TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#FakeNewsAlert

አቶ ንጉሱ ጥላሁን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው ተሾሙ በሚል የተሰራጨው መረጃ #ሀሰት መሆኑ ተገለጸ፡፡ በዛሬው እለት አቶ ንጉሱ ጥላሁን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሁነው እንደተሾሙ በማህበራዊ የትስስር ገጾች በስፋት የተሰራጨው መረጃ #ስህተት መሆኑን አሐዱ ራድዮ እና ቴሌቪዥን ከአቅርብ ምንጮቼ አረጋግጫለሁ ብሏል። አቶ ንግሱ ጥላሁን የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል ባለመሆናቸው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የመሆን እድላቸው ጠባብ መሆኑም ተመልክቷል፡፡

ምንጭ፦ አሀዱ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን
🗞ቀን ሰኔ 27/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

በበርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ላይ የቀድሞው የአማራ ክልል ኮሚንኬሽን ቢሮ ሀላፊ የነበሩት አቶ አሰማኸኝ አስረስ ባህርዳር በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በር ላይ በጥይት ተደብድበው #ተገደሉ እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እና ህዝብ ለማሸበር ሆን ተብሎ የተደርገ የፈጠራ ወሬ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ #ሰራተኞች የእድገት መሰላልና የደሞዝ ስኬል ማሻሻያ ተደረገ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን(ቴዲ አፍሮ) ላይ የግዳያ ሙከራ ተደርገበት በሚል የሚናፈሰው ወሬ ሀሰት ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

በጅማ ከተማ በዛሬው ዕለት ምንም አይነት የድጋፍ ሰልፍ እንዳልነበረ የቲክቫህ ጅማ ቤተሰቦች ተናግረዋል፡፡ የተለያዩ የቆዩ ፎቶዎችን በመጠቀም በጅማ ከተማ ሰልፍ ተደርጓል ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ ውሸት ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ "ሁለት ተማሪዎች ሞቱ" ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ውሸት መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ምንም የሞተ ተማሪ የለም፤ በውሸት መረጃም እንዳትሸበሩ ሲል ዩኒቨርሲቲው መልዕክቱን አስተላልፏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሁለት ተማሪዎች ህይወት ጠፋ እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል!

(ጅማ ዩኒቨርሲቲ)

ውድ የማህበራዊ ሚዲያ ተከታተዮቻችን!

ከሰሞኑ በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ከተፈጠረው ክስተት ጋር ተያይዞ ዩኒቨረሲቲያችን ያለውን አቋም መግለጹንና ቁጣቸውን ሲገልጹ የነበሩ ተማሪዎቻችን ለማረጋጋት ከፍተኛ ስራ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጅ አንዳንድ የማህበራዊ ገጾች በዩኒቨርሲቲያችን ያለውን ዕውነታ ቀና ባለሆነ መንገድ በመዘገብ ውዥንብር እየፈጠሩ መሆኑን ለማወቅ ችለናል፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ ሁለት ተማሪዎች እንደሞቱ ተደርጎ ሲዘገብ አመሽቷል፡፡ ነገር ግን ጉዳዩ ከዕውነት የራቀና አንድም የተማሪ ህይወት ያልጠፋ መሆኑን እየገለጽን ዩኒቨርሲቲያችን በዛሬው ዕለት ከአባገዳዎች፣ ከሐይማኖት አባቶች፣ ነባር መመህራን፣ ተማሪዎች እና የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ተማሪዎቹን የማረጋጋትና ሰላማዊ መማር ማስተማር እንቅስቃሴ እንዲጀመር ሰፊ ጥረት ሲያደረግ የዋለ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

(ጅማ ዩኒቨርሲቲ)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

(ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ)

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረ ችግር የሞተ ተማሪ እና የተደፈረች ተማሪ አለች ተብሎ በማህበራዊ ድህረ-ገጽ ላይ እየተወራ ያለው ዜና ሀሰት መሆኑን እየገለጽን የሞተም የተደፈረም ተማሪ እንደሌለ እናሳውቃለን።

(ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ)

በዚህ አጋጣሚ የዩኒቨርሲቲው ተማሪ የሆኑ የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደገለፁት በተፈጠረው አለመረጋጋት ሳቢያ በርካታ ተማሪዎች እየተንገላቱ እንደሆነ ገልፀውልናል። ግቢው ብቻ ሳይሆን ውጪውም የተረጋጋ ባለመሆኑ ከፍተኛ የደህንነት ስጋት እንደገባቸው ተናግረዋል። የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲያደርጉን እየጠየቁ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethioia
#FakeNewsAlert

በወለጋ ዩንቨርስቲ የሞተ ተማሪ የለም!

በወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተፈጠረ ችግርም ሆነ የሞተ ተማሪ የለም ሲል ዩኒቨርስቲው ገልጾ ተከታዩን መልዕክት አስተላልፏል፡-

በማህበራዊ ድህረ-ገጾች ላይ በወለጋ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረ ችግር የሞተ ተማሪ አለ ተብሎ የሚሰራጨው ዜና ከእውነት የራቀና መሰረተ ቢስ ወሬ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው በአጽኖት ለማሳወቅ ይወዳል። በመሆኑም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የምትገኙ ተማሪዎች በወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተከሰተ ችግርም ሆነ የሞተ ተማሪ አለመኖሩን እንድታውቁ ብሎም በሀሰት ወሬዎች እንዳትሸበሩ ለማሳወቅ እንወዳለን። የዚህ ዓይነቱን መሰረት የለሽ ወሬዎችን የሚያሰራጩ አካላትም ከዚህ እኩይ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ በአጽኖት ያሳውቃል።

"ሰላም ለትምህርት፤ ትምህርት ለሰላም!"

(ወለጋ ዩኒቨርሲቲ)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

ምክትል ጠ/ሚ አቶ ደመቀ መኮንን አልታመሙም!

በአንዳንድ የፌስቡክ ገፆች ምክትል ጠ/ሚ አቶ ደመቀ መኮንን ታመዋል እየተባለ የተለጠፈው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ጋዜጠኛ ተስፋዬ ጌትነት ገለፀ። ጋዜጠኛው በፌስቡክ ገፁ ይፋ ባደረገው መረጃ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዴፓ ስብሰባን ለመካፈል ባህርዳር ከተማ እንዳቀኑ አረጋግጫለሁ ብሏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከሀሰተኛ ገፆች ተጠንቀቁ!! 29,000 like ያለው ይህ በEritrean Press ስም መረጃዎችን የሚያሰራጭ ገፅ ሃሰተኛ ነው!! @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

ከቀናት በፊት 29,000 ገደማ Like ያለው በ "Eritrean Press" ስም የተከፈተው የፌስቡክ ገፅ ሀሰተኛ ዜናዎችን እያሰራጨ እንደሚገኝ ገልፀንላችሁ ነበር። ይኸው ገፅ በዛሬው ዕለት "ኢዜማ እና ብልፅግና ፓርቲ" ለመዋሃድ ንግግር ጀምረዋል የሚል ሃሰተኛ ዜና ይዞ ወጥቷል። ትክክለኛው Eritrean Press የፌስቡክ ገፅ ከ250,000 በላይ Like ያለው ነው። ውድ ቤተሰቦቻችን ከሀሰተኛ መረጃዎች እንድትጠነቀቁ እንመክራለን።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) በሕወሓት ጠሪነት “ሕገ መንግሥትና ህብረ ብሄራዊ ፌዴራላዊ ሥርዓትን ማዳን" በሚል ርዕስ በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ያለው ጉባኤ ላይ እንደማይሳተፍ ለጠሪው አካል እንዳሳወቀ ጠቅሶ በማኀበራ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው ደብዳቤ ግን የሐሰት ዜና መሆኑን በትዊተር ገጹ አሳውቋል፡፡

(አዲስ ዘይቤ)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

"የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ የስራ መልቀቂያ አላስገቡም!"-የመከላከያ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ክፍል

አቶ ለማ መገርሳ የስራ መልቀቂያ አስገብተዋል ተብሎ እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሐሰት መሆኑን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። የመከላከያ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ እንዳስታወቀው ሚንስትሩ አቶ ለማ መገርሳ መልቀቂያ አላስገቡም ብሏል።

አቶ ለማ በአሜሪካ ስራቸውን በማከናወን ላይ ናቸው የስራ መልቀቂያ አስገቡ ተብሎ እየተናፈሰ ያለው መረጃ ከአውነት የራቀ መሆኑን አስታውቋል። የኮሚንኬሽን ክፍሉ ለሬድዮ ጣቢያው እንደገለፀው በተቋም ደረጃ እንደዚህ አይነት መረጃ የለም ውሸት ነው ሲል የተናገረ ሲሆን ከዛ ውጪ የሚናፈሰው ወሬ የፖለቲከኞች እንጂ በተቋም ደረጃ ስለዚህ ጉዳይ የተነሳ ነገር የለም ብሏል፡፡

(ETHIO FM 107.8)

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#FakeNewsAlert

(Elias Meseret)

ይህ "ዛሬ ጠዋት ፕሬዝደንት ኢሳያስ ጠ/ሚር አብይ ልዩ ሰው ነው አሉ፣ እሱን በቃላት ለመግለፅ ይከብዳል ብለው ለጋዜጠኞች ተናገሩ" እየተባለ በብዛት ሼር እየተደረገ ያለ ነገር የሀሰት ነው። ብዙ ተከታይ ያላቸው ግለሰቦች፣ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲህም የሚድያ ሰዎች የሀሰት መረጃ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ላለማሰራጨት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አደም መሐመድ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ እየተባለ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገፆች የሚሰራጨው መረጃ የበሬ ወለደ አይነት ሃሰተኛ መረጃ ነው ሲል የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት በፌስቡክ ገፁ አስታውቋል።
.
ኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ያሰራጨው መልዕክት፦

".... ይህ መረጃ የበሬ ወለደ አይነት የሃሰት መሆኑን እየገለጽን ላልደረሰው #ሼር በማድረግ እንድታደርሱልን በትህትና እንጠይቃለን!" -

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

(Tigray People's Liberation Front)

- ህወሓት ከሌሎች ድርጅቶች ስለሚኖረው ግንኙነት በተመለከተ አንዳንድ የፌስቡክ ፔጆች እያናፈሱት ያሉት መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑ ልናሳስብ እንወዳለን።

- ሁለተኛ አቶ ጌታቸው ረዳ ከዚሁ ጉዳይ በተያያዘ ከድምፂ ወያነ ቴሌብዥን አደረጉት የተባለው ቃለ መጠይቅም ውሸት መሆኑን እንገልፃለን። በመጨረሻ ይህን ተግባር፣ በየጊዜው የውሸት ፕሮፖጋንዳ በመቅረፅ ህዝብን ለማደናገርና ከራሱ ዋና አጀንዳ እንዲወጣ በማሰብ የተፈበረከ የውሸት አጀንዳ መሆኑ መታወቅ ይኖሩበታል።

(Tigray People's Liberation Front)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

"የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኡመድ ኡጁሉ ሞቱ" በሚል ከትላንት ለሊት ጀምሮ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ ሀሰተኛ ነው። ርዕሰ መስተዳደሩ በህይወት አሉ።

ለውድ የቲክቫህ ቤተሰቦች መልዕክት፦

- አንድ ዜና ስትሰሙ ከማጋራታችሁ በፊት ደጋግማችሁ አረጋግጡ። ከተለያዩ ሚዲያዎችም በደንብ አረጋግጡ። በፌስቡክ እንኳን ምታነቡትም ደግማችሁ ደጋግማቹሁ አጣሩ። ጥርጣሬ የሚፈጥርባችሁን ዜና ለሌላ ሰው አታጋሩ።

- ዜናውን ማነው የሚያሰራጨው የሚለውን ገምግሙ። ምንጭ ጠይቁ! ከታማኝ ከሚባሉ ገፆችም እንኳን ቢሆን መረጃ ስታገኙ ከሌሎች ቦታዎችን ማጣራት አትዘንጉ።

- አንድ ሚዲያ ያሰራጨውን ዜና ሌሎች ሚዲየዎችስ ምን አይነት መረጃ ሰጡበት ብላችሁ ማረጋገጥ እንዳትዘነጉ።

ከሀሰተኛ መረጃ ተጠንቀቁ፤ እንጠንቀቅ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

ፕ/ሩን በሚመለከት የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው!

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት 'ህወሓት ወንጀል ፈጥሮላቸው የፍርድ ቤት ክስ እና ማዘዣ ወጣባቸው' በሚል በፌስቡክ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጀ ሀሰተኛ ነው። መረጀው የፈጠራ ወሬ እንደሆንም ሰምተናል። ፕሮፌሰር ክንደያም መረጃውን 'ውሸት' ሲሉ ገልፀውታል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

'ጉራጌ ቲዩብ, Gurage Tube' በሚባል 5,000 አካባቢ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ ኃይሌ ሪዞርት አርባምንጭ ላይ በኮሮና በሽታ የተያዘ ሰው አለ ተብሎ የተለቀቀው እና ከስራ አስኪያጁ አገኘሁት ያለው መረጃ ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን ኃይሌ ሆቴሎች እና ሪዞርቶች ማኔጅመንት አስታውቋል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

በሶማሌ ክልል መፈንቅለ መንግስት ተሞከሮ ከሸፈ መባሉ #ሐሰት መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታወቀ።

የክልሉ የኮሙንኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ ሂቦ መሃመድ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ እንዳሉት በክልሉ መፈንቅለ መንግስት ተደረገ ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ እየተናፈሰ ያለው መረጃ ሃሰት ነው ብለዋል።

ወሬውን የሰማነው ከማህበራዊ ድረገጽ ነው እንጂ የክልሉ አጠቃላይ አመራር በኮሮና ቫይረስ መከላከል ስራ ላይ እየተንቀሳቀሰ ያለው ሲሉ ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia