TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሀሰተኛ_መረጃ:ኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ ከኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግ ራሱን #አገለለ ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰት ነው። ክለቡ እስካሁን ራሴን ከሊጉ #አላገለልኩም ብሏል።

Via #ቴዎድሮስ_ታከለ/ሶከር ኢትዮጵያ/
@tikvahethsport
#FakeNews የአማራ ክልል ልዩ ኃይል #ሊፈርስ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ/በተለይም በfacebook/ የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰት ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNews ሌተናል ጄነራል #ሃሰን_ኢብራሂም ታሰሩ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #ሀሰት ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በማዕድን ዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች ሥራቸውን በተለያየ ምክንያት አቋርጠው ወጥተዋል እየተባለ ያለው #ሀሰት መሆኑን የማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
🏷የ12ኛ ክፍል የፈተና #ዉጤት አስመልክቶ በተለያዩ ማህበረዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ መረጃዎች #ሀሰት መሆናቸውን የፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ የ12ኛ ክፍል ዉጤት #በቅርቡ ይለቃቃል የሚለዉ መረጃ መሰረተ ቢስ ነዉ ብሏል። የኤጀንሲዉ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ረዲ ሺፋ ለኢትዮኤፍኤም እንዳረጋገጡት ኤጀንሲዉ የፈተናዎቹ ዉጤት ይፋ የሚሆንበትን ቀን አልወሰነም ብለዋል፡፡

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ዉጤቱ ተለቋል በዚህ ቀን ይለቀቃልና ሌሎች መሰል መረጃዎች ሀሰት እንደሆኑ አቶ ረዲ ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎቹም ሆነ ህብረተሰቡ ከተሳሳተ መረጃ እራሱን እንዲጠብቅ ሃላፊዉ ጠይቀዋል፡፡ በቀጣይ ኤጀንሲዉ የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል የፈተና ዉጤት ይፋ የሚሆንበትን ቀን ለመገናኛ ብዙሃን በይፋ ያሳውቃል ብለዋል፡፡

Via #ኢትዮኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeBot

"የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብር ልናንበሸብሽዎት በ ቴሌግራም መጥተናል። ይህ bot ቁጭ ብለው ገንዘብ የሚያፍሱበት ነው። በዚህ ቦት 1 ሰዉ ሲጋብዙ 1 ብር ያገኛሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉን።"

#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ ስምን እየተጠቀሙ የሚሰራጩ የተሳሳቱ መልዕክቶችን በርካታ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ሲቀባበሉት ተመልክተናል ይህ ፍፁም #ሀሰት ነው። መልዕክቱም የሚሰራጨው በሀሰተኛ ገፅ ነው!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeBot

"የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብር ልናንበሸብሽዎት በ ቴሌግራም መጥተናል። ይህ bot ቁጭ ብለው ገንዘብ የሚያፍሱበት ነው። በዚህ ቦት 1 ሰዉ ሲጋብዙ 1 ብር ያገኛሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉን።"

#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ ስምን እየተጠቀሙ የሚሰራጩ የተሳሳቱ መልዕክቶችን በርካታ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ሲቀባበሉት ተመልክተናል ይህ ፍፁም #ሀሰት ነው። መልዕክቱም የሚሰራጨው በሀሰተኛ ገፅ ነው!!

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeBot በኢትዮ ቴሌኮም ስም!

ትላንት በንግድ ባንክ ስም ዛሬ ደግሞ በኢትዮ ቴሌኮም ስም #ሀሰተኛ መልዕክቶች ሲሰራጩ እየተመለከትን ነው።

"Ethio Telecom ካርድ ልናንበሸብሽዎት በ ቴሌግራም መጥተናል። ይህ bot ቁጭ ብለው ገንዘብ የሚያፍሱበት ነው። በዚህ ቦት 1 ሰዉ ሲጋብዙ 1 ብር ያገኛሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉን።"

#የኢትዮቴሌኮምን ስምን እየተጠቀሙ የሚሰራጩ የተሳሳቱ መልዕክቶችን በርካታ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ሲቀባበሉት ተመልክተናል ይህ ፍፁም #ሀሰት ነው። መልዕክቱም የሚሰራጨው በሀሰተኛ ገፅ ነው!!

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዶክተር ደብረፅዮን መገለጫ ፦ ዛሬ ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መግለጫ ሰጥተው ነበር። ዶ/ር ደብረፅዮን እየተደረገ ባለው ጦርነት ኤርትራ ወታደሮች ከፌዴራል የፀጥታ ኃይል ጋር ግንባር ፈጥረው እየወጉን ነው ብለዋል። ይህን በተጨባጭ ማሳየት እንችላለን ፣ የያዝናቸው የኢሳያስ (ኤርትራ) ወታደሮች አሉ ሲሉ ገልፀዋል። እስካሁን ከ10 ሺ በላይ ወታደሮች ማርከናል ከነዚህ ውስጥ ደግሞ የኢሳያስ ወታደሮች…
'የተከዜ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ'

ትላንት ምሽት ዶክተር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል 'የተከዜ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ' በአየር ተደብድቧል ፤ የትግራይ ክልል ከተሞች በጨለማ ውስጥ እንዲቆዩ ተደርጓል ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

በፌዴራል መንግስት ስር የሚተዳደረው "የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ" ተከዜ በቦንብ እንደተመታ የሚነገረው #ሀሰት ነው ብሏል።

ባለሁለት ክበብ ቅስት ያለው እና በውሀ የተሞላ ግድብ በቦንብ ቢመታ ሊያስከትል የሚችለው መጥለቅለቅ እና ጥፋት ማንም ሊገምተው የሚችለው ነው ሲልም ገልጿል።

* የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ በጉዳዩ ላይ ያወጣው መረጃ ከላይ ተያይዟል !

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
'የሽምግልና የውይይት ጉዳይ'

በፌዴራል መንግስት ስር የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያ በዩጋንዳ የፌዴራሉ ባለስልጣናት "ከህወሓት" ጋር ለሽምግል እና ውይይት ሊቀመጡ እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰት ነው ብሏል።

ይህ መረጃ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር ሲሰራጭ ነበር።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያው ፥ "የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል የህግ የበላይነትን ለማስከበር በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል" ሲል ለህዝብ ባሰራጨው አጭር መግለጫ ገልጿል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Ethiopia

በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ እየተካሄደ ያለው ጦርነት እንዲያበቃ እና ችግሩ በድርድር እንዲፈታ በርካቶች ሲጠይቁ ቆይተዋል።

ህወሓትም ጦርነቱ ቆሞ ችግሩ በውይይት ይፈታ ዘንድ ለAU እና ለሌሎችም ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።

ድርድርን በሚመለከት የፌዴራል መንግስቱ በፍፁም ህወሓት ውስጥ ካሉት 'ወንጀለኛ' ቡድን ጋር ቁጭ ብዬ #አልደራደርም ብሎ አሳውቋል።

ይህ 'ህወሓት' ውስጥ ያለው ቡድን ታሪክ ይቅር የማይለውን ጥፋት አጥፍቷል፣ የሀገር መከታ የሆነውን መከላከያ ሰራዊት አጥቅቷል ፣ ይህን ጉዳይ አምኗል ፤ አሁን እየተካሄደ ያለው የህግ ማስከበር እና የሀገርን ህልውና እና ክብር የማስጠበቅ ዘመቻ የሚጠናቀቀው ወንጀለኞቹ ህግ ፊት ሲቀርቡ ብቻ ነው ሲል ከዚህ ቀደም አቋሙን ገልጿል።

ትላንት ምሽት ድርድርን በሚመለከት በተለያዩ መገናኛ ብዙን አንድ መረጃ ሲሰራጭ ነበር። ይህ የተሰራጨው መረጃው ግን ሀሰተኛ ነው ተብሏል።

ጉዳዩን በሚመለከት ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት የተሰጠው አጭር ምላሽ ይኸው ነው ፦

"ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኀብረት ሊቀ መንበር የሆኑትን የሲሪል ራማፎሳን ልዑካን ተቀብለው በግል ይወያያሉ።

ሆኖም ግን ፣ የፌደራል መንግሥትን እና በህወሓት የሚገኙ ወንጀለኞችን ለማሸማገል ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ በመሰራጨት ላይ የሚገኘው ዜና #ሀሰት መሆኑን እናረጋግጣለን።

#ድርድርን አስመልክቶ የፌደራል መንግሥት ያለው አቋም ፈጽሞ ያልተለወጠ ነው።"

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#BahirDar

በባሕር ዳር ከተማ ውሃ ተበክሏል እየተባለ የሚናፈሰው ወሬ #ሀሰት መሆኑን የባህር ዳር ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ለአብመድ ገልጿል፡፡

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የውሃ እና ፍሳሽ ባለሙያዎች በየዕለቱ በሁሉም ቦታዎች ማለትም (ታንከር ላይ ፣ መሥመር ላይና ቤት ለቤት በመዞር) የፊዚካል ፣ ባዮሎጂካል እንዲሁም የኬሚካል ናሙና ምርመራ ይደርጋሉ።

ዛሬ እና ትናንት በተደረገው የናሙና ምርመራ ምንም ችግር እንደሌለ መረጋገጡን የከተማው ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት አሳውቋል።

ዛሬ ህዳር 25/2013 ውሃ ተበክሏል በሚል ሥጋት ጥቆማ በተደረገባቸው የከተማዋ አካባቢዎች ናሙና ተወስዶ ምንም አይነት ችግር አለመኖሩ ተረጋግጧል።

የከተማው ውሃ በቀላሉ የሚበከል አለመሆኑ የተገለፀ ሲሆን በተለይም አጠራጣሪ በሆኑ አካባቢዎች የተጠናከረ ጥበቃ እየተደረገ ነው።

ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ/ም በኋላም የጥበቃ ሥራው መጠናከሩ ተገልጿል።

ሕዝቡ እውነቱን ተገንዝቦ 'ያለምንም መረበሽ' የእለት ተዕለት ተግባሩን እንዲከውን የከተማው ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት መልዕክት ተላልፏል። (AMMA)

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
"...የውሸት መረጃ ነው፤ የኢትዮጵያ መከላከያ አንዳችም የአፀፋ እርምጃ አልወሰደም" - አቶ ተስፋሁን ሲሳይ

ከትላንት በስቲያ ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "የኢትዮጵያ መከላከያ በሱዳን ኃይሎች የተያዘውን ቦታ አስለቀቅ፤ ሱዳኖቹም አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል" የሚሉ የተለያዩ ወሬዎች ሲሰራጩ ነበር።

የምዕራብ ጎንደር ዞን የኮሚኒኬሽን ኃላፊ የሆኑት አቶ ተስፋሁን ሲሳይ በማህበራዊ ሚዲያ የሚወራው #ሀሰት መሆኑ ለቢቢሲ ሬድዮ የትላንት ስርጭት ተናገረዋል።

የሱዳን ኃይል ከዚህ ቀደም የያዘውን አካባቢዎች አሁንም ለቆ አልወጣም ብለዋል።

አቶ ተስፋሁን፥ "አሁን ባለው ሁኔታ ምንም አይነት ግጭት የለም፤ አሁንም ቦታዎቹን እነሱ እንደያዙት ነው ያለው፤ የተለየ የተደረገ እንቅስቃሴ የለም በኢትዮጵያ በኩል" ሲሉ ተደምጠዋል።

በአካባቢው የመከላከያ እና ሌሎችም የፀጥታ ኃይሎች ስለመኖራቸው እና የወሰዱት የአፀፋ እርምጃ/ቦታዎቹን ለማስለቀቅ ያደረጉት ጥረት እንዳለ የተጠየቁት ኃላፊው ፦ በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች መኖራቸውን ገልፀው እስካሁን ቦታውን ለማስለቀቅ ያደረጉት ጥረት እንደሌለ /የአፀፋ እርምጃም እንዳልተወሰደ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ጦር እርምጃ ወስዶ የሱዳን ኃይል የያዘውን ቦታ ለቆ ወጥቷል ተብሎ የሚወራውን ጉዳይም አቶ ተስፋሁን ፥ "ይሄ የውሸት መረጃ ነው፤ የኢትዮጵያ መከላከያ አንዳችም የአፀፋ እርምጃ አልወሰደም፤ያደረገውም ነገር የለም" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

በተመሳሳይ አንድ ነዋሪ በሰጡት አስተያየት ፥ አሁንም የተያዘው መሬት በሱዳን እጅ እንዳለ ገልፀዋል። "እስካሁን መፍትሄ ሳይገኝ ክረምት ገብቷል፤ ለማረስም አይታሰብም፤ ተስፋ ቆርጠን ያለን የሌለን ንብረት አጥተን ነው ቁጭ ብለን ያለነው" ብለዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ : telegra.ph/BBC-05-08

@tikvahethiopia
#ሀሰተኛ_መረጃ

የመቐለ ጊዜያዊ ከንቲባ የነበሩት አቶ አታኽልቲ አዲስ ሹመት እንደተሰጣቸው ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው ዜና ሀሰተኛ መሆኑን አዲስ ዘይቤ ዘግቧል።

አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ ፥ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ሥራ አስፈጻሚ በመሆን አዲስ ሹመት ስለማግኘታቸው የተሰራጨው ዜና #ሀሰት መሆኑን ተናግረዋል።

የቀድሞው ጊዜያዊ ከንቲባ ፥ "አሁን የመቐለ ነዋሪ ብቻ ነኝ ሲሉ" አስረድተዋል።

ምንጭ፦ www.addiszeyeb.com

@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ እስካሁን የዘጋችው ኤምባሲ አለ ?

የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆኑት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ “ኢትዮጵያ እስካሁን በይፋ የዘጋችው ኤምባሲ የለም” ሲሉ ዛሬ በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙት ኤምባሲዎቿን እንደዘጋች የሚናፈሰው መረጃ #ሀሰት መሆኑን አስገንዝበዋል።

“ነገር ግን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደማንኛውም ተቋም ሪፎርም ላይ ይገኛል ” ያሉ ሲሆን የኤምባሲ እና ቆንስላ ፅህፈት ቤት ሰራተኞች መጥራት የተለመደ የስራ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ወደፊት የሚቀነሱና የሚዘጉ ኤምባሲዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ግን ሳይጠቁሙ አላለፉም። #ENA

@tikvahethiopia
ቱርክ ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ዘመቻ ድሮን ሰጥታለች ?

በኢትዮጵያ የቱርክ ኤምባሲ ፥ ቱርክ ለኢትዮጵያ ሰራዊት ግልጋሎት ይውላሉ የተባሉ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን /ድሮኖች/ እያቀረበች ነው #ሀሰት ሲል አስተባበለ።

ሰሞኑን የኢትዮጵያ መንግስት ለወታደራዊ ዘመቻ የሚሆኑ ቱርክ ሰራሽ ድሮኖች ወደ አገር ውስጥ አስገብቷል የሚሉ ሪፖርቶች በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተሰራጭቶ ነበር።

ይህን ተከትሎ ነው ኤምባሲው ምላሽ የሰጠው።

በኢትዮጵያ የቱርክ ኤምባሲ ፥ "በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ቱርክ ለኢትዮጵያ መንግሥት ድሮኖችን እያቀረበች ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ የሐሰት ነው" ብሏል።

በኢትዮጵያ ቱርክ አምባሳደር የሆኑት ያፕራክ አልፕ ፥ "በአሁኑ ሰዓት ምንም አይነት የቱርክ ሰዉ አልባ አዉሮፕላን ወይንም ድሮኖች በኢትዮጵያ የሉም።" ብለዋል፡፡

@tikvahethiopia
#DireDawa : " ሙሉ እና ጎዶሎ በሚል የተጀመረ የትራንስፖርት አገልግሎት የለም " - የት/ባለስልጣን

በት/ባለስልጣን የድ/ዳ/ቅ/ጽ/ቤት ፥ በድሬደዋ የታክሲ አገልግሎት ሙሉ ጎዶሎ በሚል
መሰጠት ስለመጀመሩ እየተሰራጨ ያለው መረጃ
#ሀሰት ነው ሲል አሳውቋል።

ቅ/መስሪያ ቤቱ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከመሰል የሀሰት ማደናገሪያዎችበመጠበቅ አገልግሎት መስጠታቸውን እንዲቀጥሉም አሳስቧል፡፡

የሚቀየሩ የአገልግሎት አሰጣጦች ሲኖሩ ከትራፊክ ፖሊስ ዳይሬክቶሬት ጋር በመቀናጀት እንደሚወጡና ይህንንም በተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅና በሌሎች ሚዲያዎች ይፋ እንደሚደረግ አሁን ላይ ግን ምንም አይነት የሙሉ ጎዶሎ አገልግሎት እንዳልተጀመረ እና እንደማይጀመር ገልጿል።

ከሰሞኑ በከተማው የታክሲ አገልግሎት ጎዶሎና ሙሉ በሚል እየተሰጠ አንደሚገኝ ተደርጎ ምንጩ ያልታወቀ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል፡፡

@tikvahethiopia
#ሀሰት_ነው !

" ከሱዳን ጋር #በቅርቡ በድንበር ጉዳይ የተደረሰ ስምምነት የለም " - በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ

ሰሞኑን አንዳንድ ሚዲያዎች በሱዳን የሚገኙትን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በመጥቀስ የኢትዮጵያንና የሱዳንን ድንበር በተመለከተ ስምምነት እንደተደረሰ ሲዘግቡ ተስተውሏል።

በተለይ Alsharq AL-awsat English ጋዜጣ በድህረ ገፁ “Addis Ababa, Khartoum Reach Deal on Border Dispute” በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 13 ቀን 2022 ያስነበበው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ጋዜጣው የመረጃውን ምንጭ ሳይጠቅስ ያቀረበው ሲሆን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ከዚህ ጋዜጣ ጋር ግንኙነት እንዳላደረጉ እና መረጃ እንዳልሰጡ ኤምባሲው ገልጿል።

@tikvahethiopia