TIKVAH-ETHIOPIA
#የጀግኖቹ_ወላጆች ❤️ የኢትዮጵያን ስም በዓለም ላይ ከፍ እያደረጉ ካሉት አትሌቶቻችን መካከል ቤተሰቦቻቸው የግንኙነት መስመር ከዓመት በላይ በተቋረጠበት ትግራይ ክልል ውስጥ ይኖራሉ። እነሱን ጨምሮ ሁሉም የትግራይ ህዝብ የኢንተርኔት ግንኙነት ባለመኖሩ ስሜቱን እንደኛ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለማጋራት አልታደለም። ከከተሞች ወጣ ባሉ የትግራይ ክልል ክፍል የሚኖሩ የአትሌቶች ቤተሰቦችም የልጆቻቸውን ድል…
#ሰላም #Peace

የጎተይቶም የሰላም ምኞት !

ጎተይቶም ገብረስላሰ የሴቶች ማራቶን #የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ፦

" ... ምኞቴ ሰላም ነው። ሰላም በምንም ነገር አይገኝም።

እኛ በጣም ነው ሰላምን የምንፈልገው። ዓመት ከስምንት ወር ሆኖብናል የወላጅ ናፍቆት ቀላል አይደለም።

እናቴ እንዳለችው እኔ ናፍቆት አልችልም። ማይቻል ነገር ግን የለም። ችለን እዚህ ደረስን እንጂ እኔ ናፍቆት አልችም ነበር።

አንድ ቀን ሳልደውልላት አልተኛም። አባት፣ እናቴን በጣም እወዳለሁ፤ አባቴን በጣም ነው የምወደው በዛ የተነሳ ስልክ ሳልደውልላቸው አልተኛም ነበር።

ማይቻል ነገር የለም ብላዋለች እናቴ ናፍቆትን አትችልም እሷ ይሄን ሁሉ ተቋቁማ እዚህ መድረሷ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ነው ያለችው ትክልል ነው ማይቻል ነገር የለም ችዬዋለሁ።

እግዚአብሔር ሰላም አምጥቶ እንዲያገናኘን ነው ምኞቴ። "

ጎተይቶም ገብረስላሰ የኢትዮጵያን ህዝብ ስሜት በተመለከተ፦

" .. እያየሁ ነበር የነበረውን ድባብ፣ የነበረውን ደስታ እንደዚህ ስንሆን ነው የሚያምርብን ፤ ሁሉን ነገር ትተን #ለሰላም ስንቆም ነው።

ለካ ይሄንን ያህል በህዝቡ ልብ ውስጥ አለን ብዬ ነበር ለራሴ ፤ ደጋግሜ እያየሁ ነበር።

እርግጥ ውድድሩ አጓጊና እልህ አስጨራሽ ነበር በጣም ፤ በዛ የተነሳ ሰው ስሜታዊ ሆኖ ነበር በጣም ነው የማመሰግነው። በፀሎትም፣ በሞራልም የደገፉኝ ሰዎች በጣም ነው የማመሰግነው።

ሁለተኛ ትልቅ ደስታ ነው የፈጠረብኝ። ይሄን ያህል ህዝብ ነበር ለካ የሚከታተለው ብዬ ለራሴ ውስጤን እንድጠይቅ ነው ያደረገኝ "

(አትሌት ጎተይቶም ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጠችው ቃለምልልስ)

@tikvahethiopia