ሲሉ ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ አሁን ተናግረዋል። @tikvahethiopia
#ሰላም #Peace

" ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ "

በአፍሪካ ህብረት መሪነት በዛሬው ዕለት በፕሪቶሪያ በተደረሰው "  የሰላም 🕊 ስምምነት " መሰረት ፦

- በዘላቂነት ግጭት ለማቆም ፣
- ለተቸገሩ ወገኖች ሁሉ የሰብዓዊ እርዳታ እንዲደርስ
- የሰላማዊ ዜጎችን ደኅንነትን ለማረጋጋጥ
- #አገልግሎቶችን_ለማስጀመር ስምምነት ላይ ተደርሷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Peace

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምን አሉ ?

የፕሪቶሪያ ስምምነትና የዛሬው ናይሮቢ ስምምነት ተፈፃሚ እንዲሆን ለማድረግ በሙሉ ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

ጀነራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?

የዛሬው ስምምነት በትግራይ ውስጥ በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ስቃይ ያስወግዳል የሚል ተስፋ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።

ኡሁሩ ኬንያታ ምን አሉ ?

ኡሁሩ ኬንያታ በዛሬው መግለጫ ስምምነቱ በጦር ወንጀሎች ላይ " ተጠያቂነትን " ያጠቃልል እንደሆነ ለተጠየቀ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተው ነበር።

ኡሁሩ ኬንያታ ይህ " የመሳሪያ ድምፅ ፀጥ ሲል እና አስከፊው የሰብአዊ ሁኔታ ሲስተካከል " እንደሚመጣ ተናግረዋል።

" በሰላማዊ ሰዎች ላይ ግፍ የሚፈጽም አካል ላይ ከባድ ማዕቀብ ይጣልበታል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በናይሮቢው የሰላም ስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት የትግራይ ኃይሎች አዛዥ ጄነራል ታደሰ ወረደ በናይሮቢው ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ባለፉት ቀናት ለኃይሎቻቸው ኦረንቴሽን ሲሰጥ እንደነበር እና ይኸው ኦረንቴሽን በቀጣይ ሁለት ቀን እንቀሚያልቅ ገልፀዋል። ይህን የገለፁት በክልሉ ለሚገኙት የመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ነው። ጄኔራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ? " በናይሮቢው…
#Update #Peace

በሰላም ስምምነቱ መሰረት የትግራይ ታጣቂዎች በስራቸው ከነበሩ የውግያ ግምባሮች ለቀው መውጣት እንደጀመሩ ተገልጿል።

ታጣቂዎቹ ከደቡብ ፣  ማይ ቅነጣል፣ ዛላምበሳ፣ ነበለት ፣ ጨርጨር ፣ ኩኩፍቶ ፣ ሕጉምብርዳ ፣ በሪተኽላይ እና አበርገለ ለቆ ግንባሮች ነው መውጣት እንደጀመሩ ከክልሉ መገናኛ ብዙሃን የተሰማው።

ከጥቂት ቀናት በፊት ጄነራል ታደሰ ወረደ (የትግራይ ኃይሎች አዛዥ) በሰጡት መግለጫ በናይሮቢው ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለኃይሎቻቸው ኦረንቴሽን ሲሰጥ እንደነበር እና ይኸው ኦረንቴሽን እንዳለቀ ኃይላቸው ካለበት ቦታ Disengage አድርጎ / ተላቆ የውጊያ ግንባሮች #የማፍረስ እና ሰራዊቱ ወደ ተቀመጠለት ቦታ እንደሚጓጓዝ መግለፃቸው አይዘነጋም።

ጄነራል ታደሰ ፤ " የሎጅስቲክስ አቅማችን ወይም የማጓጓዝ አቅማችን እስከፈቀደ ድረስ በአንድ ጊዜም ልናነሳው እንችላለን ምናልባት የተወሰኑ ቀናት ሊወስድ ይችላል " ማለታቸውም የሚወስ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Peace

የሰላም ስምምነቱን በተመለከተ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከሃይማኖት ተቋማት እና ሲቪክ ማህበራት ጋር ውይይት አድርገው ነበር።

በዚህ ውይይት ላይ ምን አሉ ?

- የሰላም ስምምነቱ #የህዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።

- የሰላም ስምምነቱ ፤ ከፍተኛ የሆነ ችግር ላይ ያለውን ህዝብ ለማዳንና ህዝቡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን እንዲጠቀም ሰላም እንዲያገኝ ለማድረግ የተደረሰ መሆኑን ገልፀው ሌሎች ጉዳዮች በህገመንግስት መሰረት ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚፈለግላቸው መሆኑን ገልፀዋል። ስምምነቱ ከምንም በላይ ተኩስ የማቆም ጉዳይ ነበር ሲሉ ተናግረዋል።

- የተደረሰው  የሰላም  ስምምነት  ተግባራዊ እንዲሆን እየተሰራ ባለበት በዚህ ወቅት ላይ አሁንም የኤርትራው ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ ኃይል በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ግፍ እየፈፀመ፣ ንብረት እየዘረፈ ፣ እያወደመ መሆኑና ስምምነቱ እንዲደናቀፍ እየሰራ እንደሆነ ገልፀው የፌዴራል መንግስት የህዝቡን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነበት ስላለበት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

- በስምምነቱ መሰረት ሰብዓዊ እርዳታ እና መድሃኒት እየገባ መሆኑን ተናግረዋል። " ስምምነቱ ላይ ድጋፍ በአቸኳይ እንዲገባ የሚል ነገር ነበር በወቅቱ ወዲያው የገባ ድጋፍ አልነበረም አሁን ግን ቀስ በቀስ የሚገባው ሰብዓዊ ድጋፍ እየጨመረ ነው " ብለዋል። እህል እና መድሃኒት ይዘው የሚገቡ ተሽከርካሪዎች እየጨመሩ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ደብረፅዮን ፤ ዓለም አቀፍ እርዳታ አቅራቢዎች በሙሉ ወደ እንቅስቃሴ ገብተዋል ብለዋል።

- ወደ ክልሉ ከሚገባው የሰብዓዊ እርዳታ ጋር በተያያዘ በስምምነቱ መጀመሪያ ሰሞን ላይ አስፈላጊው ስራ በጊዜ ስላላለቀ እና ባለመዘጋጀቱ ወደ ትግበራ እንዳልተገባ አሁን ላይ ግን ሁሉም ዝግጁ መሆኑን ፣ የሚያደናቅፍ ነገር እንደሌለው ፣ በመንገድ ላይ የነበረው በርካታ ፍተሻና የቁጥጥር ጣቢያዎች አሁን መስተካከሉን ተናግረዋል።

- ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ፤ " የተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች መልሰው አልተከፈቱም " ያሉ ሲሆን " በኛ በኩል ሙሉ ዝግጅት አድርገናል #ባንክ#ቴሌኮም እንዲጀምር ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለን አነስተኛ አቅም እየተጠቀምን ብንቆይም መስተካከል ያለባቸው ነገሮች መስተካከል አለባቸው። በፌዴራል አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ እያንዳንዳቸው ተፈትሸው ስራ ለመጀመር ምን ያስፈልጋቸዋል  ?  የሚለው ተጠንቷል። አገልግሎት ወደ ነበረበት ለመመለስ ሙሉ ዝግጅት ተደርጓል ፤ አሁን የሚቀረው ስርዓት አስይዞ ከፌዴራል አገልግሎት ሰጪ አካላት ጋር በመነጋገር በቅደም ተከተል ማስፈፀም ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA #PEACE

በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት ትግበራ " ተስፋ ሰጪ ነው " ሲሉ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የገለፁት የናይሮቢ ሁለተኛውን ውይይት ተከትሎ የሰላም ሂደቱ በተገመገመበት ወቅት ነው።

ዛሬ የናይሮቢውን ውይይት ተከትሎ የሰላም ሂደቱ የተገመገመ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግምገማውን ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው  " የሰላም ስምምነቱ የትግበራ ሂደት ተስፋ ሰጪ ነው። " ብለዋል።

" አሁንም ለሰላም ባለን ቁርጠኝነት ጸንተናል " ሲሉ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #Mekelle ዛሬ በአፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ የሚመራ የፌደራል መንግሥት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን የትግራይ መዲና መቐለ አቅንቷል። የልኡካን ቡድኑ ወደ መቐለ ያቀናው የሰላም ስምምነቱን የትግበራ ሂደት ለመቃኘትና በስምምነቱ የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች በታቀደው መሠረት እንዲፈጸሙ ለማድረግ ነው ተብሏል። የልኡካን ቡድኑ ከሁለት ዓመት በኋላ ወደ መቐለ የተጓዘ የመጀመሪያው የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ…
ፎቶ ፦ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ የተመራው የፌደራል መንግስት ልኡካን ቡድን የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ገብቷል።

ቡድኑ መቐለ ሲደረስ የሃይማኖት አባቶች ፣ እነ አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ ዶ/ር ሀጎስ ጎደፋይን ጨምሮ ክልሉን እያስተዳደሩ የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገዋል።

#Peace #Ethiopia

Photo Credit : Demtsi Weyane / ድምፂ ወያነ

@tikvahethiopia