TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#China_Africa_Expo

በሀገር ውስጥ ላሉ የንግዱ ማህበረሰብ ክፍሎች እንደ ትልቅ የገቢያ ትስስርና ትውውቅ ሊጠቅም ይችላል የተባለው የቻይና-ኢትዮ ኤክስፓ ለሁለተኛ ጊዜ በኤግዚቢሽን ማዕከል ይካሄዳል፡፡

- Grain processing
- Mine crusher & Equipment
- Building/ Construction/ materials (Including PVC resin tile)
- Logistics & Freight forwarding
- Automobile, Sparepart Manufacturing (Including Bus)
- Mobile phone/ home appliance/
- Oil press
- Hardware
- Electronics (Speaker)
- Power (Including Electric power)
- Telecom communication
- Wood manufacturing
- Steel Structure & Aluminium
- Textile Manufacturing
- Cleaning /cosmetic
- Packaging
- Milk Manufacturing
- Pharmaciutucal

በእነዚህና በሌሎች ዘርፎች የተሰማራችሁ የንግዱ ማህበረሰብ ክፍሎች በዚህ ፕሮግራም ላይ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል፡፡

ቀድማችሁ በተከታዩ ሊንክ መመዝገብ ትችላላችሁ https://forms.gle/4K8fntTo5TajBfsL9

#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#CHINA

በቻይና ያሉ ተማሪዎችና ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ለኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] መከላከያ የሚውል 452 ሺህ 589 ዩዋን ድጋፍ መደረጉን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

በቻይና የሚገኙ የኢትዮጵያ ተማሪዎችና አቶ አስቻለው በላይ ከተባሉ የቤጅንግ ነዋሪ በድምሩ 101 ሺህ 189 ዩዋን ገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።

በሌላ በኩል በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች 9 ሺህ 500 ዩዋን ፣ ከተለያዩ የኢፌዴሪ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች አባላት ማለትም ከጓንዦ 3 ሺህ ዩዋን ፣ ከሻንሃይ 5 ሺህ 200 ዩዋን ፣ ከክችንችን 211 ሺህ ዩዋን ሲሰበሰብ በጓንዦ ከተማ ዳያስፖራ አባላት ደግሞ 120 ሺህ ዩዋን ድጋፍ ተገኝቷል።

ከዚህም ውስጥ 351 ሺህ 400 ዩዋን በቀጥታ ቫይረሱን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በኢትዮጵያ ለተቋቋመው ብሔራዊ ሀብት አሰባሳቢ ግብረ ኃይል መላኩን ኤምባሲው ገልጿል።

ቀሪው ከተማሪዎች እና አቶ አስቻለው በላይ ከተባሉት የቤጂነግ ነዋሪ ኢትዮጵያዊ የተገኘው 101 ሺህ 189 ዩዋን ደግሞ የህክምና መሳሪያዎችን ገዝቶ ለመላክ ምርቶችን በማፈላለግ ላይ መሆኑን ኤምሳቢው አስታውቋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#CHINA

በቻይና ነዋሪነታቸውን ያደረጉ በመቶዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን የንግድ ማህበረሰብ አባላትና ተማሪዎች ከቻይናዋ ግዛት ከሚገኙ ሆቴሎችና የጋራ መኖሪያ ቤቶቸ እንዲወጡ ተደረጉ።

የአካባቢው የጤና ባለሙያዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ለማድረግ ነው ቢሉም፣ ከመኖሪያቸው የተባረሩት አፍሪካውያን በበኩላቸው የዘር መድልዎ ተፈፅሞብናል ብለዋል።

"ቫይረሱ አለባችሁ እያሉ ይወነጅሉናል" በማለት በጉዋንግዙ ተማሪ የሆነው ናይጄሪያዊው ቶቤና ቪክተር ተናግሯል።

"የቤት ኪራይ ከፍለናል፤ ኪራዩን ከተቀበሉ በኋላ ከቤት አባረሩን። ከትናንት ጀምሮ ውጭ ነው ያለነው" ብሏል።

ከሰሞኑ አፍሪካውያን በሚኖሩባቸው መንደሮች የኮሮና ቫይረስ እየተዛመተ ነው መባሉን ተከትሎ እነዚህ ሰፈሮች እንዲዘጉ ትእዛዝ ተላልፏል ቢባልም የቻይና ባለስልጣናት አስተባብለዋል።

📹Demola Olarewaju
ምንጭ፦ BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#CHINA

ቻይና የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መነሻን የሚመረምሩ ዓለም አቀፍ አጥኚዎችን አሁን ወደ ሀገርዋ እንደማትጋብዝ አስታውቃለች።

በጄኔቫ የቻይና አምባሳደር እንዳሉት ቻይና አጥኚዎቹን የምትጋብዘው ቻይና በኮሮና ቫይረስ ላይ ድል ከተቀዳጀች በኋላ ነው ብለዋል።

አምባሳደር ቼን ሹ ሀገራቸው አሁን ቅድሚያ የምትሰጠው ወረርሽኙን ማሸነፍ እና የቫይረሱን ጉዳይ ፖለቲካዊ ለማድረግ የሚሰነዘሩ ትርጉም የሌላቸው ውንጀላዎችን መቋቋም ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

የዓለም የጤና ድርጅት በበኩሉ የቫይረሱን ምንጭ ለማጣራት በሚካሄደው ምርመራ ላይ ለመሳተፍ የቻይናን #ግብዣ እየተጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።

ቻይና ግብዣውን መቼ ልታቀርብ እንደምትችል የተጠየቁት ሊቼን ሹ በአሁኑ ወቅት ቅድሚያ ሊሰጣቸው በሚችሉ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረው ፤ ይህን ለማድረግ ደግሞ ትክክለኛውን ድባብ እንፈልጋለን ብለዋል - #DW

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#China #SouthKorea #Russia

- ባለፉት 24 ሰዓት በቻይና አስራ አራት (14) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ ፤ ሁለቱ ከውጭ የገቡ እንደሆኑ ተገልጿል። በቻይና በአንድ ቀን ከ10 በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ ከ9 ቀናት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

- በደቡብ ኮሪያ በ24 ሰዓት 34 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በደቡብ ኮሪያ ከአንድ ወር በኃላ በአንድ ቀን ከ30 በላይ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

- ሩሲያ ውስጥ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ነው ፤ ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 11,012 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በተጨማሪ 88 ሰዎች ሞተዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#China

ቻይና በአዲሱ የኮቪድ-19 ዝርያ የታይዘ የመጀመሪያውን ሰው ሪፖርት አደረገች።

ቫይረሱ የተገኘባት የ23 ዓመት እድሜ ያላት ተማሪ ስትሆን ከብሪታኒያ ወደ ቻይና ገብታ የኮሮና ምርምራ ሲደረግላት ነው ቫይረሱ እንዳለባት የተረጋገጠው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#China

የዓለም ጤና ድርጅት የተመራማሪዎች ቡድን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መነሻ ለማጥናት በቻይናዋ ከተማ ውሃን መግባቱ ተገለፀ።

ቡድኑ ሐሙስ ጠዋት ቻይና የገባው በዓለም ጤና ድርጅትና በቻይና መካከል የወራት ድርድር በኋላ ነው።

10 ተመራማሪዎችን የያዘው ቡድኑ እአአ በ2019 ለወረርሽኙ መነሻ ናቸው ከተባሉ የምርምር ተቋማት፣ ሆስፒታሎች እና የባህር ምግቦች የገበያ ቦታዎች ለሰዎች ቃለ መጠይቅ ከማድረጉ በፊት ተመራማሪዎቹ ለሁለት ሳምንት ራሳቸውን ለይተው ይቆያሉ ተብሏል።

ቻይናመጀመሪያ ላይ ቫይረሱ ሲከሰት ግልፅ ባለመሆኗ በተለይ በአሜሪካ ትችት ይቀርብባታል። ~ BBC

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Tigray

የትግራይ ክልል ወቅታዊ ጉዳዮች ፦

- የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት በትላንትናው ዕለት የተናጠል በሰብዓዊነት ላይ የተመሰረተ የተኩስ አቁም ካወጀ በኃላ በተለያዩ ሀገራት የተሰጡ አስተያየቶች።

- UNICEF ያሰማው ክስ።

- በኔትዎርክ መቋረጥ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ወላጆች እና ትግራይ ክልል ውስጥ ቤተስብ ያላቸው ዜጎች ጭንቀት።

-የአሜሪካ ትግራይን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለች እንደምትገኝ መግለጿ።

- የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ሳራ ጃክሰን ስለ ትግራይ ጉዳይ የሰጡት አስተያየት።

- የህወሓት ኃይሎች ሽረን መያዛቸው፣ የኤርትራ ሰራዊት ከሽረ መውጣቱ።

- የህወሓት ኃይሎች በሰጧቸው አስተያየቶች ላይ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ያወጣው ጠንከር ያለመግለጫ።

- የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት በትግራይ ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራ ስለቀረበለት ጥሪ።

.
.
.
ሌሎችም ጉዳዮች!

(ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የተዘጋጁ)

ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tigray-Update-06-29-2
#CHINA  🇨🇳 #ETHIOPIA 🇪🇹

በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ለሚገኙ እና ይበልጥ ለኮቪድ-19 ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሆን 300 ሺህ ዶዝ የኮቪድ-19 ክትባት ቻይና ለገሰች።

በዛሬው እለት ክትባቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዥያዎ ዢዮዋን ለዶክተር ሊያ ታደሰ አስረክበዋል።

በርክክቡ ወቅት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት ይህ ከቻይና መንግስት ለሶስተኛ ግዜ ድጋፍ የተደረገው 300 ሺህ ዶዝ የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት በዋናነት በስራቸው ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች በተለይም በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ይውላል ብለዋል፡፡

በተጨማሪ ድጋፉ ካለው የኮቪድ-19 ህሙማን መብዛትና የኮቪድ-19 ስርጭት መበራከት ጋር ተያይዞ ያለውን ጫና ከመቀነስ አንጻር ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

ቻይና  🇨🇳 በዛሬው ዕለት የላከችውን 300 ሺህ ዶዝ ክትባትን ጨምሮ ለኢትዮጵያ 1 ሚሊየን ዶዝ የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ድጋፍ አድርጋለች፡፡

#MoHEthiopia

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሀገራት በፀጥታው ም/ቤት ምን አሉ?

#Russia

በUN ፀጥታ ም/ቤት የሩሲያ ተወካይ የኢትዮጵያ መንግስት ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ያወጀው የተናጥል የተኩስ አቁም በህወሓት ሀይሎች መጣሱ አሳዛኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የህወሓት ሀይሎች ከትግራይ ውጪ ወደ አማራና አፋር ክልሎች ጥቃት መክፈታውን፤የሀገር ውስጥ ፈናቃዮች ቁጥር በእጥፍ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።

“የሰብአዊ ድጋፍ ጉዳይን ፖለቲካዊ ማድረግ ተገቢ አይደለም፣ በሚዲያ የሚካሄደው መርዛማ አካሄድ የመሳካት እድሉ አነስተኛ ነው” ብለዋል፤ሰብአዊ ድጋፍ ሲቀርቡ ለትግራይ ብቻ ተብሎ ሳይሆን፤ለአማራ፣ አፋር፣ ሶማሌና ኦሮሚያም ክልሎችም መሆን አለበት ሲሉ ተናግረዋል።

“በኢትዮጵየ ፖለቲካው ውይይት እንደጀመር እንደግፋለን፤ ነገር ግን ውይይቱ ያለማንም ጣልቃ ገብነት #በኢትዮጵያውያን መሪነት ሊካሄድ ይገባል" ብለዋል።

ለኢትዮጵያ ሚደረጉ ድጋፎች የሀገሪቱን ሉአላዊነት እና አንድነት ባስጠበቀ መልኩ ሊካሄድ ይገባል ያሉ ሲሆን፤ ሰኔ ወር በተካሄደው ምርጫ ኢትዮጵያውያን የመረጡት መንግስት ሀገሪቱን ወደቀድሞ መስመር የመመለስ አቅም እንዳለው የሩሲያ መንግስት ያምናል ሲሉ ተግረዋል።

#China

የቻይና ተወካይ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ ሁሉም አካላት በራሳቸው መንግድ በሚያድርጉት የፖለቲካ ውይይት ልዩነቶቻቸውን እንደሚፈቱ ቻይና ታምለች ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ድርጅቶች ስራቸውን በሚሰሩበት ጊዜ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ባከበረ መልኩ መሆን ይገባል ብለዋል። ለኢትዮጵያ ሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። በሰብአዊ መብትና በሰብዓዊ ድጋፍ ስም በኢትዮጵየ የውስጥ ጉዳይ ላይ የሚደረጉ ጣልቃ ገብነቶችን ቻይና አጥብቃ ትቃወማለች ብለዋል።

ያንብቡ፦ telegra.ph/UNSC-08-27

@tikvahethiopia