TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢትዮጵያ ብቻዋን ነፃ አትሆንም!

(ዶክተር - TMES)

ከሰሞኑን በኢትዮጵያ ሪፖርት እየተደረጉ ያሉት ኬዞች ማነስ በርካቶችን እያዘናጋ እንደሆነ እየታየ ነው።

መልካም ዜናን የሚጠላ የለም ግን እውነታው ይህ አሁን ድረስ ፈውስ ያልተገኘለት በሽታ በመላው ዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ መሆኑ ነው።

ዶክተር ፅዮን ፍሬው ከኒው ዮርክ እንዳሉት በየቀኑ የሚመዘገበው ቁጥር 0 እና 1 ሆነ ማለት የኮሮና ቫይረስ እየጠፋ ነው ማለት አይደለም።

የፋሲካ ሰሞን በሀገራችን የነበረው መዘናጋትና ቸልተኝነት እየባሰበት እንጂ እየቀነሰ አልመጣም። ይህ ደግሞ ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍለናል።

ሁላችንም በየእምነታችን ይህ በሽታ ከዓለም እንዲጠፋ፤ ፈጣሪም ለዚህ ወረርሽኝ መፍትሄ ለማምጣት የሚሰሩትን ሳይንቲስቶን መንገዱን ያሳያቸው ዘንድ እየተማፀንን በከፍተኛ ደረጃ ጥንቀቄያችን እናጠንክር።

ኢትዮጵያ ብቻዋን በፍፁም ነፃ አትሆንም ፤ ጎረቤት ሀገራት በወረርሽኙ እየታመሱ እኛ ጤና ሆነን እንኖራለን ማለት አይቻልም ፤ አይደለም ጎረቤት ሀገራት የቻይና፣ አሜሪካ፣ ኢራን፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ጣልያን ...ሌሎችም ሀገራት ህዝቦች ጤና መሆን ካልቻሉ ህይወታችን እንደተቃወሰ ይቀጥላል፤ ምክንያቱም ተሳስረናልና!

ዘወትር ለኢትዮጵያ #ብቻ ሳይሆን ለዓለም ጤና መሆን፣ ለሰው ልጅ መዳን፣ ለሰው ልጅ ሰላም መሆን በየእምነታችን ፈጣሪን እንለምን።

እኛ የጤና ባለሞያዎች ደከመን ሰለቸን ሳንል ይኸው ህይወታችን ሰጥተን እያገለገልን ነው፤ እናንተም በመዘናጋት የሚመጣውን የከፋ ቀውስ ለመከላከል አብራችሁን ቁሙ!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ATTENTION

በአዲስ አበባ የኮቪድ-19 ስርጭት በእጅጉ #እየጨመረ ነው። ከሚያዚያ 29 እስከ ዛሬ ግንቦት 11 ባሉት ቀናት #ብቻ አንድ መቶ ሃያ (120) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

• ሚያዚያ 29/2012 ዓ/ም - ሃያ አንድ (21) ሰዎች
• ሚያዚያ 30/2012 ዓ/ም - ሶስት (3) ሰዎች
• ግንቦት 1/2012 ዓ/ም - አስራ ሶስት (13) ሰዎች
• ግንቦት 2/2012 ዓ/ም - ሃያ አንድ (21) ሰዎች
• ግንቦት 3/2012 ዓ/ም - አምስት (5) ሰዎች
• ግንቦት 6/2012 ዓ/ም - አምስት (5) ሰዎች
• ግንቦት 7/2012 ዓ/ም - ስምንት (8) ሰዎች
• ግንቦት 8/2012 ዓ/ም - ሁለት (2) ሰዎች
• ግንቦት 9/2012 ዓ/ም - አራት (4) ሰዎች
• ግንቦት 10/2012 ዓ/ም - ሃያ ዘጠኝ (29) ሰዎች
• ግንቦት 11/2012 ዓ/ም - ዘጠኝ (9) ሰዎች

አሁንም ስርጭቱ ከዚህ በላይ እንዳይባባስ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ በድጋሚ መልዕክት ለማስተላለፍ እንወዳለን። የጤና ባለሞያዎችን ምክር የማናዳምጥ ከሆነ፣ የሚወጡትን መመሪያዎች የማናከብር ከሆነ ይህ ወረርሽኝ 'ከቁጥጥር ውጭ' ሊወጣ ይችላል።

መዘናጋትና ቸልተኝነት ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍላል!

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮቪድ-19 ስርጭት በአዲስ አበባ!

በአዲስ አበባ ከተማ በአራት (4) ተከታታይ ቀናት #ብቻ ሰባ ስምንት (78) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

• ግንቦት 12/2012 ዓ/ም - ዘጠኝ (9) ሰዎች
• ግንቦት 13/2012 ዓ/ም - ሶስት (3) ሰዎች
• ግንቦት 14/2012 ዓ/ም - አስራ ስምንት (18) ሰዎች
• ግንቦት 15/2012 ዓ/ም - አርባ ስምንት (48) ሰዎች

አብዛኞቹ በቫይረሱ መያዘቸው የተረጋገጠ ሰዎች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ #የሌላቸው ናቸው።

መዘናጋት ዋጋ ያስከፍላል፤ ጥንቃቄ ይደረግ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮቪድ-19 ስርጭት በአዲስ አበባ!

በአዲስ አበባ ከተማ በአምስት (5) ተከታታይ ቀናት #ብቻ አንድ መቶ ሃምሳ አንድ (151) ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

• ግንቦት 12/2012 ዓ/ም - ዘጠኝ (9) ሰዎች
• ግንቦት 13/2012 ዓ/ም - ሶስት (3) ሰዎች
• ግንቦት 14/2012 ዓ/ም - አስራ ስምንት (18) ሰዎች
• ግንቦት 15/2012 ዓ/ም - አርባ ስምንት (48) ሰዎች
• ግንቦት 16/2012 ዓ/ም - ሰባ ሶስት (73) ሰዎች

አብዛኞቹ በቫይረሱ መያዘቸው የተረጋገጠ ሰዎች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር 'ንክኪ የሌላቸው' ናቸው።

ይህ ከፍተኛ የሆነ ኮቪድ-19 ስርጭት በአዲስ አበባ ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም። የክልል ከተሞች ነዋሪዎች የቫይረሱ ስርጭት እየጨመረ በመምጣቱና የትራንስፖርት እንቅስቃሴም #ባለመቋረጡ እጅግ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርጉ።

አስገዳጅ ካልሆነ ከቤት አትውጡ!

ከቤት ምትወጡበት አስገዳጅ ምክንያት ካለ ደግሞ ሰዎች ሚሰባሰበሰቡበት ቦታ በፍፁም አትገኙ ፣ ከሰዎች ጋር አትጨባበጡ ፣ በስራ ቦታችሁ ሳትዘናጉ ጥንቃቄ አድርጉ ፣ የእጃችሁን ንፅህና ጠብቁ ፣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ያድርጉ!

መዘናጋት ዋጋ ያስከፍላል፤ ጥንቃቄ ይደረግ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የተጠነቀቀ ይህን የከፋ ጊዜ ይሻገራል!

ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የሩቅ ሀገር በሽታ ነው ሲባል እንዳልነበር ዓለምን አዳርሶ ዛሬ ሀገራችንን እያመሰ ነው።

በአዲስ አበባ አሁንም መደበኛ ህይወት የሚመራባቸው አካባቢዎች እንዳሉ ተመልክተናል። ይህ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍል ነው።

በአ/አ የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ቢገኝም አሁንም ከክልሎች ጋር 'የህዝብ ትራንስፖርት' አልቆመም ይህ ሁኔታ መላው የሀገሪቱን ህዝብ አደጋ ላይ እየጣለ ነው።

የክልል ከተሞች ላይ የሚታየው መዘንጋት ደግሞ ችግሩን የከፋ ሊያደርገው ይችላል። ጊዜው ሳይረፍድ መፍትሄ ቢፈልግ መልካም ነው።

የክልል ነዋሪዎች ጋር ቫይረሱ በስፋት ያለው አዲስ አበባ #ብቻ ነው እኛ ጋር አይደርስም በሚል የተሳሳተ አመለካከት ካለ አሁን መታረም አለበት።

የውጭ ሀገር ነው ሲባል የነበረው በሽታ ዛሬ ሀገራችን ፣ ሰፈራችን ደርሷል፤ #ካልተጠነቀቅን የእያንዳንዳችንን ቤት ማንኳኳቱ አይቀርም።

የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መከላከያ መንገዶች እጅግ በጣም ቀላል ሆነው ሳለ ለምን የማይገባ ዋጋ እንከፍላለን ?

• የእጆቻችንን ንፅህና እንጠብቅ! /መታጠብ/

• ቤት ውስጥ እንቀመጥ! /መቀመጥ/

• የስራችን ሁኔታ ከቤት የሚያስወጣና አስገዳጅ ጉዳዮች ኖረውን ከቤት ከወጣን የአፍንጫና አፍ መሸፈኛ እናድርግ! /መሸፈን/

• በሁሉም ቦታ አካላዊ ርቀት እንጠብቅ! /መራራቅ/

የኢትዮጵያ መንግስት የቫይረሱን ከፍተኛ ስርጭት ከግምት ውስጥ ሊያስገባና በህዝብ ትራስፖርቶች ላይ ያለውን ሁኔት ሳይውል ሳያድር መፍትሄ ሊፈልግለት ይገባል። ካልሆነ በሀገር ደረጃ የሚከፈለው ዋጋ ከፍተኛ ነው!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከፍተኛ ጥንቃቄ!

#SHARE #ሼር

በኢትዮጵያ የምትኖሩ የቲክቫህ አባላት ፣ ይህን መልዕክት የኢንተርኔት አገልግሎት አግኝታችሁ ማንበብ የቻላችሁ በሙሉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በከፍተኛ ደረጃ በሀገሪቱ እየተሰራጨ በመሆኑ ጥንቃቄ አድርጉ።

ኢትዮጵያ የመመርመር አቅሟን እያሣደገች መጥቱን ተከትሎ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።

በሀገሪቱ በሁለት ቀናት #ብቻ (ሀምሌ 9/2012 እና ሀምሌ 10/2012) 672 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በምርመራ ተረጋግጧል።

በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥርም እየጨመረ መጥቷል በትላንት እንዲሁም በዛሬ ሪፖርት መሰረት 15 ሰዎች ከቫይረሱ ጋር በተገናኘ ህይወታቸውን አጥተዋል።

ይህንን መልዕክት በስልካችሁ ያገኛቹ ወገኖቻችን እራሳችሁ እና ቤተሰባችሁን በሙሉ ከዚህ አስፈሪ ወረርሽኝ ሳትዘናጉ እንድትጠብቁ ጥሪ እናቀርባለን ፤ ኢንተርኔት ማግኘት ላልቻሉ ወዳጆቻችሁ በSMSና በመደወል አሳሳቢውን ሁኔታ አሳውቋቸው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የ12ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተፈታኞችን በሚመለከት ፦

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሐረጓ ማሞ ከ12ኛ እና ከ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር በተያያዘ ተከታዩን ብለውናል ፦

- የ12ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲሰጥ በቅድሚያ ትምህርት ቤቶች ኮቪድ-19 መከላከልን መርህ ባደረገ መልኩ ዝግጅት ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል።

- ከፈተናው አስቀድሞ የትምህርት ቤቶችን ዝግጁነት የማረጋገጥ ስራ በትምህርት ሚኒስቴር ይሰራል።

- ይህ ተግባራዊ እንዲሆን ሁሉም ትምህርት ቤቶች ፣ የጤና ተቋማት፣ ወላጆች፣ አጠቃላይ ማህበረሰቡ ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

- የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የ11ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀቁ እና የ12ኛ ክፍልን የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ መሆን አለባቸው።

- የ8ኛ ክፍል ተፈታኛ ተማሪዎች የ7ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቁ እና የ8ኛ ክፍልን የአንደኛ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

- ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው በሙሉ አቅም እንዲመለሱ የስነ ልቦና ድጋፍ ይደረግላቸዋል።

- የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እና ምዝገባ በኦንላይን ይካሄዳል። ተማሪዎች የ45 ቀን የክለሳ እና የቴክኖሎጂ መለማመጃ ጊዜም ይኖራቸዋል።

- በነገራችን ላይ ትምህርት ቤቶች የሚከፈቱት ፣ ፈተናዎችም የሚሰጡት ትምህርት ቤቶች አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ማሟላት ሲችሉ #ብቻ ነው።

- ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶች እንዲከፈቱ ያስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ሳይሸራረፉ እንዲተገበሩ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጠው ትምህርት ለማስቀጠል እንዲሁም ተመራቂ ተማሪዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ የቀራቸውን ትምህርት ተከታትለው እንዲመረቁ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲዎች ጥሪ ማድረግ ጀምረዋል።

ዛሬ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ዓ.ም ተመራቂ መደበኛ ተማሪዎች #ብቻ የምዝገባ (Registration) ጊዜ አሳውቋል።

በዚህም ተመራቂ ተማሪዎች ብቻ ጥቅምት 23 እና 24/2013 ዓ/ም እንዲመዘገቡ ጥሪ የቀረበ ሲሆን የመጀመሪያ ቀን ትምህርት (Day - One - Class - One) ጥቅምት 25 / 2013 ዓ/ም እንደሚጀምር ተገልጿል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TikvahFamily

ከ1 ወር በላይ ተቋርጦ የቆየው የቲክቫህ ማስታወቂያ ከነገ ጀምሮ ይቀጥላል።

ህጋዊ የንግድ ፍቃድ አውጥታችሁ የምትንቀሳቀሱ የቲክቫህ አባላት የድርጅት ባለቤቶች ፓኬጁን : @Tikvahpromo / +251942293508 #ብቻ ማግኘት ትችላላችሁ።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
* ATTENTION

ከዛሬ ነሃሴ 15/2013 ጀምሮ በሰ/ሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ የሰዓት እላፊ ገደብ ተጥሎ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል።

የሰአት እላፊ ገደቡን የወሰነው የወረዳዉ ፀጥታ ምክር ቤት ነው።

የሚዳ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አሁን ያለዉ የሃገሪቱ የሰላም ሁኔታ ከወረዳዉ መልክአ ምድር አቀማመጥ ጋር ሲነፃፀር አሳሳቢ ሆኖ በመገኘቱ የወረዳዉ ፀጥታ መዋቅር ዉይይት አካሄዶ ለፀጥታ ስጋት ነዉ በማለት የዉሳኔ አቅጣጫ አስቀምጧል ብሏል።

በዚህ መሰረትም ከዛሬ ነሃሴ 15/2013 ዓ.ም ጀምሮ ፦

1ኛ. መጠጥ ቤቶች ከንጋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 2 ሰአት ድረስ #ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል።

2ኛ. የግል አሽከርካሪዎች ሞተር ሳይክልን ጨምሮ ከምሽቱ 1 ሰአት በኋላ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ውሳኔ ተላልፏል።

3ኛ. ማንኛዉም የመንግስት ተሸከርካሪ ለስራ የወጡ ካልሆነ በስተቀር ከሁለት ሰአት በኋላ የትም ቦታ ከመንግስት ተቋም ዉጪ መቆም የለባቸውም ፤
- የጤና ባለሙያዎች፣
- የሃይማኖት አባቶች
- ለፀጥታ ስራ ከሚንቀሳቀሱ ሰዎች በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰአት በኋላ እንቅስቃሴ የተገደበ ነው።

ህብረተሰቡ ማንኛውም አይነት #የተለየ_ነገር ከተመለከተ ጥቆማ ለመስጠት እነዚህን ስልክ ቁጥሮች ፦
• 096602287 ፣
• 0913146121
• 0901064105 መጠቀም ይችላል።

@tikvahethiopia
#SPHMMC

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የ75 ዓመት ክብረ በዓል እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8 ) ቀንን ምክንያት በማድረግ የካቲት 29 ቀን ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት የሚሰጠው በሴቶች የቀዶ ሕክምና ቡድን አባላት #ብቻ እንደሚሆን አሳውቆናል።

ኮሌጁ በላከል መልዕክት ፤ በተለያዩ የሕክምና ዘርፍ የሰለጠኑ እና ልምድ ያላቸው ቀዶ ሐኪሞቹ በልዩ ልዩ የባለሙያዎች ቡድናቸው ታግዘው አገልግሎት ይሰጣሉ ብሏል።

ይህም የኮሌጁን ሴት ባለሙያዎች የላቀ አገልግሎት እንደሚሰጡ ይህ ጥሩ ማሳያ እንደሆነም አሳውቆናል።

@tikvahethiopia
#ዋጋ

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ያለአገልግሎት የተከማቹ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ በስክራፕ መልክ የሚወገዱ ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎችን መሸጫ የዋጋ ዝርዝር ይፋ ሆኗል።

1ኛ. ስቲል - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር)  64.00

2. ካስት አይረን  - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር) 51.75

3. አልሙኒየም - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (ብር) 120.00

4. ስክራፕ ያደረገ ተሽከርካሪ / ማሽነሪ - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር) 51.25

5. ያገለገለ የተሽከርካሪ / ማሽነሪ መለዋወጫ - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ  (በብር) 51.25

በዚህ መሰረት መሰሪያ ቤቶች ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን የማዕድን ሚኒስቴር ለሚመድብላቸው የብረታ ብረት አቅላጭ ኢንዱስትሪ/ለአምራች ኢንዱስትሪ #ብቻ በቀጥታ እንዲሸጡ ከሽያጭም የሚገኘውን ገንዘብ ወደ መንግስት ማዕከላዊ ግ/ቤት የባንክ አካውንት ገቢ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

(ለተጨማሪ መረጃ ከላይ የተያያዙትን ደብዳቤዎች ይመልከቱ)

Credit : M. (Tikvah Family)

@tikvahethiopia
#DrAbrhamBelay

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ፤ በትግራይ ያጋጠመውን ቀውስ አይነተኛ የመፍቻ መንገድ፣ " ህዝቡ በተደራጀ አዲስ የሀሳብ ጥላ የመፍትሔው ባለቤት እና አካል ለመሆን ሲወስን #ብቻ የሚረጋገጥ ነው " አሉ።

የመከላከያው ሚኒስትር ይህንን ያሉት ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰራጩት ፅሁፍ ነው።

" ጊዜው ያለፈበት የፖለቲካ ኃይልም ሆነ አስተሳስብ፣ ከትግራይ ህዝብ ኑባሬ ደህንነት፣ ሰላምና መረጋጋት ከቶ ሊበልጥ አይገባም " ያሉት ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ ፤ " በመላው ትግራይ እና የተለያዩ አከባቢዎች የምትገኙ የትግራይ ተወላጆች የመፍትሔ ሀሳቦች እንዲንሸራሸሩ ፣ የተደራጀ #አስቸኳይ ህዝባዊ ስክነትና ምክክር እንዲሰፍን እንድንዘጋጅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር  ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን መቼ ለመስጠት እቅድ ይዟል ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰውና በትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች የተሰራጨ አንድ ደብዳቤ የዚህ ዓመት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ሊሰጡ #የታቀደበትን ጊዜ ያመለክታል።

የደብዳቤውን ትክክለኝነት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከታቸው የትምህርት ሚኒስቴር አካላት #ማረጋገጥ ችሏል።

በዚህ መሰረት ፦

1ኛ. በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት #በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ኘሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀውን ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደትም እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስመቅጧል።

2ኛ. በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማእከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 /2015 እስከ ሐምሌ 13 /2015 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል።

3ኛ. የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

በተጨማሪም እንደ አገር ዓመታዊ የትምህርት ካላንደር ከ2016 ጀምሮ ለማስተካከል ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻቸውን በዚሁ ማዕቀፍ አንዲያስተካክሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል።

ከሀገር አቀፍ ፈተናዎች ጋር በተያያዘ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ የተለያዩ #ያልተረጋገጡ መረጃዎችን እየሰሙ አለመረጋጋት ውስጥ መግባታቸውን ሲገልፁልን ነበር ፤ በቀጣይም ትምህርት ሚኒስቴር / የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የሚሰጡትን ትክክለኛ መረጃ #ብቻ እንድትከታተሉ ፤ በቀረው አጭር ጊዜም ዝግጅታችሁን ታጠናክሩ ዘንድ መልዕክት እናስተላልፋለን።

(ከላይ የተያያዘው ደብዳቤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከተው አካል #ትክክለኝነቱን ያረጋገጠው ነው።)

@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#MoE

አገር አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡባቸው እና የምረቃ ቀናት እንዲሁም የሬሜዲያ ፈተና ወጤት አያያዝ ላይ ቅያሪ ተደርጓል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ግንቦት 9 ቀን 2015 ዓ/ም ያስተላለፈውን ሴርኩላር በተመለከተ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ት/ቢሮ አመራሮች ጋር በድጋሚ ግንቦት 22 ቀን 2015 በበይነ-መረብ ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ መሰረትም ፦

- ፈተናዎች የሚሰጡባቸው ቀናት፣

- የተማሪዎች ምረቃ በዓል፣

- የሪሜዲያል ፈተና ውጤት አያያዝ በተመለከተ ቅያሪ መደረጉን ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ የተላከውን ደብዳቤ #ትክክለኝነት ከሚመለከታቸው አካላት አረጋግጧል።

በዚህም ፦

- በ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 30 ከመቶ፣ #በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 70 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

- በ2015 ዓ/ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማእከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ 8 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ ውጤት ሐምሌ 10 ቀን የሚገልጽ ይሆናል ተብሏል።

- የተማሪዎችን ምረቃ በተመለከተ ከሐምሌ 11 እስከ ሐምሌ 16 ቀን ባሉት ቀናት ውስጥ ማካሄድ የሚቻል መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር የገለፀ ሲሆን በመርሃ-ግብሩ ላይ የሚሳተፉት የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች #ብቻ ናቸው ብሏል።

- የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 16 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከተው የትምህርት ሚኒስቴር አካል ትክክለኝነቱን ያረጋገጠው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ዋቸሞ_ዩኒቨርሲቲ

ከመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ የነበረንን ጥያቄ ለማቅረብ በወጣንበት " የኃይል እርምጃ ተወስዶብናል " ሲሉ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቅሬታ አቀረቡ።

ተማሪዎቹ ጥያቄ የነበረው ከመውጫ ፈተና በኃላ ለሚካሄደው ምርቃት " ምርቃቱ ላይ ለመገኘት የወደቀ ያለፈ መባል የለበትም ፤ አንድ ላይ መመረቅ አለብን ፤ ለ16 አመት ያክል የለፋንበት ፣ ቤተሰብም ብዙ የደከመበት ነው ይሄ ጉዳይ መልስ ያሻዋል " በሚል መሆኑን ገልጸዋል።

" ይህን ጥያቄያችንን ድንጋይ፣ ዱላ ሳንይዝ ምላሻ እንዲሰጠን ለመጠየቅ ሰልፍ ብናደርም የፀጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመጠቀም፣ ከፍተኛ ድብደባ በመፈፀም፣ የወንድ እና የሴቶች ዶርም ድረስ በመዝለቅ ጉዳዩን የማያውቁ ተማሪዎችን ጭምር በመደብደባ እና በማዋከብ ጥያቄያችንን ለማፈን ሞክረዋል " ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ተማሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኳቸው የቪድዮ ማስረጃዎች የፀጥታ ኃይሎች ተማሪዎችን በደቦ ሰደበድቡ ፣ ወደ ሴቶች ዶርም ዘልቀው ገብተው ተማሪዎችን በኃይል ሲያስወጡ ያሳያል።

ዩኒቨርሲቲው እስካሁን ስለጉዳዩ ያለው ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተቋሙ ሰራተኞች በኩል ሃስብ ለመቀበል ጥረት አድርጓል። አንድ በሳምንት መጨረሻ ቀናት ለማስተማር በተቋሙ የተገኙ መምህር ጉዳዩን ውስጥ ሆነው ሲከታተሉ እንደነበር ገልጸዋል።

የፀጥታ ኃይሎች ወደ እርምጃ የገቡት ተማሪዎቹ የግቢ ውስጥ እየጮሁ የመማር ማስተማር ስራውን ሲያውኩ፣ መንገድ በድንጋይ ሲዘጉ፣ ንብረት ላይ ጉዳት ለማድረስ እንዲሁም በፀጥታ ኃይሎች ላይ ትንኮሳ ለመፈፀም በሞከሩበት ወቅት መሆኑን አመልክተዋል።

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጩ ቪድዮዎች የነበረውን አጠቃላይ ሁኔታ የሚያሳይ አይደለም የሚሉት መምህሩ ግቢውን ለመረበሽ የሞከሩ ተማሪዎች እንዲሁም በተማሪዎች ላይ ከልክ ያለፈ እርምጃ የወሰዱ የፀጥታ ኃይሎችን እኩል ማውገዝ ይገባል ብለዋል።

" ተማሪዎቹን ንጹሕ፤ የጸጥታ ሀይሉን በመወንጀል የሚሰራ ዜና ሚዛናዊነት የሚጎድለው ሁኔታውን የማያስረዳ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ሌላ አንድ የግቢው ሰራተኛ የፀጥታ ኃይሎች ወደ እርምጃ የገቡት የግቢው የመማር ማስተማር ስራ ሲታወክ እና ግቢው ሲረበሽ ነው ብለው የተወሰደው እርምጃ ግን ልክ ያለፈ መሆኑን ገልጸዋል።

መልዕክታቸውን የላኩ ተማሪዎቹ ግን በግቢው ሰራተኞች በኩል የተሰጠው ሃሳብ የማይቀበሉት ሲሆን አጠቃላይ የነበረው ሁኔታ ሰላማዊ እንደነበር፤ ተማሪዎች ግቢ ለመረበሽ ያደረጉት ሙከራ እንደሌለ፣ የፀጥታ ኃይሎች እርምጃ መውሰድ በጀመሩበት ወቅት ግን መንገድ ለመዝጋት መሞከሩን አመልክተዋል።

አንድ የግቢው ተማሪ፤ " በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ከማቅረብ በዘለለ ድንጋይ በፀጥታ ኃይሎች ላይ ለመወርወር የሞከረ  ፤ ዓመታትን በተማረበት ተቋም ጥፋት ለማድረስ የሞከር ተማሪ አልነበረም ብሏል።

" በእርግጥ መንገድ ዘግተዋል መንገድ የዘጉበት ምክንያት ፖሊስ ተማሪን መምታት ሲጀመር ነው " ሲል ገልጿል።

በርካታ ተማሪዎች የፀጥታ ኃይሎች እርምጃ መውሰዳቸው፤ ተቋሙ ለሰለማዊ ጥያቄ ከውይይት ይልቅ ኃያልን አማራጭ ማድረጉን የሚገልፅ መሆኑን እና በተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች መጎዳታቸውን፣ ንብረትም መዘረፉን አመልክተዋል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠንን ምላሽ ተከታትለን እናሳውቃለን።

ትምህርት ሚኒስቴር፤ የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ 8 ባሉት ቀናት እንደሚሰጥ የተማሪዎችን ምረቃ ከሐምሌ 11 እስከ ሐምሌ 16 ቀን ባሉት ቀናት እንደሚካሄድ በመርሃግብሩ ላይ የሚሳተፉት የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች #ብቻ መሆናቸውን ማሳወቁ ይታወሳል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-11

@tikvahethiopia
#ExitExam

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ " የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ ይረዳኛል ፤ ትውልድ እና ሀገርንም ከውድቀት ይታደጋል " በሚል ዘንድሮ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መስጠት ይጀምራል።

ለዚህ ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 8 ለሁሉም የመንግስት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች በኦንላይን ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና 180 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ፈተናው ላይ ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ተቋማት ለፈተናው ተማሪዎቻቸውን ዝግጁ እያደረጉ ይገኛሉ።

ከዚህ የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ ፈተናውን የማለፍ የማይችሉ ተማሪዎች ፈተናውን ደጋግመው እንዲወስዱ ዕድል ያላቸው ሲሆን በተማሪዎች ምረቃ ላይ ግን የሚሳተፉት የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች #ብቻ ናቸው።

ይህን የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ ሁሉም ተቋማት ለማስፈፀም እየሰሩ ይገኛሉ።

ለአብነት ፤ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ " የመውጫውን ፈተና ያለፉ ብቻ " የመመረቂያ ጋዎን እንዲሰጣቸው ክትትል እንዲደረግ አሳስቧል።

የተቋሙ የሬጅስትራር እና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ/ም የመውጫ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎችን በሚመለከት ለሁሉም የተቋሙ አካዳሚክ ክፍል ሬጅስትራሮች በፃፈው ደብዳቤ የትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው " የመውጫ ፈተና አፈፃፀም መመሪያ " መሰረት ፤ ኮርስ አጠናቀው ያልተመዘገቡ እንዲሁም ያልተመዘገቡትና ያልፋቁት " F " ያላቸው ተማሪዎች በስህተት ለመውጫ ፈተና ዝርዝራቸው የተላኩ ካሉ የመውጫ ፈተናውን እንደማይፈተኑ ከወዲሁ እንዲነገራቸውና የመውጫ ፈተና ኮርስም እንዳይመዘገቡ አዟል።

የመውጫ ፈተና " መመዝገብ የሚችሉት " ብቻ ኮርሱን እንዲመዘገቡና የምዝገባ ስሊፕ ለመውጫ ፈተና መግቢያ እንዲያገለግላቸው ከወዲሁ ለተማሪዎች እንዲሰጣቸውም ብሏል።

ከዚህ ባለፈ ዳይሬክቶሬቱ ፤ ለምረቃ መሟላት ከሚገባቸው መመዘኛዎች በተጨማሪ የመውጫ ፈተና ያለፉ (50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡ) ብቻ ለምረቃ እንዲቀርቡ ፤ የምረቃ መስፈርቱን ያሟሉና የመውጫ ፈተና ያለፉ ብቻ የመመረቂያ ጋዎን እንዲሰጣቸው ክትትል እንዲደረግ ዳይሬክቶሬቱ አሳስቧል።

እንደ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዘንድሮ የተማሪዎችን ምረቃ ከሐምሌ 11 እስከ ሐምሌ 16 ቀን ባሉት ቀናት ውስጥ ማካሄድ ይችላሉ።

More : @tikvahUniversity