TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#China_Africa_Expo

በሀገር ውስጥ ላሉ የንግዱ ማህበረሰብ ክፍሎች እንደ ትልቅ የገቢያ ትስስርና ትውውቅ ሊጠቅም ይችላል የተባለው የቻይና-ኢትዮ ኤክስፓ ለሁለተኛ ጊዜ በኤግዚቢሽን ማዕከል ይካሄዳል፡፡

- Grain processing
- Mine crusher & Equipment
- Building/ Construction/ materials (Including PVC resin tile)
- Logistics & Freight forwarding
- Automobile, Sparepart Manufacturing (Including Bus)
- Mobile phone/ home appliance/
- Oil press
- Hardware
- Electronics (Speaker)
- Power (Including Electric power)
- Telecom communication
- Wood manufacturing
- Steel Structure & Aluminium
- Textile Manufacturing
- Cleaning /cosmetic
- Packaging
- Milk Manufacturing
- Pharmaciutucal

በእነዚህና በሌሎች ዘርፎች የተሰማራችሁ የንግዱ ማህበረሰብ ክፍሎች በዚህ ፕሮግራም ላይ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል፡፡

ቀድማችሁ በተከታዩ ሊንክ መመዝገብ ትችላላችሁ https://forms.gle/4K8fntTo5TajBfsL9

#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#CHINA

በቻይና ያሉ ተማሪዎችና ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ለኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] መከላከያ የሚውል 452 ሺህ 589 ዩዋን ድጋፍ መደረጉን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

በቻይና የሚገኙ የኢትዮጵያ ተማሪዎችና አቶ አስቻለው በላይ ከተባሉ የቤጅንግ ነዋሪ በድምሩ 101 ሺህ 189 ዩዋን ገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።

በሌላ በኩል በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች 9 ሺህ 500 ዩዋን ፣ ከተለያዩ የኢፌዴሪ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች አባላት ማለትም ከጓንዦ 3 ሺህ ዩዋን ፣ ከሻንሃይ 5 ሺህ 200 ዩዋን ፣ ከክችንችን 211 ሺህ ዩዋን ሲሰበሰብ በጓንዦ ከተማ ዳያስፖራ አባላት ደግሞ 120 ሺህ ዩዋን ድጋፍ ተገኝቷል።

ከዚህም ውስጥ 351 ሺህ 400 ዩዋን በቀጥታ ቫይረሱን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በኢትዮጵያ ለተቋቋመው ብሔራዊ ሀብት አሰባሳቢ ግብረ ኃይል መላኩን ኤምባሲው ገልጿል።

ቀሪው ከተማሪዎች እና አቶ አስቻለው በላይ ከተባሉት የቤጂነግ ነዋሪ ኢትዮጵያዊ የተገኘው 101 ሺህ 189 ዩዋን ደግሞ የህክምና መሳሪያዎችን ገዝቶ ለመላክ ምርቶችን በማፈላለግ ላይ መሆኑን ኤምሳቢው አስታውቋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#CHINA

በቻይና ነዋሪነታቸውን ያደረጉ በመቶዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን የንግድ ማህበረሰብ አባላትና ተማሪዎች ከቻይናዋ ግዛት ከሚገኙ ሆቴሎችና የጋራ መኖሪያ ቤቶቸ እንዲወጡ ተደረጉ።

የአካባቢው የጤና ባለሙያዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ለማድረግ ነው ቢሉም፣ ከመኖሪያቸው የተባረሩት አፍሪካውያን በበኩላቸው የዘር መድልዎ ተፈፅሞብናል ብለዋል።

"ቫይረሱ አለባችሁ እያሉ ይወነጅሉናል" በማለት በጉዋንግዙ ተማሪ የሆነው ናይጄሪያዊው ቶቤና ቪክተር ተናግሯል።

"የቤት ኪራይ ከፍለናል፤ ኪራዩን ከተቀበሉ በኋላ ከቤት አባረሩን። ከትናንት ጀምሮ ውጭ ነው ያለነው" ብሏል።

ከሰሞኑ አፍሪካውያን በሚኖሩባቸው መንደሮች የኮሮና ቫይረስ እየተዛመተ ነው መባሉን ተከትሎ እነዚህ ሰፈሮች እንዲዘጉ ትእዛዝ ተላልፏል ቢባልም የቻይና ባለስልጣናት አስተባብለዋል።

📹Demola Olarewaju
ምንጭ፦ BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#CHINA

ቻይና የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መነሻን የሚመረምሩ ዓለም አቀፍ አጥኚዎችን አሁን ወደ ሀገርዋ እንደማትጋብዝ አስታውቃለች።

በጄኔቫ የቻይና አምባሳደር እንዳሉት ቻይና አጥኚዎቹን የምትጋብዘው ቻይና በኮሮና ቫይረስ ላይ ድል ከተቀዳጀች በኋላ ነው ብለዋል።

አምባሳደር ቼን ሹ ሀገራቸው አሁን ቅድሚያ የምትሰጠው ወረርሽኙን ማሸነፍ እና የቫይረሱን ጉዳይ ፖለቲካዊ ለማድረግ የሚሰነዘሩ ትርጉም የሌላቸው ውንጀላዎችን መቋቋም ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

የዓለም የጤና ድርጅት በበኩሉ የቫይረሱን ምንጭ ለማጣራት በሚካሄደው ምርመራ ላይ ለመሳተፍ የቻይናን #ግብዣ እየተጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።

ቻይና ግብዣውን መቼ ልታቀርብ እንደምትችል የተጠየቁት ሊቼን ሹ በአሁኑ ወቅት ቅድሚያ ሊሰጣቸው በሚችሉ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረው ፤ ይህን ለማድረግ ደግሞ ትክክለኛውን ድባብ እንፈልጋለን ብለዋል - #DW

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#China #SouthKorea #Russia

- ባለፉት 24 ሰዓት በቻይና አስራ አራት (14) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ ፤ ሁለቱ ከውጭ የገቡ እንደሆኑ ተገልጿል። በቻይና በአንድ ቀን ከ10 በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ ከ9 ቀናት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

- በደቡብ ኮሪያ በ24 ሰዓት 34 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በደቡብ ኮሪያ ከአንድ ወር በኃላ በአንድ ቀን ከ30 በላይ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

- ሩሲያ ውስጥ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ነው ፤ ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 11,012 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በተጨማሪ 88 ሰዎች ሞተዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#China

ቻይና በአዲሱ የኮቪድ-19 ዝርያ የታይዘ የመጀመሪያውን ሰው ሪፖርት አደረገች።

ቫይረሱ የተገኘባት የ23 ዓመት እድሜ ያላት ተማሪ ስትሆን ከብሪታኒያ ወደ ቻይና ገብታ የኮሮና ምርምራ ሲደረግላት ነው ቫይረሱ እንዳለባት የተረጋገጠው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#China

የዓለም ጤና ድርጅት የተመራማሪዎች ቡድን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መነሻ ለማጥናት በቻይናዋ ከተማ ውሃን መግባቱ ተገለፀ።

ቡድኑ ሐሙስ ጠዋት ቻይና የገባው በዓለም ጤና ድርጅትና በቻይና መካከል የወራት ድርድር በኋላ ነው።

10 ተመራማሪዎችን የያዘው ቡድኑ እአአ በ2019 ለወረርሽኙ መነሻ ናቸው ከተባሉ የምርምር ተቋማት፣ ሆስፒታሎች እና የባህር ምግቦች የገበያ ቦታዎች ለሰዎች ቃለ መጠይቅ ከማድረጉ በፊት ተመራማሪዎቹ ለሁለት ሳምንት ራሳቸውን ለይተው ይቆያሉ ተብሏል።

ቻይናመጀመሪያ ላይ ቫይረሱ ሲከሰት ግልፅ ባለመሆኗ በተለይ በአሜሪካ ትችት ይቀርብባታል። ~ BBC

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Tigray

የትግራይ ክልል ወቅታዊ ጉዳዮች ፦

- የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት በትላንትናው ዕለት የተናጠል በሰብዓዊነት ላይ የተመሰረተ የተኩስ አቁም ካወጀ በኃላ በተለያዩ ሀገራት የተሰጡ አስተያየቶች።

- UNICEF ያሰማው ክስ።

- በኔትዎርክ መቋረጥ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ወላጆች እና ትግራይ ክልል ውስጥ ቤተስብ ያላቸው ዜጎች ጭንቀት።

-የአሜሪካ ትግራይን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለች እንደምትገኝ መግለጿ።

- የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ሳራ ጃክሰን ስለ ትግራይ ጉዳይ የሰጡት አስተያየት።

- የህወሓት ኃይሎች ሽረን መያዛቸው፣ የኤርትራ ሰራዊት ከሽረ መውጣቱ።

- የህወሓት ኃይሎች በሰጧቸው አስተያየቶች ላይ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ያወጣው ጠንከር ያለመግለጫ።

- የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት በትግራይ ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራ ስለቀረበለት ጥሪ።

.
.
.
ሌሎችም ጉዳዮች!

(ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የተዘጋጁ)

ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tigray-Update-06-29-2
#CHINA  🇨🇳 #ETHIOPIA 🇪🇹

በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ለሚገኙ እና ይበልጥ ለኮቪድ-19 ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሆን 300 ሺህ ዶዝ የኮቪድ-19 ክትባት ቻይና ለገሰች።

በዛሬው እለት ክትባቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዥያዎ ዢዮዋን ለዶክተር ሊያ ታደሰ አስረክበዋል።

በርክክቡ ወቅት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት ይህ ከቻይና መንግስት ለሶስተኛ ግዜ ድጋፍ የተደረገው 300 ሺህ ዶዝ የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት በዋናነት በስራቸው ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች በተለይም በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ይውላል ብለዋል፡፡

በተጨማሪ ድጋፉ ካለው የኮቪድ-19 ህሙማን መብዛትና የኮቪድ-19 ስርጭት መበራከት ጋር ተያይዞ ያለውን ጫና ከመቀነስ አንጻር ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

ቻይና  🇨🇳 በዛሬው ዕለት የላከችውን 300 ሺህ ዶዝ ክትባትን ጨምሮ ለኢትዮጵያ 1 ሚሊየን ዶዝ የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ድጋፍ አድርጋለች፡፡

#MoHEthiopia

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሀገራት በፀጥታው ም/ቤት ምን አሉ?

#Russia

በUN ፀጥታ ም/ቤት የሩሲያ ተወካይ የኢትዮጵያ መንግስት ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ያወጀው የተናጥል የተኩስ አቁም በህወሓት ሀይሎች መጣሱ አሳዛኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የህወሓት ሀይሎች ከትግራይ ውጪ ወደ አማራና አፋር ክልሎች ጥቃት መክፈታውን፤የሀገር ውስጥ ፈናቃዮች ቁጥር በእጥፍ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።

“የሰብአዊ ድጋፍ ጉዳይን ፖለቲካዊ ማድረግ ተገቢ አይደለም፣ በሚዲያ የሚካሄደው መርዛማ አካሄድ የመሳካት እድሉ አነስተኛ ነው” ብለዋል፤ሰብአዊ ድጋፍ ሲቀርቡ ለትግራይ ብቻ ተብሎ ሳይሆን፤ለአማራ፣ አፋር፣ ሶማሌና ኦሮሚያም ክልሎችም መሆን አለበት ሲሉ ተናግረዋል።

“በኢትዮጵየ ፖለቲካው ውይይት እንደጀመር እንደግፋለን፤ ነገር ግን ውይይቱ ያለማንም ጣልቃ ገብነት #በኢትዮጵያውያን መሪነት ሊካሄድ ይገባል" ብለዋል።

ለኢትዮጵያ ሚደረጉ ድጋፎች የሀገሪቱን ሉአላዊነት እና አንድነት ባስጠበቀ መልኩ ሊካሄድ ይገባል ያሉ ሲሆን፤ ሰኔ ወር በተካሄደው ምርጫ ኢትዮጵያውያን የመረጡት መንግስት ሀገሪቱን ወደቀድሞ መስመር የመመለስ አቅም እንዳለው የሩሲያ መንግስት ያምናል ሲሉ ተግረዋል።

#China

የቻይና ተወካይ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ ሁሉም አካላት በራሳቸው መንግድ በሚያድርጉት የፖለቲካ ውይይት ልዩነቶቻቸውን እንደሚፈቱ ቻይና ታምለች ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ድርጅቶች ስራቸውን በሚሰሩበት ጊዜ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ባከበረ መልኩ መሆን ይገባል ብለዋል። ለኢትዮጵያ ሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። በሰብአዊ መብትና በሰብዓዊ ድጋፍ ስም በኢትዮጵየ የውስጥ ጉዳይ ላይ የሚደረጉ ጣልቃ ገብነቶችን ቻይና አጥብቃ ትቃወማለች ብለዋል።

ያንብቡ፦ telegra.ph/UNSC-08-27

@tikvahethiopia
#CIA #USA #CHINA

የኮሮና ቫይረስ መነሻው ምንድነው ? መደምደሚያ ያላገኘው ጥያቄ አሁንም መነጋገሪያነቱ እንደቀጠለ ነው።

የአሜሪካ ብሔራዊ የስለላ ቢሮ ዳይሬክተር ጽ/ቤት የኮሮና ቫይረስ "ከቻይና ቤተ ሙከራ ያፈተለከ ነው ወይስ በተፈጥሮ የተከሰተ ነው" በሚለው ላይ ለ2 ተከፍሏል።

ነገር ግን ይህ የአገሪቱን 18 የስለላ ኤጀንሲዎች የሚቆጣጠረው ተቋም ኮሮናቫይረስ ባዮሎጂካል የጦር መሣሪያ እንዳልሆነ መደምደሚያ ላይ ደርሷል ሲል ቢቢሲ በድረገፁ ላይ አስነብቧል።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የCIA ሪፖርት ከመውጣቱ ቀደም ብሎ ሪፖርቱን "ፀረ ሳይንስ" በማለት ውድቅ አድርጎታል።

ይህ ከዳይሬክተሩ ጽሕፈት ቤት የወጣው ሪፖርት የደኅንነቱ ማኅበረሰብ በኮሮናቫይረስ መነሻ ላይ አሁንም የተከፋፈለ አቋም መያዙን ገልጿል።

"ሁሉም ኤጀንሲዎች በቫይረሱ ከተበከለ እንስሳ ጋር በተፈጠረ ተፈጥሯዊ ንክኪ ወይም ከቤተ ሙከራ ጋር በተያያዘ ክስተት አምልጦ ይሆናል በሚሉት በሁለቱም ግምቶች ይስማማሉ" ሲል ሪፖርቱ አስነብቧል።

በሪፖርቱ ላይ ስማቸው ያልተጠቀሰ የስለላ ተቋማት፤ ኮሮና ቫይረስን ከሚሸከም እንስሳ ወይም ከቫይረሱ ጋር ቅርበት ካለው ሌላ ቫይረስ ካለበት እንስሳ ጋር በተፈጠረ ንክኪ ቫይረሱ ወደ ሰዎች ተላልፎ ይሆናል ብለው ያምናሉ። ነገር ግን በዚህ መደምደሚያ ላይ ዝቅተኛ እምነት እንዳለቸው ተጠቅሷል።

አንድ የስለላ ድርጅት ከ10 ዓመታት በላይ የኮሮና ቫይረስን በተለይም በለሊት ወፎች ላይ ሲያጠና በቆየው የዉሃን የቫይረሶች የምርምር ተቋም ውስጥ የመጀመሪያው የሰዎች ንክኪ ተፈጥሯል የሚል የተሻለ እምነት ማሳደሩ ተጠቅሷል።

የቢቢሲን ዘገባ ያንብቡ : telegra.ph/BBC-08-28

@tikvahethiopia
#CHINA

ቻይና በኢትዮጵያ 🇪🇹 እየተሻሻለ መጥቷል ያለችውን የሀገር ውስጥ ሁኔታና መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቀነ ገደብ ከመድረሱ በፊት እንዲያበቃ ያሳለፈው ውሳኔ ደስ እንዳሰኛት ገልፃለች።

የኢትዮጵያ ህዝብ የውስጥ ጉዳዩን በአግባቡ የመቆጣጠር ጥበብና ብቃት እንዳለውም አምናለሁ ስትል አስታውቃለች።

@tikvahethiopia
#CHINA

ሹዌ ቢንግ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ተሾሙ።

#ቻይና በአሁኑ ወቅት በግጭት እየታመሰ ላለው የአፍሪካ ቀንድ ሹዌ ቢንግን ልዩ መልዕክተኛ አድርጋ መሾሟ ታውቋል።

ሹዌ ቢንግ ቀደም ሲል በፓፑዋ ኒው ጊኒ የቻይና አምባሳደር በመሆን አገልግለዋል። በአፍሪካ፣ በአሜሪካ እና በኦሺንያ የመሥራት ልምድ እንዳላቸው የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ዛሬ ማክሰኞ አስታውቋል።

@tikvahethiopia
#US #CHINA

ቻይና በአሜሪካ ውስጥ ያሉ ዜጎቿ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳሰበች።

በአሜሪካ የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ በሀገሪቱ ያለው የደህንነት ሁኔታ ለቻይናውያን ዜጎች አሳሳቢ ነው ብሏል።

በመሆኑም አሜሪካ የሚገኙ ቻይናውያን ዜጎች ለግል ደህንነታቸው ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ኤምባሲው አሳስቧል።

በአሜሪካ የሚገኙ የቻይና ዜጎች እና የእሲያ ፊት ያላቸው ሰዎች ላይ የሚንፀባረወቅ ጥላቻ እየጨመረ መሆኑን ኤምባሲው ገልጿል።

በቻይና ዜጎች እና የእሲያ ፊት ያላቸው ሰዎች ላይ ሆን ተብሎ የሚፈፀሙ " ተንኮል አዘል " ጥቃቶች የቻይና ዜጎች ላይ ጉዳት እያስከተለ መሆኑንም ኤምባሲው አስታውቋል።

የጥቃቱ ሰለባ ከሆኑ መካከልም በቻይና የገንዘብ ድጋፍ እየተደረገላቸው በአለም አቀፍ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎችን እና ሰራተኞችን እንደሚገኙበትም ጠቅሷል።

በቻይናውያን ዜጎች ላይ የሚፈፀሙ መሰል ጥቃቶች በአሜሪካ እየተበራከቱ መሆኑን ያስታወቀው ኤምባሲው፤ በአሜሪካ የሚገኙ የቻይና ዜጎች በሀገሪቱ ውስጥ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ለግል ደህንነታቸው ጥንቃቄ እንዲያድርጉ አሳስቧል።

መረጃውን ሮይተርስን ዋቢ አድርጎ አል ዓይን ኒውስ ነው ያስነብበው።

@tikvahethiopia
#CHINA #USA

ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች።

ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነው።

አሜሪካ ሰኞ ዕለት በሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ላይ እጃቸው አለበት ባለቻቸው የቻይና ባለስልጣናት ላይ ነው የቪዛ እገዳ ጥላ ነበር።

መረጃው የአል ዓይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia