TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UPDATE

የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ጽኑ ህሙማንን መቀበል የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ስራ እያጠናቀቀ መሆኑን አስታወቀ።

ሆስፒታሉ የኮሮና ቫይረስ ድንገት ወደ ሀገር ውስጥ ቢገባ በቫይረሱ የተጠቁ ጽኑ ህሙማንን ተቀብሎ እንዲያስተናግድ በጤና ሚኒስቴር መመረጡ ይታወሳል።

በዚህም የተሟላ የህክምና ማሽን እና አምስት የጽኑ ህሙማን ታካሚዎችን ማስተናገድ የሚችል የጽኑ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከል ለይቶ ማዘጋጀቱን ዋና ስራ አስፈጻሚው ዶክተር ታምሩ አሰፋ ገልፀዋል።

ከዚህ ባለፈም በጽኑ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከሉ ውስጥ ለሚሰሩ 40 ሰራተኞች በቫይረሱ ህክምና እንዲሁም የቅድመ ጥንቃቄና መከላከያ ስራዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።

በቫይረሱ ዙሪያ ግንዛቤን ለመፍጠር እንዲያስችልም ብሮሸሮችና በራሪ ወረቀቶች በማተም በሆስፒታሉ ለመታከም ለሚመጡትም ሆነ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑም ነው የተገለፀው።

በአዲስ አበባ ለሚገኙ 13 ሆስፒታሎችም በኢትዮጵያ አየር መንገድና በባቡር ጣቢያዎች ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች 5 ሺህ ለቅድመ መከላከያ የሚያገለግል የአልኮል እጅ ማጽጃ፥ በሆስፒታሉ የፋርማሲ አገልግሎት ክፍል ተመርቶ መሰራጨቱን ከሆስፒታሉ የፌስ ቡክ ገፅ የተገኘነው መረጃ ያመላክታል።

[የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በቤንች ሸኮ ዞን በጉራፈርዳ ወረዳ ከጸጥታ መደፍረስ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 73 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የዞኑ ሠላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አድማሱ ባኩስ እንደገለፁት ግለሰቦቹ የተያዙት የካቲት 8/2012 ዓ.ም በወረዳው ከተከሰተ ግጭት ጋር በተያያዘ እጃቸው እንዳለበት በመጠርጠራቸው ነው።

የወረዳውን ጸጥታ ከማስከበር እና ህዝብን ከማረጋጋት አኳያ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ያልተወጡ አመራሮችን ጨምሮ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል 13 የሚሆኑት የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንደሚገኙበት ይገኙበታል። “ቀሪዎቹ 12 የመንግስት ሠራተኞች ሲሆኑ 48 የሚሆኑት ደግሞ የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው” ብለዋል።

#ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#የካቲት12

ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ በየካቲት 12 ሰማዕታት ዕለት!

ከ83 ዓመት በፊት የካቲት 12 በፋሺስት ጣሊያን ጦር የተጨፈጨፉበት ሰማዕታት ለመዘከርና የአበባ ጉንጉን ለማኖር በዛሬው ዕለት ረፋድ ላይ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ የፓለቲካ ፓርቲ ፕሬዝዳንት የሆነው እስክንድር ነጋና የፓርቲው አባላት በቦታው በመገኘት የህሊና ጸሎትና የፎቶ ስነ-ስርዓት በማካሄድ አስበዋል፡፡

#TikvahFamily
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#DrAmirAman

ጤና ሚኒስቴር በሀገሪቱ የጤናው ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ላላቸው የቀድሞው የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር አሚር አማን የምስጋና እና የእውቅና ኘሮግራም ተካሂዷል።

[ጤና ሚኒስቴር]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ምንነቱ ባልታወቀ ህመም ሰዎች እየሞቱ ነው...

በሱማሌ ክልል ሰዎች ምንነቱ ባልታወቀ ህመም እየሞቱ እንደሆነ ዘ ጋርዲያን አስነብቧል፡፡ ሟቾች እና ታማሚዎች በአፍ እና አፍንጫቸው ደም ይፈሳቸዋል፤ ከባድ ትኩሳትም ታይቶባቸዋል፡፡

የጤና ችግሩ የተከሰተው በቻይናው የካሉብ ጋዝ ፕሮጀክት አካባቢ ነው፡፡ ነዋሪዎች የሕመማችን ምክንያት የፕሮጀክቱ ኬሜካል የምንጠጣውን ውሃ ስለበከለብን ነው ብለዋል፡፡

https://www.theguardian.com/global-development/2020/feb/20/the-mystery-sickness-bringing-death-and-dismay-to-eastern-ethiopia

#WazemaRadio
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#UPDATE

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ለከፍተኛ ኃላፊነት ሹመት ሰጡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዐማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ ፈንታ ደጀንን ከየካቲቲ 5/2012 ዓ.ም ጀምሮ በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ ሹመዋል፡፡

መቀንጨርን ለመከላከል ለሰቆጣ ቃል -ኪዳን ስምምነት ተፈፃሚነት የትምህርት ቤት ምግብናን በማስጀመር፣ በትምህርትና በዐዕምሮ ልማት ላይ ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው የሚታወቁትን ወ/ሮ ፍሬአለም ሽባባውን ደግሞ ከጥር 28/2012 ዓ.ም ጀምሮ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ ዶ/ር ዓብይ ሹመዋቸዋል፡፡ ወ/ሮ ፍሬአለም የታዋቂዋ ድምፃዊ እጅግአየሁ ሽባባው እህት ሲሆኑ በቅርቡም ላስብበት የተሰኘ መጽሐፍም አሳትመዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ከመቂ ቲክቫህ ቤተስቦች፦

ከመቂ ቲክቫህ ቤተሰቦች በደረሰን ጥቆማ ከመቂ 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የአንበጣ መንጋ መከሰቱን ገልፀውልና ህብረተሰቡ መንጋውን ለማባረር ጥረት እያደረገ ይገኛል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በቃፍታ ሁመራ ወረዳ የአንበጣ መንጋ ተከሰተ!

በትግራይ ምዕራባዊ ዞን በቃፍታ ሁመራ ወረዳ ልዩ ስሙ ሕለጌን በተባለው ቀበሌ የአንበጣ መንጋ ከትናንት ጀምሮ መከሰቱን የወረዳው ግብርናና ገጠር ልማት ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ኤክሳይዝታክስ

ከላይ ባለው ምስል የምትመለከቱት የኤክሳይዝ ታክስ የሚከፋባቸው ዕቃዎች ከኤክሳይዝ ታክስ ነፃ የተደረጉ ናቸው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
excise_amharic_new_8.pdf
21.1 MB
#ኤክሳይዝታክስ

ይህ ከኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው የPDF ፋይል ስለ ኤክሳይዝ ታክስ የተሟላ መረጃ የሚሰጥ ነው። ውድ ቤተሰቦቻችን ፋይሉን ከፍታችሁ ብታነቡት ስለኤክሳይዝ ታክስ ለሚፈጠርባችሁ ጥያቄዎች መልስ ይሰጣችኃል።

[21.1 MB WiFi ተጠቀሙ]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በአወዳይ ምን ተፈጠረ?

ዛሬ በአወዳይ ከተማ በመንግሥት እና በተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች መካከል ግጭት መከሰቱን የከተማዋ ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ዛሬ ጠዋት የጠቅላይ ሚንስርት ዶክተር ዐብይ መንግሥት እና ፓርቲን ለመደገፍ የከተማዋ ነዋሪዎች አደባባይ የወጡ ሲሆን፤ በተቃራኒው ደግሞ የጠቅላይ ሚንስትሩን መንግሥት በመቃወም መፈክር እየሰሙ የወጡ ሰዎች እንደነበሩ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

አንድ ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ የፖሊስ ባልደረባ ለቢቢሲ እንደተናገረው "ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይን ለመደገፍ ሰዎች ሰልፍ ወጡ። ከዛ ለምን ለድጋፍ ወጣችሁ የሚሉ ሌሎች ሰዎችም መውጣት ጀመሩ።

ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚያወግዝ መፈክር በማሰማት ድንጋይ መወርወር ጀመሩ" በማለት የግጭቱን አጀማመር ያስረዳል። በደንጋይ ተመተው እና በዱላ ተደብድበው ጉዳት የደረሰባቸው ብዙ ሰዎች መኖራቸውን የፖሊስ አባሉ ተናግረዋል።

More https://telegra.ph/BBC-02-20

#BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በቢራ ምርቶች ላይ የተደርገው የዋጋ ጭማሪ!

- የቢራ ሳጥን ዋጋ እስከ 140 ብር ሲጨምር በርሜል ድራፍት ከ300 ብር በላይ ጨምሯል።

- በአዲስ አበባ ገበያ አንድ ሳጥን ቢራ (24 ጠርሙስ) ከፋብሪካ እንደወጣ የሚያከፋፍልበትን ዋጋ ወደ 430 ብር ከፍ አድርጓል፡፡ ሐበሻ ቢራ በበኩሉ የፋብሪካ ዋጋውን ወደ 415 ብር ከፍ አድርጓል፡፡ ሐይኒከን ቢራ በዋልያ ምርቱ ላይ ከቢጂአይ እኩል የአንድ ሳጥን ቢራ መሸጫ ዋጋውን ወደ 430 ብር አሳድጓል፡፡

- የአንድ በርሜል ድራፍት የማከፋፈያ ዋጋ ላይ የ345 ብር ጭማሪ ተደርጓል፡፡ እስካሁን ሲከፋፈልበት በነበረው 815 ብር ላይ የ345 ብር ተጨምሮ ታክሎበት፣ በ1,165 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዋሊያ ድራፍት በበርሜል 340 ብር ጨምሮ 1,600 ብር እንደሚያከፋፍል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

- በ15 ብር ይሸጡ የነበሩ፣ 330 ሚሊ ሌትር መጠን ያላቸው ቢራዎች ከየካቲት 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ 20 ብር እና ከዚያ በላይ እየተሸጡ ነው፡፡ ከ15 እስከ 20 ብር ይሸጡ የነበሩ ግለሰብ ነጋዴዎችና ግሮሰሪዎችም ከ25 እስከ 30 ብር መሸጥ እንደጀመሩ እየታየ ነው፡፡

More https://telegra.ph/ሪፓርተር-02-20

ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከ6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የምግብና መዋቢያ ምርቶች መያዛቸው ተገልጻል!

ግምታዊ ዋጋቸው ከ6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን መደሃኒትና የመዋቢያ ምርቶችን በህገወጥ መንገድ ሲጓጓዙ በቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረጉን የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ቅቤ እና ማርን ከባእድ ነገሮች ጋር ቀላቅለው ሲሸጡ የተገኙ 13 ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱንና 72 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ጉዳያቸው በህግ እየታየ እንደሚገኝ ተጠቅሷል፡፡

#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia