TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"በአንዳንድ አካባቢዎች ሰው ችግኝ ስያልቅበት በብሩ ገዝቶ እየተከለ ነው 👏" #አዲስአበባ #ጅማ #አዳማ
#ጅማ

የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ በጅማ ከተማ ለሚገኙ ከ400 በላይ ነዋሪዎች ድጋፍ ተደረገ። ዛሬ ድጋፉ የተሰጠው በጅማ ዩኒቨርሲቲ እንስሳትና ህክምና ኮሌጅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ በተዘጋጀው ስነስርአት ላይ ነው፡፡

ፎቶ፦ #Amole
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጅማ_ዩኒቨርሲቲ

ዛሬ የጅማ ዪኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ለአርንጓዴ አሻራ ከ5 መኪና በላይ ወደ ግልገል ጊቤ በመሄድ የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የTIKVAH-ETH #የStopHateSpeech ሀገር አቀፍ ዘመቻዎች/በዩኒቨርሲቲ ደረጃ/ና በየተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ውስጥ የተደረጉ ጉብኝቶችን ለመከታተል #የዩትዩብ ቻናላችንን ይጎብኙ!

#ሀረማያ #ጅማ #ወልቂጤ #ሀዋሳ #ወላይታ_ሶዶ #አርባምንጭ #መቐለ #ዋቻሞ #ወሎ #ደብረብርሃን #ወልዲያ

Watch ""የአንድ እናት ልጆች ነን" በመቐለ ዩኒቨርሲቲ #TIKVAH_ETHIOPIA" on YouTube
https://youtu.be/qjyt56okb3U
#አምቦ #ለኩ #ጅማ #ከሚሴ #ይርጋለም #ሃዋሳ #ሶዶ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

#አዲስ_አበባ
0970514616/ዮናስ ገ/መስቀል/
0924140293/መባ/

#ሰበታ
0932540523/ያሬድ ለማ/
0921421493/ያብስራ ካሳ/

#መቐለ
0912178520/ኤርሚያስ ደጀኔ/
0923602445/ፊራኦል መስፍን/

#ራያ_ቆቦ
+251949256094/ሉላይ/

#ጅማ
0911670454/አሰፋ/

#ድሬዳዋ
0915034762/መሃሪ/

#አዳማ
0949377735/ሰላም/

#ሀዋሳ
+251926429534/ተስፋ/
+251935932153/ብስራት/

#ለኩ
0919687777/ዳዊት እንዳለ/

#ይርጋለም
0953804369-/አሸናፊ/
0964039768-ብርሀኑ/

#ከሚሴ
0915543171/ሁሴን/

#ወላይታሶዶ
+251913776084/Aso/
0926172318/Beza/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት ማህበራትና ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናሳውቃለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ዶዶላ #ሻሸመኔ #ቡታጅራ #ጅማ #ከሚሴ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

ቤት ካላችሁ የመማሪያ መፅሃፍ ቢያንስ አንዱን ለሀገራችሁ በስጦታ አበርክቱ!

#ዶዶላ
0920068173/ቶሎሳ/

#ከሚሴ
0921632606/ኑር አህመድ/
0915543171/ሁሴን/

#ሻሸመኔ
+251915596576/አሸናፊ/

#ቡታጅራ
0910899212/Yab/

#ጅማ
+251942630419/ፍላጎት/
0911670454/አሰፋ/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ የመደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት #ማህበራትና #ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናውቃለን!

📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚

ትግራይ ክልል #ኢሮብ አካባቢ የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት መልዕክት አስቀምጡልን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጅማ #JIMMA

•በጅማ ከተማ ምንም ቤተክርስቲያን አልተቃጠለም
•የሃይማኖት አባቶች አልታረዱም፤ አልተገደሉም
•ከፍተኛ እልቂት እየተፈፀመ ነው የሚባለውም ሀሰት ነው።

የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን👇

√በጅማ ከተማ በሃይማኖት ሽፋን ብጥብጥ ለመፍጠር ሲደረግ የነበረው እንቅስቃሴ በሕዝቡ እና በፀጥታ አካላት ተሳትፎ ከሽፏል።

√በከተማው በሃይማኖት ሽፋን ክልሉን እና ሀገሪቱን ለማመስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አካላት በሕዝቡ እና በፀጥታ ኃይሎች ድጋፍ ሴራቸው ሊከሽፍ ችሏል።

√"በጅማ ከተማ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ተቃጠለ" በሚል የሐሰት ወሬ ሕዝቡን በመቀስቀስ ብጥብጥ ለመፍጠር እና ክስተቱም ወደሌሎች ከተሞች እንዲስፋፋ በተቀናጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር።

የተለያዩ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ለTIKVAH-ETH የተገሩት፦

ስለውጥረቱ መነሻ ተመሳሳይነት ያለው መረጃ አላገኘንም! የሚመለከታቸውን አነጋግረን እናቀርባለን!

•ከትላንት 7:00 ጀምሮ ውጥረት ነበር።

•ቁጥራቸው ብዙ ባልባልም በመኪና ሆነው የሚንቀሳቀሱ አካላት ነበሩ።

•ወጣቶች ቤተክርስቲያን ሲጠብቁ ነው ያደሩት። አሁንም እዛው ናቸው።

•ፖሊስ በከተማው ውስጥ ለየት ያለ እንቅስቃሴ ሲታይ አስቸኳይ መፍትሄ አልሰጠም።

•የተቃጠለ ቤተክርስቲያን የለም፤ ግን ሙከራ ነበር ብለን እናምናለን።

•በፌስቡክ ላይ የሚነገረው ግን በተሳሳተ ምልኩ ነው።

•ፖሊስ ይህን ያህል ውጥረት ሳይፈጠር በከተማው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አካላትን መቆጣጠር ይችል ነበር።

•አመሻሹን ከቤተክርስቲያን የሚመለሱ አካላት በሚመለሱ ወቅት ግርግር ተፈጥሮ ነበር።

•አንዳንድ ወጣቶች በግርግሩ ውስጥ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

•የከተማይቱን ሁኔታ መንግስት ትኩረት ይስጠው።

•ዛሬም አልፎ አልፎ የተኩስ ድምፅ እየሰማን ነው። ውጥረት አለ!

•የከተማው ፀጥታ ኃይል ነገሮች እንዲ ስሳይባባስ ማስቀረት ይችል ነበር፤ ትኩረት አልተሰጠውም።

•ሙስሊሙም ክርስቲያኑም ቤተክርስቲያን እየጠበቀ ነው።

•ያለውን ስጋት ለመቅረፍ መንግስት አስፈላጊውን ትኩረት ይስጥና ይስራ።

•ሚዲያዎችም ከአንድ ወገን ብቻ የሚያቀርቡትን መረጃ ማስተካከል አለባቸው።

#TIKVAH_ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጅማ

ዛሬም በጅማ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ ነበር። በከተማዋ ውጥረት ከመንገሱ ባሻገር በሰውም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩን አንድ የከተማዋ ነዋሪ ለጀርመን ራድዮ ጣቢያ ተናግረዋል። ወታደሮችም የፌዴራል ፖሊሶችም የኦሮሚያ ፖሊሶችም አድማ በታኞችም አሉ፤ በከተማዋ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ይገኛል ሲሉ የከተማው ነዋሪ ገልፀዋል።

#DW

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Congratulations 🎉

ዛሬ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ።

#ጅማ_ዩኒቨርሲቲ

ጅማ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 868 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ተማሪዎቹ በመጀመሪያ፣ ሁለተኛ እና ሦሥተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ያስመረቃቸው ተማሪዎች በመደበኛ፣ በተከታታይ፣ በርቀት እንዲሁም በክረምት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

#ዋቻሞ_ዩኒቨርሲቲ

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ማስመረቅ ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው 3 ሺ 134 የቅድመ ምረቃ እና 42 የድህረ ምረቃ ተማሪዎችን በድምሩ 3 ሺህ 176 ተማሪዎችን ዛሬ እና ነገ ያስመርቃል።

ዩኒቨርሲቲው ከሚያስመርቃቸው ተማሪዎች መካከል 434 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች #በዱራሜ_ካምፓስ የተማሩ ሲሆን የምርቃት ስነ - ስርዓታቸው ነገ ይካሄዳል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮችን https://publielectoral.lat/joinchat/RYD_4tbNBwRoKR2h ተከታተሉ።

@tikvahethiopia