TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ማስጠንቀቂያ‼️

ልዩነትን የምታሰፉ እና ብጥብጥ በሚፈጥሩ እንቅስቃሴዎች የምትሳተፉ፦ #አክቲቪስቶች እና #የፖለቲካ_ፓርቲዎች ከድርጊታችሁ ተቆጠቡ ካልሆነ ግን የማያድግም #እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል በዶ/ር ዐብይ የሚመራው መንግስት‼️

#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ተቃዋሚውን ወደ ሀገር ስንጋብዝ ሀገራቸው ስለሆነ እና መብታቸውም ስለሆነ ነው። ውጪ ያሉትን ተቃዋሚዎች ወደ ሀገር ስንጋብዝ ለሀገር ግንባታ አሴት ስለሆኑ ነው። ከውጪ የመጡት #ተቃዋሚዎችም ሆኑ #አክቲቪስቶች በዚህ አስቸጋር ጊዜ ሀገራችንን ያሻግሯታል ብለን ነው። ነገር ግን እነዚህ ወገኖቻችን ህዝባችንን #ሊያባሉ እጃቸውን #ከሰደዱ ኪሳራ ነው። ስለዚህ ከእንደዚህ ዓይነት ተግባር እንዲቆጠቡ እንመክራለን።"

ክቡር ለማ መገርሳ የኦህዲድ ምክትል ሊቀመንበር(ጅማ)

©Dereje Gerefa Tullu
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ክቡር ፕረዝዳንት ለማ መገርሳ #ኢፍትሃዊነት እና #የአሻጥር ፖለቲካን የሚጸየፉ፣ በህዝቦች ወንድማማችነት፣ እኩልነት እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በጽኑ የሚያምኑ ይንንም በተግባር ታግለዉ #ጠንካራ ሥብዕናቸዉን በተግባር ያረጋገጡ የህዝብ ልጅ ናቸዉ፡፡" አቶ አዲሱ አረጋ
.
.
.
ሠሞኑን አንዳንድ #አክቲቪስቶች እና ፖለቲከኞች የክቡር ፕረዝዳንት ለማ መገርሳን ንግግሮች ከተነገረበት አዉድ ዉጪ እና ትርጉም ጭምር አጣምመዉ በማቅረብ ፕረዝዳንት ለማን የአሻጥር ፖለቲካ አራማጅ አስመስለዉ በማቅረብ የማጥላላት ዘመቻቸዉን ተያይዘዉታል፡፡ ለአብነትም በአንድ መድረክ ስለ ከተማ ዲሞግራፊ የተነገረዉን ንግግር በአሻጥር ፖለቲካ ተርጉመዉ እያራገቡት ይገኛሉ፡፡

በዚህ መድረክ አንዱ ተሳታፊ በኦዲፒ የእስካሁን አጠቃላይ እንቅስቃሴ የኦሮሞ ህዝብ በኢኮኖሚ ሆነ በማህበራዊ እድገቱ እምብዛም እንዳልተሻሻለ አሁንም በገጠር በሞፈር እና ቀንበር እያረሰና የከብት ጭራ እየተከተለ እየኖረ እንደሆነ፣ ኦሮሞነት በገጠር እና በኋላ ቀር ኑሮ እየተመሰለ ነዉ የሚል ጠንከር ያለ ትችት አዘል ጥያቄ ከአንድ ተሳታፊ ለክቡር ፕረዝዳንቱ ተነስቶ ነበር፡፡ ለዚህም ጥያቄ ፕረዝዳንት ለማ ማብራሪያ ሲሰጡ ይህንን ችግር እንደ ፓርቲ ለመቀየር መስራት አለብን ከሚል ቅን ሀሳብ በመነሳት ኦሮሞነት በኋላ ቀር እና በገጠሬነት ብቻ ሳይሆን የከተማ ዘመናዊ ኑሮም መገለጽ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ በዚህም ረገድ ኦዲፒ ጠንክሮ በመስራት ላይ እንደሚገኝና ከኢትዮጵያ ሶማሌ በኦሮሞነታቸዉ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን ጭምር በኦሮሚያ ከተሞች በህዝቡ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲሰፍሩና የከተማ የኑሮ ዘይቤን እንዲለማመዱ መደረጉን፤ የልማት ተነሽ አርሶ አደሮች እና የአርሶ አደር ልጆች በከተማ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታን እንዲያገኙ መደረጉን፤ በኦሮሚያ ከተሞች የኦሮሞ ህዝብ ወደ ከተማ ኑሮ እየተሰባጠረ መምጣቱን፤ ወደ ፊትም የኦሮሞ የስነ ህዝብ ስብጥር (ዲሞግራፊ) በገጠር ብቻ ተወስኖ መቅረት እንደሌለበትና ህዝባችን በከተማም መኖር እንዳለበት ለዚህም ኦዲፒ ጠንክሮ እንደሚሰራ አጥብቀዉ ምላሽ ሠጥተዋል፡፡

የሚገርመዉ ጉዳይ ኦሮሞ ህዝብ አኗኗር በኋላ ቀር የገጠር ኑሮ ብቻ መታወቅ የለበትም፣ ህዝባችን ኑሮዉ መሻሻል አለበት ገጠርም ከተማም መኖር አለበት የሚል ሃሳብ እንዴት የአሻጥር ፖለቲካ ሊሆን ይችላል? የኦሮሞን ህዝብ ኑሮ ለማሻሻል እና ወደ ከተሜነት ማዘመን የክልሉ መንግስት ግዴታ ነዉ፡፡ ለዚህ ደግሞ የክልሉ መንግስት የማንም ፈቃድ እና ቡራኬ አያሻዉም፡፡

ክቡር ፕረዝዳንት ለማ መገርሳ ኢፍትሃዊነት እና የአሻጥር ፖለቲካን የሚጸየፉ፣ በህዝቦች ወንድማማችነት ፣እኩልነት እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በጽኑ የሚያምኑ ይንንም በተግባር ታግለዉ ጠንካራ ሥብዕናቸዉን በተግባር ያረጋገጡ የህዝብ ልጅ ናቸዉ፡፡ አምርረዉ የሚጠሉትንና ሲታገሉት የነበረዉን የሴራ እና የአሻጥር ፖለቲካ በማራማድ የኦሮሞን ህዝብም ሆነ በግላቸዉ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት የሚያስብ ስብዕና ፈጽሞ የላቸዉም፡፡

ነገር ግን ፕረዝዳንት ለማ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ፕረዝዳንት እንደመሆናቸዉ የኦሮሞን ህዝብ ኑሮ ለመለወጥ መስራት ግዴታቸዉ እንደሆነም መዘንጋት የለበትም፡፡ ስለሆነም ፕረዝዳንቱ የኦሮሞን ህዝብ የልማት እና የለዉጥ አጀንዳዎች ባነሱ ቁጥር በአሻጥር ለመክሰስ መሯሯጥ ኢ-አመክኖአዊ እና ተቀባይነት የሌለዉ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡

#AddisuArega

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ክልል መንግስት #አክቲቪስቶችን አሳሰበ።

የአማራ ክልል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ግዛቸው ሙሉነህ በሰጡት መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የህወሓት ቡድን በኃይል በወረራቸው አካባቢዎች ላይ በተሰወሰደው ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ የሆኑ ጀብዱዎች ተፈፅመዋል ሲሉ ገልፀዋል።

ወታደራዊ እርምጃ ከተወሰደባቸው ቦታዎች መካከል ፦
- ወልድያና አካባቢው፣
- ጋይትና አካባቢው፣
- ዛሬማና አካባቢው፣
- ሰቆጣና አካባቢው፣
- ጋሸናና አካባቢው ይገኙበታል። በእነዚህ ቦታዎች ላይ በተወሰደው ወታደራዊ እርምጃ ህወሓት ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበታል ብለዋል።

ይህ ሆኖ ሳለ ግን የማህበረሰብ አንቂዎች (#አክቲቪስቶች) በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማህበራዊ ትስስር ገፆች (የማህበራዊ ሚዲያዎች) ላይ ሽብረተኛ ተብሎ የተፈረጀውን ህወሓት ለመደምሰስ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲታቀቡ አሳስበዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia