TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአማራ ክልል መንግስት #አክቲቪስቶችን አሳሰበ።

የአማራ ክልል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ግዛቸው ሙሉነህ በሰጡት መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የህወሓት ቡድን በኃይል በወረራቸው አካባቢዎች ላይ በተሰወሰደው ወታደራዊ እርምጃ ታላላቅ የሆኑ ጀብዱዎች ተፈፅመዋል ሲሉ ገልፀዋል።

ወታደራዊ እርምጃ ከተወሰደባቸው ቦታዎች መካከል ፦
- ወልድያና አካባቢው፣
- ጋይትና አካባቢው፣
- ዛሬማና አካባቢው፣
- ሰቆጣና አካባቢው፣
- ጋሸናና አካባቢው ይገኙበታል። በእነዚህ ቦታዎች ላይ በተወሰደው ወታደራዊ እርምጃ ህወሓት ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበታል ብለዋል።

ይህ ሆኖ ሳለ ግን የማህበረሰብ አንቂዎች (#አክቲቪስቶች) በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማህበራዊ ትስስር ገፆች (የማህበራዊ ሚዲያዎች) ላይ ሽብረተኛ ተብሎ የተፈረጀውን ህወሓት ለመደምሰስ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲታቀቡ አሳስበዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia