#UPDATE

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ለከፍተኛ ኃላፊነት ሹመት ሰጡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዐማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ ፈንታ ደጀንን ከየካቲቲ 5/2012 ዓ.ም ጀምሮ በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ ሹመዋል፡፡

መቀንጨርን ለመከላከል ለሰቆጣ ቃል -ኪዳን ስምምነት ተፈፃሚነት የትምህርት ቤት ምግብናን በማስጀመር፣ በትምህርትና በዐዕምሮ ልማት ላይ ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው የሚታወቁትን ወ/ሮ ፍሬአለም ሽባባውን ደግሞ ከጥር 28/2012 ዓ.ም ጀምሮ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ ዶ/ር ዓብይ ሹመዋቸዋል፡፡ ወ/ሮ ፍሬአለም የታዋቂዋ ድምፃዊ እጅግአየሁ ሽባባው እህት ሲሆኑ በቅርቡም ላስብበት የተሰኘ መጽሐፍም አሳትመዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot