TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ማስጠንቀቂያ‼️

ልዩነትን የምታሰፉ እና ብጥብጥ በሚፈጥሩ እንቅስቃሴዎች የምትሳተፉ፦ #አክቲቪስቶች እና #የፖለቲካ_ፓርቲዎች ከድርጊታችሁ ተቆጠቡ ካልሆነ ግን የማያድግም #እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል በዶ/ር ዐብይ የሚመራው መንግስት‼️

#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ንቁ! #ሰውነት_ከምንም_ይበልጣል!
ሀገር
ብሄር
ዜግነት
ባንዲራ...ሁሉም ነገር እኛ እንደሰው ልጅ ካልተከበርን #አይጠቅሙንም። ሰው ሲገደል፣ ሰው ሲደበደብ፣ ሰው ሲፈናቀል ልባችን #ሊደማ የሚገባው የኛ #ብሄር ተወላጅ ስለሆነ አይደለም እንደኛ ሰው #ብቻ ስለሆነ መሆን አለበት። ያን ጊዜ ለሰማይም ለምድርም መልካም ስራን ሰርተን ማለፍ እንችላለን። ከሁሉም የሚበልጠው ሰውነት ብቻ ነው። ትግሬው የአማራው፤ አማራው የትግሬው ሞት ካላስለቀሰው፣ ኦሮሞው የአማራው፤ አማራው የኦሮሞው ሞት እና ስቃይ ካልተሰማው፣ ኦሮሞው የጋሞው ጋሞውም የኦሮሞው ችግር እና መከራ ካልተሰማው፣ ሲዳማው የወላይታው፤ ወላይታው የሲዳማው ሞት እና ስቃይ ካላስለቀሰው ችግሩ #የፖለቲካ ሳይሆን የሰውነት ስሜት መጥፋት ነው። የሰውነት ስሜት መጥፋት ደግሞ በቁም #መሞት ነው።

መፍትሄው....

እኔም አንተም አንቺም በገባን ልክ ስለሰው ክቡርነት እናስተምር። በየቤታችን ስለሰውነት እንነጋገር። ታች ወርደን ስለሰውነት እናስተምር። ሁላችንም ትልቅ ሀላፊነት አለብን! መጀመሪያ ሰው ሁሉ እንዲከበር፣ እንዲወደድ፣ እንዲፈቀር እንስራ!


ፀጋአብ ወልዴ
#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሸዋሮቢት‼️

በሸዋሮቢት ከተማ የተከሰተው አለመረጋጋት ከተፈጸመው #አሰቃቂ_ግደያ ጋር ተያይዞ ማህበረሰቡ ብሶቱን ለመግለጽ እንጂ ከየትኛውም #የፖለቲካ ጉዳይ ጋር የተያያዘ አለመሆኑን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ኢ/ር #ሞገስ_ባየህ ለአማራ ብሁሃን መገናኛ ለ91.4FM በስልክ በሰጠው መግለጫ አስታውቀዋል።

የከተማው ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ለ91.4 FM እንዳገለጹት #ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውሏል አስፈላጊውን የምርመራ ስራ ተሰርቶና ተጣርቶ ህጋዊ #እርምጃ እንዲወሰድ ይደረጋል ውጤቱንም ለህዝብ እናሳውቃለን ህብረተሰቡ ከስሜታዊነት ወጥቶ በተረጋጋ መንግድ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጠይቀዋል።

እንደ ሀላፊው ገለጻ ከአካባቢው የሀይማኖት አባቶች፣ ሀገር ሽማግሌዎች እና ከከተማው ህብረተሰብ ጋር በመከካከር ወደ ነበረበት ሰላም ለመመለስ የምክክር ስራ ይሰራል ብለዋል። አሁን ከህብረተሰቡ የሚጠበቀው በሰላም ወደ እየቤቱ መመለስ እንዳለበት የተዘጉ መንገዶችን ከፍቶ መንገደኞችን #መሸኘት እንደለበት አሳስበው ድርጊቱ ግን ብሶትን /ቁጭትን/ ለመግለጽ እንጂ #የፖለቲካ_አጀንዳ እንደሌለው ሀላፊው ተናግረዋል። የጸጥታ ሀይሉም ጉዳዩ በህግና በህግ እንዲያልቅ የማረጋጋት ስራ እየሰራ ነው።

Via Shewa Robit City Administration Kentiba office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያን እንፈልጋታለን‼️

ምስኪኑ ዜጋ ሲፈናቀል፣ ሲሰቃይ፣ ሲቸገር፣ ተበደልኩ ሲል፣ ፍትህ ተነፍጊያለሁ ብሎ ሲጮህ፣ መንግስት በድሎኛል ብሎ ሮሮውን ሲያሰማ ለርካሽ #የፖለቲካ_ትርፍ እና #ሀገር_ለማትራመስ የምትሯሯጡ ጨካኝ አረመኔ ሰዎች ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ሰብስቡልን።

ሰዎች ሰውነታቸውን ክደው #ሀዘናቸውን እንኳን #ብሄር ለይተው እንዲገልፁ የምትገፋፉ ሰውነታችሁን የከዳችሁ ሁሉ #ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ከሀገራችን ላይ አንሱ።

በደንብ ስሙኝ...🔥

ህዝቡን በብሄር ከፋፍላችሁ #ወደጦርነት ለመክተት ፌስቡክ ላይ #ተዘፍዝፋችሁ የምትውሉ ሰዎች--የምትወዱትን ማጣት ስትጀምሩ፣ ምስኪን ህፃናት እንደቅጠል ሲረግፉ ማየት ስትጀምሩ፣ ሚሊዮኖች ሰላም ፍለጋ መሰደድ ሲጀምሩ ስታዩ ደም እምባ እያለቀሳችሁ እያንዳንዷን ፌስቡክ ላይ የዋላችሁበትን ቀን #ትረግሟታላችሁ
.
.
መንግስት በአስቸኳይ #ፍትህ እንፈልጋለን ብለው የሚጮሁ ዜጎች ካሉ ያዳምጥ፤ ምላሽ ይስጥ፤ በምስኪን ዜጎች ህይወት ላይ #ቁማር የሚጫወቱ የፖለቲካ ነጋዴዎችንም አደብ ያስገዛ!

#FACEBOOK ከብዶናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ለሦስት ቀናት በመተከል ዞን ደንጉር ወረዳ የተከሰተው ግጭት ከትናንት ቀን አጋማሽ በኋላ ወደሠላም ተመልሷል፡፡››

‹‹የጥምረት ኮሚቴው ለኅብረተሰቡ ሰላም እንዲያረጋግጥ እና አጥፊዎች እንዲጠየቁ እየሠራ ነው፡፡›› የአማራ ክልል ሰላምና የሕዝብ ደኅንነት ጉዳዮች ቢሮ

.
.
የአማራ ክልል ሰላምና የሕዝብ ደኅንነት ጉዳዮች ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኮሎኔል አለበል አማረ ዛሬ ለአብመድ በሰጡት መግለጫ ከሦስት ቀናት በፊት ጀምሮ በቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ላይ የተከሰተው ግጭት ከትናንትና ቀን አጋማሽ በኋላ #ወደሰላም መመለሱን አስታውቀዋል፡፡

ኮሎኔል አለበል እንደተናሩት ችግሩ ከተከሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ትናንት እኩለ ቀን ድረስ በደንጉር ወረዳ 30 ቀበሌዎች ጠንከር ያሉ ጥቃቶች ተፈጽመው የሰው ሕይወት አልፏል፤ ቤቶች ተቃጥለዋል፤ የአካል ጉዳትም ደርሷል፡፡ ለዜጎቹ ሰብዓዊ ዕርዳታ እንዲያገኙ እየተደረገ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

የግጭቱ መነሻ በሁለት ግለሰቦች የትራንስፖርት ክፍያ ‹ጨምር አልጨምርም› የተጀመረ ቢሆንም ከበስተጀርባ ግጭቱ እንዲባባስ የሚፈልጉ የአከባቢው መዋቅር እና ረጅም ጊዜ እቅድ ያላቸው #የፖለቲካ_ኃይሎች አሉ፡፡ በሌሎች ማንነቶች ላይ የተፈጠረው ግጭት በጉሙዝ እና በአማራ ነዋሪዎች ላይ የተቃጣ እንዲመስል አድርጓል ብለዋል፡፡

ከቤኔሻንጉል ጉሙዝና አማራ ክልሎች እንዲሁም የፌዴራል ጥምር ኃይል ኅብረተሰቡ እንዳይፈናቀል እና ሰላሙ እንዲያረጋግጥ እንዲሁም አጥፊዎች እንዲጠየቁ እየሠራ እንደሆነም ኮሎኔሉ በመግላጫቸው ጠቅሰዋል፡፡

በተያያዘም ኮሎኔል አለበል ቀደም ብሎ በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር አካባቢዎች ተፈጥረው በነበሩ ግጭቶች ላይ የተሳተፉትን በሕግ ቁጥጥር የማዋል ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

‹‹በቀጠናው የተፈጠረው የግጭት መነሻ አንዳንድ የፖለቲካ ኃይሎች እና ከድርጊቱ ትርፍ የሚሹ ‹አክቲቭስቶች› ጥንስስ ነው፡፡ ጥቃቱን የፈፀመው የእነዚህን ኃይሎች ጥያቄ ተሸክሞ ራሱን ‹እንትና ነኝ› ሳይል በህቡዕ የሚንቀሳቀስ ሰፊ የሽብር ግብረ ኃይል መሆኑን አረጋግጠናል›› ብለዋል ኮሎኔል አለበል በ መግለጫቸው፡፡

አንድ የመከላከያ ሠራዊት ግለሰብ ‹ግጭቱን የፈጠሩት የአማራ ክልል ልዩ ኃይሎች ናቸው› ብለው የሰጡት መረጃ ትክክል እንዳልሆነ በኋላ ላይ ከመከላከያ ጋር የጋራ መደረጉንም አስታውቀዋል፡፡ ‹‹የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ከሽብር ኃይሎች ጥቃት ሕዝቡን ሊጠብቅ ብቻ የሂደ ነው›› ሲሉም አስረድተዋ፡፡

በአማራ ክልል በየወቅቱ የተለያዬ መልክ እየያዙ የሚስተዋሉ ግጭቶችን በመፍታት በዘላቂነት ሰላም ለመፍጠር እንደመንግሥት ከቀደሙ ችግሮች ትምህርት መወሰዱንም ነው ምክትል ቢሮ ኃላፊው የተናሩት፡፡ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱም የጋራ ጥቅም ላይ እንዲመሠረት ጥረቶች እንዳሉ አስውቀዋል፡ ኅብረተሰቡም በዚህ ወቅት ለሰው ቅርብ ተደርው የሚፈጠሩ ግጭቶች የታለመላቸው መሆናቸውን በመጠርጠር ከፀጥታ አካላት ጋር አብሮ በመሥራት ብቻ የሚፈቱ እንደሆኑ እንዲረዳ ኮለኔል አለበል አሳስበዋል፡፡

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሀገራዊ ሰላም በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ በማስተላለፍ ውሳኔውን የሚያስፈጽሙ አባቶችን ሰይሟል። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ 23 የመወያያ አጀንዳዎችን አጽድቆ በመወያየት ልዩልዩ ውሳኔዎችን ማስተላለፍ ጀምሯል። ዓመታዊው የግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ ግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ.ም በጸሎት ከተጀመረ በኋላ በትላንትናው ዕለት በጠዋቱ መርሐ ግብር…
#Update

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የቀጠለ ሲሆን ትላንት ግንቦት 18፣ 17 እና 16 በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክሯል።

በትላንት የጉባኤው ውሎ በትግራይ ክልል የሚገኙ አባቶች ያስተላለፉትን መግለጫ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያይቶበታል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ወቅታዊውን ችግር ተከትሎ በትግራይ ክልል የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሰጧቸውን መግለጫዎች መመልከቱን ቃላቸውንም ከመገናኛ ብዙኃን ማድመጡ ተገልጿል።

በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ ጉዳዩ የሃይማኖትና የቀኖና ልዩነት ሳይሆን #የፖለቲካ_ችግር መሆኑን በመረዳት ሰፊ ውይይት ማድረጉን ለማወቅ ተችሏል።

ሌላው ጉባኤው የሃይማኖት ህጸጽ ተገኝቶባቸው ከቤተክርስቲያንና ምእመናን አንድነት በውግዘት የተለዩ ግለሰቦች ያቀረቡትን የይቅርታ ደብዳቤተመልክቶታል፡፡ በዚህም ምልዓተ ጉባኤው ይቅርታ ጠያቂዎቹ በቃል የተናገሩትን በመጽሐፍ የጻፉትን በተግባር ያደረጉትን የሊቃውንት ጉባኤ መርምሮ ለምልአተ ጉባኤው እንዲያቀርብ ወስኗል፡፡

በሰሜን አሜሪካና በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች በተከሰቱ ችግሮች ላይ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን በተጨማሪ በቤተክርስቲያኗ የልማት ሥራ በጀት በሚያስፈልጋቸው አጀንዳዎች ላይ ውይይት አድርጓል። ጉባኤው በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሕክምና ዙርያም ውይይት አድርጓል፡፡

በግንቦት 17 ውሎው በሀገራችን ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ያተኮሩ ልዩ ልዩ አጀንዳዎችን ተመልክቷል።

በሌላ በኩል ጉባኤው በግንቦት 16 ውሎ በተለያዩ ጉዳዮች ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።

በእስር ላይ ቆይተው የነበሩ የአ/አ ሀገረ ስብከት አገልጋዮች ያቀረቡትን አቤቱታ ተመልክቷል።

የብፁዓን አባቶች ምደባ ተከናውኗል እንዲሁም #በወቅታዊ ጉዳይ #ለመንግሥት በሚላክ ደብዳቤ ላይ ውሳኔ አስተላልፏል - telegra.ph/EOTC-TV-05-27-2

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚደረግ የበጀት ድጎማ ከመደበኛው ሥራ ይልቅ ከዋናው ተልዕኮ ውጪ ለሆነ #የፖለቲካ_ሥራ እንደሚውል በፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የተጠና ጥናት ላይ መገለፁን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ኮሚሽኑ ጥናቱን ያከናወነው በፌዴራል ደረጃ በሚገኙ የመንግሥትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የጥናቱ ትኩረት ሙስናና ብልሹ አሠራር በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚያደርሰውን የሙስና ሥጋት ለመለየት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ከምንጮቼ አገኘሁት ያለውና ኮሚሽኑ በተመረጡ 61 ተቋማት ላይ ያደረገው የጥናት ሪፖርት እንደሚያሳየው ፦

- በተቋማቱ፤ ከመምህራን ልማት እና ከአሠልጣኞች ምልመላ ጋር በተገናኘ፣ የዘመድና የፓርቲ አሠራር፣ እንዲሁም አድልኦና ጉቦ የመቀበል አዝማሚያ በስፋት ይስተዋላል።

- በመምህራንና ሠራተኞች አስተዳደር ክፍል ሕገወጥ ቅጥርና ዝውውር መኖር፣ መምህራን ተማሪዎችን ለይቶ ለመጥቀም የሚደረግ ዝንባሌ መኖር፣ ለመምህራን ቅጥር ውድድር ተፈልጎ እኩል ውጤት ሲመጣ፣ አንዱን በትውውቅ ብቻ የመምረጥ አሠራር እንደሚስተዋል ተገልጿል፡፡

- ከሐሰተኛ የትምህርት ሰነድ ጋር በተያያዘ የብቃት ማረጋገጥና ፈቃድ አሰጣጥ ላይ መሥፈርት ሳያሟሉ፣ ለተቋማት ፈቃድ መስጠት እና የፈቃድ ዕድሳት እንደሚከናወን ተግልጿል።

- መምህራንና በትምህርት አስተዳደር አመራር ላይ ያሉ ሠራተኞች ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች እንደተገኘባቸው ፤ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጣራት ሲሞከር ደግሞ ሠራተኞች ከሥራ ቀድመው የመልቀቅ እንቅስቃሴ እንዳለ ተገልጿል።

- በግል ኮሌጆች የሲኦሲ ምዘና ሳያልፉና ትምህርት አጠናቀው ሳይጨርሱ፣ እንዲሁም ፈጽሞ ያልተማሩ ሰዎች የትምህርት ማስረጃ አትሞ መስጠትና በኮሌጆች ሽያጭ የመፈጸም ድርጊት መኖሩን ሪፖርቱ ገልጿል።

- በኮሌጆችና በዩኒቨርሲቲዎች ሬጅስትራሮች ውስጥ የተማሪዎችን ውጤት የማሳሳትና የማጭበርበር ድርጊት እንዳለ ተጠቅሷሳ።

- በግል ትምህርት ተቋማት ውሳኔዎች የሚተላለፉት ለተቋማቸው መልካም ስም ቅድሚያ በመስጠት እንደሆነ፣ በመንግሥት ተቋማት ደግሞ ሰነድ ማዘጋጀት እንጂ ትግበራ ላይ እምብዛም እንደሌሉበት ተገልጿል።

- በተደረገው ጥናት በተቋማቸው ውስጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ ወይ ተብለው ከተጠየቁት ውስጥ 65 በመቶ የሚሆኑት " አዎ " የሚል መልስ መስጠታቸውን፣ 35 በመቶ የሚሆኑት " የለም " የሚል መልስ ሲሰጡ፣ በተመሳሳይ የሙስና ችግሮች መኖራቸውን 66 በመቶ መናገራቸውና 47 በመቶ ደግሞ ለሚቀርቡ ጥቆማዎች ከተቋማቱ መልስ እንደማይሰጥ ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

- በትምህርት ተቋማቱ የመምህራን በተደጋጋሚ ወደ ክፍል አለመግባት፣ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ መስጠት፣ በአመራር የሚከናወን ስርቆት፣ ሕገወጥ ዝውውርና የደረጃ ዕድገት፣ ሕግና ደንብን ተከትሎ የማይከናወን ግዥ፣ የመረጃና ማስረጃ ማጭበርበር፣ ግልጽነት የሌለው አሠራር መብዛት፣ በሬጅስትራር የሚፈጸም ብልሹ አሠራር ተቋማቱን ለከባድ ሙስና አደጋ ጥሏቸዋል፡፡

- በግዥ ወቅት ለተቋም የማያስፈልግ ንብረት እንዲገዛ ተጨማሪ በጀት ማስያዝ፣ በጨረታ ወቅት የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ እንዲጋብዝ አድርጎ ሰነድ ማዘጋጀት፣ ወቅቱንና ጥራቱን ያልጠበቀ ግንባታ እንዲከናወን ማድረግ፣ በሕንፃ ርክክብ ጥራቱን ያልጠበቀ ሕንፃ እንዲገነባ ማድረግና ያልተጠናቀቀ ሕንፃ መረከብ ተቋማቱን ለከባድ ሙስና እንዳጋለጣቸው ሪፖርቱ ያሳያል።

እንደ ምክንያት የተጠቀሱት ችግሮች ምንድናቸው ?

• የሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ ፣
• የተጠናከረ የቁጥጥር ሥርዓት አለመኖር፣
• የሞራል መላሸቅ፣
• የተጠያቂነት ማነስ፣
• የላላ የአመራር ቁጥጥርና ከፍተኛ የሆነ የበጀት ምደባ የሚሉት ይገኙበታል።

ጥናቱ በሚደረግበት ወቅት ምን ችግሮች አጋጠሙ ?

➤ የተቋማት አመራሮች በቦታው ላይ አለመገኘት፣
➤ ተቋማት መረጃ ለመሥጠት ፈቃደኛ አለመሆን፣
➤ የተቋማት አመራሮች እና ሠራተኞች መረጃዎችን በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመሥርቶ አለመስጠት ... መሰል ዓይነት ችግሮች ነበሩ።

ሪፖርተር 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-09-25

@tikvahethiopia
" ዳግም #ሞት እና #ውድመት ውስጥ መግባቱ ይቅርብን " - የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ፤ በሀገራችን እየተካሄደ ያለው ጦርነት ባስቸኳይ እንዲቆምና ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ ተማጸነ።

" ዳግም ሞት እና ውድመት ውስጥ መግባቱ ይቅርብን " ሲልም ጥሪ አቅርቧል።

ጉባኤው በላከልን መግለጫ ጦርነት ለየትኛውም አይነት የፖለቲካዊ ችግር መፍትሔ ሆኖ አያውቅም ብሏል።

" ፖለቲካዊ ችግር መፈታት ያለበት መከባበር ባለበት የጋራ ጥቅም በሚያስቀድም ሁኔታ በሚደረግ የፖለቲካ ውይይት ነው " ያለው ጉባኤው ፤ " ውይይቱ ፦
- ብሶት የወለዳቸውን ምሁራንን፣
- የሀገር ሽማግሌዎችን፣
- የሃይማኖት አባቶችን፣
- ወጣቶችን እና ሴቶችን ጭምር ያካተተ ቢሆን የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ሙሉ እምነታችን ነው " ሲል ገልጿል።

ይህ እንዲሆን የመንግሥት #የፖለቲካ_ፈቃደኝነት በጣም አስፈላጊ እንደሚሆን አመልክቷል።

ምክንያቱም " መንግስት ከሁሉም በላይ እኛ በብዙ መልኩ ወንድማማችና እህትማማች የሆነውን ኢትዮጵያውያንን በጋራ የማምጣት አቅም አለው ብለን ስለምናምን ነው " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ በዚሁ መግለጫው ፤ በሀገራችን እየተካሄደ ያለው ጦርነት ባስቸኳይ እንዲቆምና በውይይት ችግሮች እንዲፈቱ መንግስትንና ተፋላሚ ወገኖችን አጥብቆ ተማጽኗል።

" በዚህ በፍልሰታ ጾም ጸሎት ወቅት ልቦናችንን ወደ እግዚአብሔር እንድንመልስ ፤ ስለ ሰላም ፣ ፍትህ፣ ውይይት እንድንጸልይ ለምዕመኖቻችንና በጎ ፊቃድ ላላቸው ወገኖቻችን ሁሉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን " ብሏል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

" ... አሁንም ቢሆን ለያዥ እና ገናዥ አስቸጋሪ የሆነው የመንግስት አቋም ነው " - መረራ ጉዲና (ፕሮፌሰር)

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ( #ኦፌኮ ) ሊቀመንበር መረራ ጉዲና (ፕ/ር) በሀገራችን ጉዳይ ላይ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

Q. በተለያዩ ቦታዎች ያለውን የጸጥታው ችግር እንዴት ትገመግሙታላቹ ? መፍትሄውስ ምንድን ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" ብሔራዊ እርቅ እና ብሔራዊ መግባባት የሚባለውን እኮ ከኢህአዴግ መጀመሪያ ዓመት ጀምሮ እስከ 30 ዓመታት ስንጠይቅ ቆይተናል።

አሁንም ቢሆን መልክ አልይዝ እያለ ያስቸገረው / ለያዥና ለገናዥ አስቸጋሪ የሆነው የመንግስት አቋም ነው።

ስልጣንን በMonopoly መያዝ ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ እንደ ባህል ተይዟል። አሁንም ቀጥሏል። የኢትዮጵያ መሪዎች ከዛ አልወጣ አሉ። ውጤቱ ደግሞ የታወቀ ነው። 

ደርግ ወጣቶችን ጨፍልቆ ነው የሄደው ፤ ኢህአዴግ ለ27 ዓመታት አገሪቱን ቀላል ያልሆነ ቀውስ ውስጥ ከቷት ነው ጡረታ የወጣው ፤ ብልጽግናም በባሰ መንገድ ይህንኑ ሁኔታ እየተከተለ ነው።

የኢትዮጵያ ጸጥታ ሁኔታ ' ከድጡ ወደ ማጡ ' ተብሎ የሚገለጽበት ደረጃ ላይ ነው።  መፍትሄው ቁጭ ብሎ መወያዬት ነው።

ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን #ከመገዳደል ፓለቲካ ወደ #መደራደር ፓለቲካ ማምጣት እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። "

Q. በየጊዜው የንጹሐን ሕይወት በግፍ እየተቀጠፈ ነው። ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ መስራትም የሞት ጊዜን እንደማፋጠን ሆኖ ይስተዋላል።  መፍትሄ እንዲመጣ ምን እየሰራችሁ ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና፦

" ለ30 ይሁን ለ6ቱ ዓመታት በዴሞክራሲ የሚደረገው ለውጥ በተለይ ዴሞክራሲያዊ ምህዳርን እንዲያሰፉ ደጋግመን ስንጠይቅ ነበር።

አሁንም ያን መጠየቅ ቀጥለናል። ሜዳው / ምህዳሩ ግን በተቃራኒው እየጠበበ፣ አስቸጋሪ ሁኔታዎች በአገሪቷ ላይ እየተንሰራፉ የመጡበት ሁኔታ ነው ያለው።

ምህዳሩ ካልሰፋ፣ ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል መልክ ካልያዘ፣ ወጣቱንም ወደ ጫካ እየተገፋ የትም አያደርሰንም። "

Q. ከመንግስት የሚደርስባችሁ ጫና ምንድን ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" ከኦነግ ቀጥሎ ከፍተኛ ጫና ያለበት የእኛ ፓርቲ ነው።

ለምሳሌ የዛሬ 4 ዓመት ከ200 በላይ ቢሮዎች ነበሩን፤ አሁን ያሉን 3 ብቻ ናቸው። አባሎቻችን #ግድያ እና #እስራት ይፈጸምባቸዋል። 

ለምሳሌ ፦ የምሥራቅ ወለጋ የቢሮ ኃላፊ ከተወሰደ የት እንደገባ አላወቅንም 2 ዓመታት ሊሆነው ነው።

የምሥራቅ ሸዋ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላችን ለዚያውም የዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር ታስሯል።

አምቦ 4 ወጣቶች ታስረው 2 ሳምንታት ሆኗቸዋል። "

Q. #ብልሹ_አሰራርና #ሙስናን በተመለከተ ኢትዮጵያ በምን ደረጃ ትገኛለች ? መፍትሄውስ ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" በኢትዮጵያ ታሪክ የተለዬ/የከፋ የሙስና ደረጃ ነው ያለው።

መንግስትና ተቋማቱ የአንድ ቡድን ጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው ሲዋቀሩ እንዲህ አይነት ሁኔታዎች ይፈጠራሉ።

አሁንም መንግስት ተጠያቂነት ባለው መንገድ እንደገና ካልተዋቀረ በስተቀር፣ ከዚህ በሽታ የምንወጣበት መንገድ ያለ አይመስለኝም።

Q. የኑሮ ውድነቱ ሕዝቡን በእጅጉ አማሮታል። ፓርቲያችሁ ለመንግስት ያላችሁ ግምገማን ቢያጋሩ ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" ዜጎች እጅግ አስቸጋሪ ፣ ፈታኝ ሁኔታ ላይ ደርሰዋል።

መንግስት አስፈላጊ እርምጃ እንዲወስድ በተደጋጋሚ ተይቀናል።

መንግስት ግን ጆሮ ያለው አይመስልም። ችግሩ ግን እጅግ በጣም ፈታኝ ነው። "

Q. በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" የፓለቲካ ምህዳር ለማግኘት የመገዳደል ፓለቲካው እንዲቆም እየጠየቅን ነው። ምርጫ ከዚያ በኋላ የሚመጣ ነው።

ለነፃና ፍትሃዊ ምርጫ አስቻይ የሆነ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ የለም።

ትልልቆቹ አማራና ኦሮሚያ ክልሎች ጦርነት ውስጥ ናቸው። በዚህ ሁኔታ ምን አይነት ምርጫ እንደሚካሄ የምናየው ነው። መደራጀቱን ቀጥለናል። "

#TikvahEthiopiaFamilyAA

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ?

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ብሔራዊ_ፈተና

" በበይነ መረብ የሳይበር ጥቃት በመፈጸም ፈተናውን ለመስረቅ ጥረት አያደርጉም ብለን እንጠብቅም ፤ ያንን ለመከላከል ዝግጅት ተደርጓል  " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

በበይነ መረብ / #በኦንላይን የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሳይበር ጥቃት እንዳይሰረቅ ዝግጅት መደረጉን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል ፤ " በዚህ ዓለም ምንም አይነት ችግር የሌለበት ነገር የለም። ሁሉም ነገር የራሱ የሆነ ችግር / ጉድለት ይኖረዋል ያለን ምርጫች ግን ችግሩን የመከላከል አቅም ጎን ለጎን መገንባት ነው " ብለዋል።

" በበይነ መረብ የሳይበር ጥቃት በመፈጸም ፈተናውን ለመስረቅ ጥረት አያደርጉም ብለን እንጠብቅም " ያሉት ዋና ዳይሬክቲ ፥ " የሳይበር ደህንነት (ሴክዩሪቲ) ስራዎች ፦
° ሞያው ባላቸው ፣
° መሳሪያዎች ባሏቸው
° አቅም ባላቸው ተቋማት በኩል ተገቢ የሆነ ዝግጅት አድርገን እየሰራን ነው " ሲሉ አሳውቀዋል።

" በማህበራዊ ሚዲያ ስለ ፈተናው ብዥታ ለመፍጠር የሚፈልጉ ፣ ፈተናው ላይ ጥቃት ለመፍጠር የሚያስቡ አካላት ማወቅ ያለባቸው ይሄ #የፖለቲካ#የሃይማኖት ጉዳይ አይደለም ማንም ወላጅ ልጁን አስተምሮ የሚያደርስበት ስለሆነ ሁለት ሶስቴ ማሰብ አለባቸው ፤ ተማሪዎቹ ነገ ለሀገር እዳ እንዳይሆኑ ማሰብ ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።

ከኦንላይን ፈተናው ጋር በተያያዘ ማንም አካል ወላጆችን " ኮምፒዩተር አቅርቡ " አላለም ፤ ሊጠየቁም አይገባም ከተጠየቅም ስህተት ነው ተብሏል።

ፈተና የሚሰጠው መንግሥት በሚያቀርበው አቅርቦት / ኮምፒየተር እንደሆነ ተመላክቷል።

ይህ ማለት የኮምፒዩተር አቅም ኖሯቸው ት/ቤታቸውን ማገዝ የሚፈልጉ ዜጎችን አይችሉም ማለት አይደለም ተብሏል።

የወረቅት ፈተናን በተመለከተ አሁን ላይ ህትመት ወደ መጠናቀቁ ሲሆን ፈተናው ልክ እንዳለፉት ፈተናዎች ደህንነቱ እንዲጠበቅ በቂ ዝግጅት መደረጉ፣ በክፍል ውስጥም ኩረጃ እንዳይኖርና ተማሪዎች በራሳቸውን ሰርተው እንዲያልፉ ካለፈው #በጠነከረ ሁኔታ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ ተገልጿል።

#Ethiopia
#NationalExam
#Grade12

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 " አሁን ላይ ያሉ ችግሮች ምፍትሄ እስካላገኙ  ስለ ምርጫ ማሰብ #ቀልድ ነው " - አቶ ግርማ በቀለ የሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሕብር) ሊቀ መንበር አቶ ግርማ በቀለ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ቆይታ አድረገዋል። Q. የዜጎች በሕይወት የመኖር መብት ጥሰትን በተመለከተ ስለሚነሱ ጉዳዮች የፓርቲዎ ግምገማ ምን ይላል ?   አቶ ግርማ…
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል።

የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

Q. ከዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ጥሰት አንፃር የፓርቲዎን ግምገማና መፍትሄውን ቢገልጹ ?

አቶ ጀሚል ሳኒ፦

“ ሰዎች በተደጋጋሚ ሕይወታቸውን እያጡ ነው። በዋና ከተማዋ ሲይቀር ሰዎች እየታሰሩ፣ እየታገቱ ነው።

የትኛውም ዜጋ የደህንነት ስሜት እየተሰማው አይደለም። 

መንግስት #በዋነኛነት የተመሠረተበትና እንዲሰራው ኃላፊነት የተሰጠው ስራ ከየትኛውም ቅድሚያ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ የተዘነጋ የሚመስልበት ዘመን ላይ ነን።

በመወያየትና በመነጋገር ጦርነትን ማስቆም ይገባል።

ሰላምን ከማስፈን ይልቅ #ስልጣንን_የመጠበቅ ፣ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመስራት ነው አብዛኛው አቅም እየባከነ ያለው።

ከዚያ ይልቅ አገሪቱን በሚያሻግሩ ሀሳቦች ላይ አተኩሮ መስራት ያስፈልጋል።

ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦተ እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው። ”

Q. በሙስና ተዘፍቀው ስለሚገኙ ባለስልጣናት እንዲሁም በአጠቃላይ ስለብልሹ አሰራር ፓርቲዎ ምን ይላል ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ አሁን ላይ #ሀዘኔታዎች_የጠፉበት ፣ ሌላው ይቅርና የዜጎች ቤቶች ‘ሕገ ወጥ ናቸው’ ተብለው ቤታቸው የሚፈርስባቸው ሰዎች ላይ ገንዘብ የሚጠየቅበት ሁኔታ ነው ያለው። 

ከኢትዮጵያ Norm ሁላ ያፈነገጠበት ወቅት ላይ ነው ያለነው። በአብዛኛዎቹ መስሪያ ቤቶች የተለመደውን አይነት አሰራር ከመስራት ይልቅ ከእግሮች እጆች እየቀደሙ ነው።

#ሙስና_በግልጽ_እየተጠየቀ ፣ ቢሮ ውስጥ ሥራ አስፈጻሚዎች #በግልጽ_ድርድር እያደረጉበት ያለበት ሂደት ነው አሁን ያለው።

አለ የተባለ የትኛውም ችግርን ለመቅረፍ ላይከብድ ይችላል ፤ ነገር ግን ከተንሰራፋ የትኛውንም ችግር ልቅረፍ ማለት የማይታሰብ ይሆናል። 

ሙስና የሀገር ተቋርቋሪነትን፣ ስሜትን ያጠፋል።

እያየነው ያለውም ይሄው ነውና ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።”

Q. እንደ ፓርቲ የሚደርስባችሁ ጫና ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የምስረታ ጉባዔ ባደረግንበት፣ የጉባዔውን ውጤትና የምርጫ ቦርድ ኮሮጆ ጭምር ይዘን በነበረበት ሰዓት ነው እስር የተጀመረው። ክፍለ አገርም አዲስ አበባም እስሮች አሉ። 

በአባል ደረጃ አንድ የፓርቲው አባል ከ5 ወራት በላይ ያለ ክስና ዋስትና በእስር ላይ ይገኛሉ። ከአባላቶች እስራትና ተንቀሳቅሶ ከመስራት ጋር ዘተያያዘ ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው።

ፓርቲውን የሚደግፉ አባላት #ወጣቶች_እየተላኩ ማስፈራሪያ ያደርሱባቸዋል።

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ሕገ መንግስቱን ያልከተለ በመሆኑ ምስረታው እንዲታገድ፣ ኢ - ሕገ መንግስታዊ ስራዎች በሰሩ ባለስልጣናት ላይ የመሰረትነው ክስ በቀጠሮ እየተጉላላ ነው ያለው። ”

Q. ሕዝቡ በኑሮ ውድነቱ ተማሯል። ለዚህም “ መንግስት ትኩረት አልሰጠም  ” የሚሉ ወቀሳዎች ይቀርባሉ። የፓርቲዎ ግምገማ ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የኑሮ ውድነት በራሱ የሚፈጠር ነገር አይደለም። እስካሁን ከላይ የተነጋገርንባቸው ነገሮች ናቸው እየገፉ የሚያመጡት። 

አንዲት አገር #በጦርነት ላይ ሆና ሚሊዮን ዶላሮችም ለጦርነት እያወጣች ፣ አርሶአደር ማምረትና በሰላም ወጥቶ መግባት ባልቻለበት ፣ የመልካም አስተዳደር ፣ የአቅም ፣ የብቃት ጉዳዮች የመጨረሻ ውጤታቸው የኑሮ ውድነቱ ማምጣት ነው።

እነዚህን ችግሮች ማጥፋት፣ መቀነስ ካልተቻለ የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት፣ የተረጋጋ ኢኮኖሚ ማስፈን አይቻልም። ”

Q. ስለምርጫ ያላችሁ አስተያዬት ምንድን ነው ? በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ?


“ ከምርጫ ጋር በተገናኘ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራው፣ አጀንዳውም የሚያዘው ከሚደረገው #የፓርላማ እና #የክልል_ምክር_ቤቶች ጋር በተገናኘ ነው። 

ይሄ ስርዓቱን ለመቀየር የሚያስችል ብቸኛው መንገድ አይደለም። ከዚህ ይልቅ ምርጫ በየአካባቢው ማድረግ ያስፈልጋል። የአካባቢ ምርጫ የተደረገው ከ8 ዓመታት በፊት ነው።

የአካባቢ ምርጫ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።

አሁን ባለንበት ሁኔታ ላይ #ምርጫ ሊደረግ ይችላል ብሎ ማለት ትንሽ አዳጋች ነው። ”

◾️በቀጣዩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፓርቲ የሰጠው ቃል ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia