TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ብዙ አይነት ቀለም ቢኖረንም #በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ አንድ ነን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከብሄራዊ ትያትር⬆️

"የክቡር ዶ/ር አርቲስት #ጥላሁን_ገሰሰ 78ኛ ዓመት #የልደት ቀን መታሰቢያ ዝግጅት ዛሬ #በኢትዮጵያ_ብሔራዊ ቲያትር በደመቀ ስነ ስርዓት እየተከበረ ይገኛል።"

ምንጭ፦ ሱራፌል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወንጀለኞች መሸሸጊያ የላቸውም...

#በኢትዮጵያ_ወንጀል_ሰርተው በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የትም ሆነ የት መሸሸጊያ ያላቸውን እጃቸውንም #አንጠልጥዬ ለኢትዮጵያ መንግስት አስረክባለሁ ሲል አለም አቀፍ የፖሊስ ተቋም ኢንተርፖል ማስተማመኛ ሰጠ፡፡

ትናንትና አዲስ አበባ የመጡት የኢንተርፖል ዋና ሀላፊ ዶ/ር ጀርጋን ስቶክ ከፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል እንዳሻው ጣሰው ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው ወሬው የተሰማው፡፡

ከንግግሩ በኋላ መግለጫ የሰጡት ኮሚሽነር ጀነራል #እንዳሻው_ጣሰው በኢትዮጵያ ወንጀል ሰርተው በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያንን ኢንተርፖል ለኢትዮጵያ አሳልፎ እንደሚሰጥ ማስተማመኛ ሰጥቷል ብለዋል፡፡

ኮሚሽነር ጀነራሉ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት የፈፀሙና ሀገር የዘረፉ ሰዎች ግማሾቹ በሀገር ውስጥ ግማሾቹ ደግሞ ባህር አቋርጠው በውጭ አገር እንደሚኖሩ ታውቋል ብለዋል፡፡

ይህንን ወንጀል ፈፃሚዎቹ የትም ይደበቁ የትም ይኑሩ ኢንተርፖል እጃቸውን አንጠልጥሎ ለኢትዮጵያ መንግስት እንደሚያስረክብ ሀላፊው አረጋግጠውልናል ሲሉ መናገራቸውን ከመንግስታዊ ምንጮች ስምቻለሁ ብሎ ሸገር ዘግቧል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከሰሞኑ ባስተላለፉት መልዕክት በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች ማንም ይሁን ማን ከየትኛውም ብሔር ገብተው ይደበቁ፣ የትኛውም ወገን ይጩህላቸው በወንጀል እስከተጠረጠሩ ድረስ ካሉበት አድነን ለህግ እናቀርባቸዋልን ማለታቸው
ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አና ጎሜዝ አዲስ አበባ ገቡ🔝

#አና_ጎሜዝ አዲስ አበባ ገብተዋል። አና ጎሜዝ #በኢትዮጵያ የሦስት ቀናት ጉብኝት ለማድረግ ነው ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ የገቡት። በሦስት ቀናት ቆይታቸው የመንግስት #ባለስልጣናትን፣ የፓርቲ #መሪዎችንና የበጎ አድራጎት አመራሮችን እንዲሁም ከመገናኛ ብዙሃን ጋር እንዲገናኙ ፕሮግራም ተይዞላቸዋል፡፡

Via Getu Temsegn
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር🔝

#በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታዩ ያሉት የፀጥታ ችግሮች በርካቶች ከቀያቸው #እንዲፈናቀሉ እና የሰው ሕይወት በየቦታው #እንዲቀጠፍ ምክንያት እየሆኑ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ 51 አህጉረ ስብከቶች ስለሰላም የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና አተገባበር ዙሪያ ለሃይማኖት አባቶች እና ለምዕመናን በባሕር ዳር ስልጠና እየሰጠች ነው፡፡

በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ደብረ ፀሐይ ሰላም አድርጊው ማርያም ገዳም አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ፍቅረ ማርያም ‹‹አሁን ላይ በሀገሪቱ የተፈጠረው የሰላም እጦት የሰው ልጆች ለእግዚአብሔር ያለመታዘዝ ምንጮች ናቸው፤ እግዚአብሔር ግን በመጽሐፍ ቅዱስ በምድር ላይ ሳለን የሰላም አስፈላጊነት የሁሉም ነገር ቁልፍ ናት ብሎ አስተምሮናል፤ ይህ ሰላም እንዲኖር የሃይማኖት አባቶች በጸሎት እና አስተምህሮ ከዚህ የበለጠ መሥራት እንደሚጠበቅብን አመላካች ነው›› ብለዋል፡፡

የፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ሰፊው ወልደትንሳኤ ካህናት ሕዝቡ ሰላምን ያገኝ ዘንድ እንዲያስተምሩ አደራ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል፡፡ ‹‹ካህናት ስለሰላም የሠራነው ሥራ ስለምን በዚህ ትውልድ ፍሬ #አላፈራም? ሕዝቡስ ስለምን ሰላምን አጣ? ብለን ሁከት የሚፈጥር እንዳይኖር በትኩረት እንድንሠራ ኃለፊነት አለብን›› ብለዋል፡፡

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ #አብርሃም ደግሞ ሀገሪቱ ዜጎች እየተሰደዱ፣ ሀብት ንብረታቸው እየወደመ እና ሕይወታቸውን እያጡ ያሉበት ወቅት ላይ እንደምትገኝ ነው የተናገሩት፡፡ ሁኔታው ቤተ ክርስቲያን #ስለሰላም ከዚህ በላይ መሥራት እንዳለባት አመላካች መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ብጹዕነታቸው ‹‹ሰላምን የማይሻ ሰው ውስጡ የፍርሃት ባሕር አለ፡፡ በፍርሃት የሚቅበዘበዝ ትውልድ ደግሞ የተዋቡ ከተሞችን ዶግ አመድ ያደርጋል›› ነው ያሉት፡፡ ግጭት የሕጻናት እና እናቶችን ዋይታ እንደሚያበዛና ለፀብ የሚያነሳሱ ሰበቦችና መደለያዎች ግን በርካታ መሆናቸውንም አመልክተዋል፡፡ ‹‹የምንመራው ሕዝብ #ሰላም_ከሌለው አይጸድቅም፤ ጽድቅ የማያገኝ የእግዚአብሔር ትውልድ እንዳይኖር ደግሞ የሃይማኖት አባቶች ከዚህም በላይ መሥራት ይኖርብናል›› በማለትም አቡነ አብርሃም አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethioia
የጥላቻ ንግግሮች‼️

#በኢትዮጵያ የጥላቻ ንግግሮች እና ቅስቀሳዎች ለብዙዎች ሞት፤ ለበርካቶች መፈናቀል እና ለዘመናት የተገመዱ ማኅበራዊ ትስስሮች መላላትን ንብረት መውደም ምክንያት መሆናቸው በከፍተኛ መጠን ማደግ ምክንያት መሆናቸው ተነገረ።

በብሄር አደረጃጀት የተዋቀረው የሃገሪቱ የፖለቲካ ስርአተ ማህበር የችግሩ ዋነኛ ምንጭ በመሆኑ የህግ ማእቀፎችን ከማውጣት በላይ መዋቅሩ ላይ መስራት እንደሚገባም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ፕሮጀክት ከካናዳ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ስለ ጥላቻ ንግግር ምንነ፤ #የጥላቻ_ንግግር በኢትዮጵያ ሕግ ማእቀፍ እንዴት ይታያል፤ የማኅራዊ ሚዲያ መስፋት አጠቃቀም እና የጥላቻ ንግግር አዝማሚያዎች ምን ይመስላሉ? በሚሉ እና ከማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምጋር በተገናኙ ያሉ ክፍተቶችን ለመዳሰስ ዛሬ ውይይት ተደርጓል።

ብሄርን እንደ #አቀጣጣይ ነገር መጠቀም፤ ከዚህ በፊት ተበድያለሁ የሚል ስሜት ማደግ እና የማኅበራዊ መገናኛዎችን በስፋት የመጠቀም ባህል እያደገ መምጣት ችግሩን ተቆጣጣሪ አልባ እያደረገው መሆኑም በውይይቱ ተዳስሷል፡፡

የብሄር ማንነትን እንደ ስነልቦናና ማህበራዊ ወሳኝ እሴት በማየት ቋንቋ የሚጎለብበት፤ ባህል የሚዳብርበትና ታሪክ ጥበቃ የሚደረግበት ተቋማዊ ቅርጽ መፍጠር ለችግሩ መቃለል እንደመፍትሄ ተቀምቷል በውይይቱ።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

የሱዳን ጦርና ተቃዋሚዎች የሽግግር መንግስት ለመመስረት #ከስምምነት ደረሱ። ከአልበሽር መውደቅ በኃላ በአፍሪካ ህብረት እና #በኢትዮጵያ አደራዳሪነት በሱዳን ወታደራዊ አመራሮችና ተቃዋሚዎች መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ዛሬ ላይ ህገ መንግስታዊ ስምምነት በመድረስ ተቋጭቷል።

የአፍሪካ ህብረት እንዳስታወቀው ከሆነ ሁለቱ አካላት ሱዳንን አዲስ ህገ መንግስታዊ የሽግግር መንግስት አቋቁመው ወደ አዲስ ምሽራፍ ለማሻገር ተስማምተዋል።

የህብረቱ አደራዳሪ #ሞሐመድ_ሀሰን ለመገናኛ ብዙሃን እንዳሉት ከሁለቱም ወገን በስምምነቱ ዝርዝር አፈፃፀሞች ላይም ወይይቱን ለመቀጠል ተስማምተዋል። የሁለቱ ወገኖች ስምምነት ሰነድም የሽግግር መንግስቱና የመንግስት መዋቅሮች የስልጣን ግንኙነትና ክፍፍልንም ያማላከተ ነው ተብሏል።

ሱዳን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷ #ኦማር_አልበሽር በህዝባዊ ተቃውሞ ከስልጣን ከተወገዱ በኃላ ካለፈው ሚያዚያ ጀምሮ በከባድ ቀውስ ውስጥ ለመሰንበት ተገዳለች። ወታደራዊ ኃይሉና የተቃዋሚዎች ጎራ የሽግግር መንግስት መስርተው ወደፊት ለመራመድ ከስምመነት መድረሳቸውን ተከትሎ ሱዳናዊያን በዛሬው ዕለት በካርቱም አደባባዮች ወጥተው ደስታቸውን እየገለፁ መሆኑ ተዘግቧል።

ምንጭ፦ #አልጀዚራና #ቢቢሲ/#etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጥንቃቄ #አዲስ_አበባ

🏷ከገርጂ መብራት ወደ የረር በሚወስደው መንገድ እያሽከረከራችሁ የምትገኙ መንገዱ በውሃ ተሞልቷልና ጥንቃቄ አድርጉ።

√በሌሎች የአዲስ አበባ አካባቢዎችና #በኢትዮጵያ ከተሞች የምትገኙ የTIKVAH-ETHIOPIA ቤተሰብ አባላት ወቅቱ ክረምት በመሆኑ ስታሽከረክሩ ከፍተኛ #ጥንቃቄ አድርጉ።

ፎቶ: ኤርሚ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኤሌክትሪክ ኃይል የምትሰራዋ መኪና!

ዛሬ የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ 'በኤሌክትሪክ ኃይል' የምትሠራ መኪና በማራቶን ሞተርስ ሙሉ በሙሉ #በኢትዮጵያ የተገጣጠመች በስጦታነት እንደተበረከተላቸው ይታወቃል።

ይህች በኤሌክትሪክ ኃይል የምትሰራው መኪና በአንድ ጊዜ ሙሉ ቻርጅ 300 ኪሎ ሜትር (ከአዲስ አበባ - ሀዋሳ) ድረስ መጓዝ እንደምትችል ጠቅላይ ሚስትር ዶ/ር አብይ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopiaOfficial
#በኢትዮጵያ_ኮቪድ19_እየተባባሰ_ነው😷

የጤና ሚኒስቴር ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ዶክተር ተገኔ ረጋሳ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እየተባባሰ መምጣቱን #ለቪኦኤ ተናገሩ።

ዶ/ር ተገኔ ሰው ‘አስገዳጅ መመሪያ ተነስቷል ፤ ኮሮና ቫይረስ የለም’ በሚሉ የተሳሳቱ አስተሳሰቦች እየተመራ እራሱን ለበሽታው እያጋለጠ መሆኑን ገልፀዋል።

ይሁን እንጂ አስገዳጅ መመሪያውም አለመነሳቱን፣ የቫይረሱ ሥርጭትም እየተባባሰ መሆኑን ዶክተር ተገኔ አሳስበዋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
5 ዓመት የቱርክ መፈንቅለ መንግስት ከከሸፈ ...

እአአ ጁላይ 15/2016 ተሞክሮ የከሸፈው የቱርክ መፈንቅለ መንግስት ትላንት 5 ዓመት ደፍኗል። በወቅቱ የቱርክ ህዝብ ታንክን ጨምሮ ከባባድ መሳሪያዎችን በባዶ እጁ ፊት ለፊት በመጋፈጥ እጅግ በተጠና ሁኔታ የተደራጀውን ሙከራ ያከሸፈው።

ተሞክሮ በከሸፈው መፈንቅለ መንግስት ወቅት ለሀገራቸው ዘብ ቆመው ህወታቸውን ያጡ የቱርክ ዜጎች ትላንት በመላው ቱርክ ታስበዋል።

ከቱርክ ውጭ በሚገኙም የቱርክ ኤምባሲዎችም ዕለቱ ታስቦ ውሏል።

#በኢትዮጵያ የቱርክ ኤምባሲ አባላት ዕለቱን (ጁላይ 15) እና በዕለቱ ህይወታቸው ያለፈውን 251 ዜጎች በማስታወስ 15 ችግኞችን በአዲስ አበባ ተክለዋል።

የሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን መንግስት ላይ በ2016 በተሞከረው መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ወቅት 251 ዜጎች ሲሞቱ 2,200 ሰዎች መጎዳታቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ በ #ኢትዮጵያ ጉዳይ ፦

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ም/ቤት (UNSC) በትግራይ ክልል ግጭት ዙሪያ ትላንት ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ የድርጅቱ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስ የተገኙ ሲሆን፤ በጦርነቱ የተካፈሉ አካላት በሙሉ የተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ምንም እንኳን የኢትዮጵያ መንግስት የተናጥል ተኩስ አቁም በማወጅ ከትግራይ ቢወጣም የህወሓት ሀይሎች ወደ ጎረቤት አፋር እና አማራ ክልሎች ጥቃት በመክፈታቸው አጠቃላይ የተኩስ አቁም ላይ መደረስ እንደልተቻለ ገልጸዋል።

ከወራት በፊት በትግራይ ክልል የተከሰተው ግጭት አሁን ላይ እየተስፋፋ መሆኑን እና በርካታ ሰብአዊ ኪሳራዎች እያስከተለ መሆኑን ተናግረዋል።

በጦርነቱ ሳቢያ፦
- የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር በየእለቱ እያሻቀበ መሆኑን
- ከ2 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን ግጭቱን ተከትሎ መፈናቀላቸውን
- ከትግራይ ክልል በተጨማሪም ወደ አማራ እና አፋር ክልል በተስፋፋው ግጭት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን፤
- ከሰብአዊ ቀውስ በተጨማሪም የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየተጎዳ መሆኑን
- የበሀገሪቱ የብድር ጣራ እየጨመረ መሆኑን
- ሀገሪቱ እዳ የመክፈል አቅሟ እየተዳከመ መምጣቱን፣
- የኑሮ ውድነቱ በከፍተኛ ሁኔታ እያሸቀበ መምጣቱን ገልፀዋል።

ገተሬስ ፥ የኢትዮጵያ አንድነት እና የቀጠናው መረጋጋት ወሰሳኝ ናቸው ያሉ ሲሆን አሁን ላለው ሁኔታ ወታደራዊ መፍትሄ የለም ሲሉ ተናረዋል።

በጦርነቱ የተካፈሉ አካት በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም እንዲያድርጉ፣ የውጭ ሀገራት ሀይሎች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ፣ ለሰብአዊ ድጋች መተላለፊያ መንገዶች እንዲከፈቱ እና ችግሩን ለመቅረፍ #በኢትዮጵያ_የሚመራና ሁሉንም አካታች የሆነ ውይይት እንዲካሄድ ጥሪ አቅርበዋል።

#Al_AIN

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #Afar #Amhara " ለሰላም ተስፋ አለ " የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሀመድ ዛሬ ስለኢትዮጵያ ጉብኝታቸው መግለጫ ሰጥተዋል። በጦርነቱ የተጎዱትን ትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎችን ከጎበኙ በኋላ ለሰላም ተስፋ እንዳለ የገለጹ ሲሆን " በእርግጥ የሚስተዋለው ከጥቂት ወራት በፊት ከነበሩ ግጭቶች ያነሰ ነው " ብለዋል። ከትግራይ ክልል አመራሮች፣…
#USA , #NewYork📍

" በሰማሁት ታሪክ እንባዬን መቆጣጠር አቅቶኛል " - አሚና መሀመድ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ምክትል ሃላፊ አሚና መሃመድ የኢትዮጵያ ግጭት በሴቶች ላይ ባደረሰው ከባድ ጉዳት እጅጉን መደንገጣቸውን ገለጹ፡፡

ምክትል ዋና ጸሃፊዋ ይህንን ያሉት ለ5 ቀናት #በኢትዮጵያ
- በትግራይ ክልል
- አማራ ክልል
- አፋር ክልል
- ሶማሌ ክልል ያደረጉትን ጉብኝት በማስመለክት ትላንት በ #ኒውዮርክ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው፡፡

አሚና የትግራይ ክልል ግጭት ባስከተለውን አስከፊ መዘዝ የተጎዱቱን የኢትዮጵያ ሴቶች አግኝተው ማነጋገረቻውን እና በሰሙትም ታሪክ እንባቸው መቆጣጠር እንዳቃታቸው ገልጸዋል፡፡

አሚና ግጭት ባለባቸው የኢትዮጵያ ክልሎች ያሉት ሴቶች " ሊታሰብ የማይቻል አሰቃቂ አደጋ አጋጥሞቸዋል " ብለዋል።

በተለይ በጦርነቱ ወቅት አስገድዶ መድፈር የተፈጸመባቸውን ታሪክ ማድመጥ ኩፉኛ የሚያምና የሚያስለቅስ ጉዳት መሆኑን ገልፀዋል። " ኢትዮጵያውያን ሴቶች ሊታሰብ በማይቻል መልኩ ተጎድተዋል " ብለዋል አሚና መሐመድ።

በልጆቻቸው ፊት ከተደረፈሩት ባሻገር የደረሰባቸውን ጉዳት የማያስታውሱ ሴቶችን ጭምር ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

አሚና መሀመድ ፤ በትግራይ አንዲት በተደጋጋሚ በቡድን የተደፈረች፣ በዚህም ወንድ ልጅ የወለደችና አሁን ላይ የቤተሰቦቿንና ማህበረሰቡ አይን ማየት ተስኗት ራሷን አግላ የምትገኝ እንስት አግኝተው አሳዛኝ ታሪክ መስማታቸውን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የአብሮነት ጉዞ ነበር ያሉት አሚና " ተመድ በተለይ ለሴቶች እና ህጻናት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ማገገም አስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ ቅድሚያ መስጠቱን ይቀጥላል " ሲሉ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፅፈዋል።

በጦርነቱ ከተጎዱት ሴቶች ባሻገርም የኢትዮጵያን ጦርነት በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ፕሬዝዳንት እንዲሁም ደግሞ ከትግራይ ክልል መሪዎች ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን ተናግረዋል።

" ለተፈጸመው ግፍ ሁሉም ተጠያቂ ነው " ያሉት አሚና " አንድ አካል በሌላው ላይ እንዲህ ማድረጉ ፍጹም ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ ሴቶች ላይ ለተፈጸመው ሁሉ " ያለ ጥርጥር ፍትህ እና ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል።

ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች ሳይታረቁና ተጠያቂ ካልሆኑ ዘላቂ ሰላም ማምጣት እንደማይችል አስረግጠው ተናግረዋል።

(አል ዓይን ኒውስ)

@tikvahethiopia
#EFN

Ethio Fitness & Nutrition በውጤታማነታቸውና በፈጣን የሰውነት ለውጣቸዉ ተመራጭ የሆኑትን ኦርጅናሉን 100% ክሬቲን አቅርቧል።

ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👉https://publielectoral.lat/ethiofitnessnutrition

አድራሻ ፦ መገናኛ ከዘፍመሽ 200 ሜትር ወረድ ብሎ ግሬስ ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ

አገልግሎቱን ከመጠቀሞ በፊት በድርጅቱ የጥሪ ማእከል #የባለሞያ_ምክርን ያግኙ ፤ 9369

NB : ምርቱ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ ያለው #በኢትዮጵያ_ምግብና_መድኃኒት_ባለስልጣን ተመዝግቦ አስፈላጊውን ፍቃድ ያገኘ አስፈላጊውን ፍተሻ ያለፈ ነው።
#ኔዘርላንድ #አቶእሸቱ_ዓለሙ #ደርግ

በኔዘርላንድ የሚገኝ የይግባኝ ፍ/ቤት እ.አ.አ በ2017 ዓ.ም በጦር ወንጀለኝነት ጥፋተኛ የተባሉትን አቶ እሸቱ ዓለሙን የዕድሜ ልክ እስራት ባሳለፍነው ረቡዕ አጽንቷል።

የ67 ዓመቱ ተከሳሽ #በኢትዮጵያ በ1960 ዎቹ እና በ1970ዎቹ በነበረው ጨካኝ ኮሚኒስት ሥርዓት ወቅት የጦር ወንጀል ፈጽመዋል ሲል በደች የሚገኝ ፍ/ቤት የጥፋተኝነት ብይን ከ5 አመታት በፊት ሰጥቶ ነበር።

አቶ እሸቱ ዓለሙ የ2017 ፍርድ እንዲቀለበስላቸው ይግባኝ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም በሄግ የሚገኘው የይግባኝ ፍርድ ቤት ግን በ1960ዎቹ መጨረሻ እና በ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ በኢትዮጵያ በኮ/ሌ መንግሥቱ ኃ/ማሪያም አመራር በተፈጸመው የቀይ ሽብር ዘመቻ ተሳታፊ ነበሩ ሲል ውሳኔውን አጽንቷል።

አቶ እሸቱ በመታመማቸው ምክንያት በይግባኝ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ አልተገኙም ነበር።

የጉዳዩ ባለሞያዎች እንደሚሉት ከሆነ ወደ 150,000 የሚጠጉ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ምሑራንና የፖለቲካ ሰዎች በወቅቱ የነበረው ስርዓት ተቃዋሚዎቹን ለማጥፋት ባደረገው ዘመቻ በጭካኔ ተገድልዋል።

አቶ ዓለሙ እአአ በ1978 በጎጃም ክፍለ ሀገር የደርግ ተወካይ የነበሩ ሲሆን በወቅቱ ደርግ በክፍለ ሀገሩ ከተቃዋሚዎቹ አንዱ ከነበረው ከኢህአፓ ጋር ሲፋለም ነበር።

ፍርድ ቤቱ እንዳለው " በተከሳሹ እውቅናና ተሳትፎ " የጦር ወንጀል በክፍለ ሃገሩ ይፈጸም ነበር።

በመቶዎች የሚቆጠሩና አብዛኞቹ ወጣት ተማሪዎች የሆኑት ሰለባዎች ካለ በቂ ምክንያት ተይዘው ኢሰብአዊ በሆነ ሁኔታ የታሰሩ ነበር።

አንዳንዶች በከፋ ሁኔታ ሲደበደቡ አብዛኞቹ ደግሞ ካለ ፍርድ ሂደት ወደ እስር ቤት ይጋዙ ነበር። በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰለባዎች ደግሞ በሞት ተቀጥተዋል።

" የሞት ቅጣቱ በተከሳሹ አመራር ሰጪነት በጭካኔ ይፈጸም ነበር " ብሏል ፍ/ቤቱ።

አቶ ዓለሙ በ2017 የጥፋተኝነት ውሳኔ በተሰጠበት የፍርድ ሂደቱ መጀመሪያ ላይ በስሜት ተሞልተው ባደረጉት ንግግር በደርግ ላይ የቀረበውን ውንጀላ ተቀብለው ነገር ግን እርሳቸው በግላቸድ የፈፀሟቸው አለመሆናቸውን ለዳኞች ገልፀው ነበር።

አቶ ዓለሙ በደች ፍ/ቤት ጉዳያቸው ሊታይ የቻለው ከ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ጀምሮ ኔዘርላንድ ውስጥ መኖር በመጀመራቸውና በ1998 የሀገሪቱን ዜግነት በመቀበላቸው ነው።

#ASSOCIATED_PRESS | #VOA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ስለ #ኢትዮጵያ እና ታላላቅ ሀይቆች ቀጠና ምን አሉ ? ዛሬ ቃለ መሀላ የፈፀሙት የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ባደረጉት ንግግር በኢትዮጵያ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚያከናውኑትን ተግባር እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ሩቶ ፤ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ እና በታላላቅ ሐይቆች ቀጠና (ግሬት ሌክስ) ሰላም ለማምጣት…
#KENYA

አሜሪካ ያሰራጨችው ፅሁፍ ?

ከቀናት በፊት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የኬንያ ፕሬዜዳንት ሆነው ቃለመሀላ በፈፀሙ ወቅት ባሰሙት ንግግር የቀድሞ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ #በኢትዮጵያ እና በታላላቅ ሐይቆች ቀጠና (ግሬት ሌክስ) ሰላም ለማምጣት የሚያስመሰግን ተግባር ማከናወናቸውን ገልፀው እሳቸውም የተጀመሩ የሰላም ጥረቶች ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን አሳውቀው ነበር።

ሩቶ ፤ የቀድሞው ፕሬዝዳንት የጀመሩትን ሰላም የማምጣት ጥረት ለመቀጠል መስማማታቸውን እና የኬንያ ሕዝብን በመወከል የሰላም ንግግሮችን ለመምራት መስማማታቸውንም በዕለቱ ገልፀው ነበር።

ትላንት የአሜሪካ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባሰራጨው መልዕክት ኡሁሩ ኬንያታ በሰሜን ኢትዮጵያ እና በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ላለው ግጭት የሰላም ልዩ ልዑክ ሆነው መሾማቸውን በደስታ እንደምትቀበለው ገልፃለች።

አሁሩ በሰላም ልዩ ልዑክነት የተሾሙበት ወቅት ለሁለቱም ግጭቶች ወሳኝ በሆነ ጊዜ መሆኑን እና ስራቸውም ወሳኝ እንደሚሆን አሳውቃለች።

አሜሪካ ትላንት ባሰራጨችው መልዕክት ኡሁሩ ኬንያታን ማን እንደሾማቸው በግልፅ አለመፃፏን ተከትሎ በርካቶች ዘንድ ግርታን ፈጥሯል፤ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ምትክ የተሾሙ የመሰላቸውም አልጠፉም።

ግርታው አሜሪካ ያሰራጨችው መልዕክት ሙሉ ባለመሆኑ የተፈጠረ ሲሆን ኡሁሩ ኬንያታ የተሾሙት በሀገራቸው ኬንያ ፤ የኬንያን ህዝብ እና መንግስት ወክለው የተጀመሩ ሰላም ንግግሮችን እንዲቀጥሉ ነው እንጂ በአፍሪካ ህብረት ስር አይደለም።

የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦባሳንጆ አሁንም ስራ ላይ ናቸው፤ ከጥቂት ቀናት በፊት የኃላፊነት ጊዜያቸው እንደተራዘመላቸው መገለፁ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ በፕሪቶሪያ ፤ በኢትጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነትን በተመለከተ የወጣው የጋራ መግለጫ 12 ነጥብ የያዘ ነው። ከዚህም ስምምነት መካከል ፦ - የህወሓት ቡድን #ትጥቅ_እንዲፈታ ከስምምነት ተደርሷል። - የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ለማረጋገጥ እና የኢፌደሪ ሕገ-መንግሥቱን ለማስከበር የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ተስማምተዋል። …
#ETHIOPIA🇪🇹

#በኢትዮጵያ_መንግስት እና #በህወሓት መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ይዘት የሚገልፅ 12 ነጥብ ያለው #የጋራ_መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

ነገ ሁለት ዓመት የሚደፍነውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲበጅለትና ህዝቡም እረፍት እንዲያገኝ ፤ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ፣ አርሶ አደሮችም ወደ እርሻቸው ፣ ሰራተኞችም ወደ ስራቸው፣ ነጋዴዎችም ወደንግዳቸው እንዲመለሱ አጠቃላይ የቀደመው ሁኔታ እንዲፈጠር  ሁሉም አካል ዛሬ ወደ ተደረሰው " የሰላም ስምምነት " #ተፈፃሚነት እና #ተግባራዊነት ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

የአፍሪካ ህብረት ፤ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ የዛሬው ስምምነት በስኬት እንዲጓዝ እና ሰላም እንዲሰፍን  የስምምነቱ ትግበራ " ወሳኝ ይሆናል " ሲሉ ነው ያስገነዘቡት።

በዚሁ አጋጣሚ ለሰላም መስፈን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከሚጫወቱት ሚና ባለፈ በዚህ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ጥላቻ እና እርስ በእርስ መራራቅን ከሚሰብኩ ንግግሮች በመቆጠብ በሰላም ማስፈኑ የራሳቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው።

@tikvahethiopia
የካንሰር ህክምና . . . #በኢትዮጵያ

#ጥቁር_አንበሳ

የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፤ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት ወረፋ የሚጠብቁ መኖራቸውን አስታውቋል።

የሆስፒታሉ የካንሰር ሕክምና ማዕከል ክፍል ኃላፊ ኤዶም ሰይፉ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" የተለያዩ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠብቁ ከ2013 መጨረሻ፣ 2014 ዓ.ም. እና 2015 ዓ.ም. ወረፋ ያልደረሳቸው አሉ፡፡

ይሁን እንጂ በየዕለቱ የሚመጡ ድንገተኛ የካንሰር ታካሚዎች በመኖራቸው በቅድሚያ ለእነዚህ ታካሚዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ይደረጋል።

በሆስፒታሉ ቆይተው መታከም ይችላሉ ተብለው የተለዩት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ሕክምና ለማግኘት እየተጠባበቁ ያሉትን ለማስተናገድ ጥረት እየተደረገ ነው።

ለዚህ ወረፋ መብዛት ዋነኛ ምክንያት ብለው ያቀረቡት በሆስፒታሉ የሚገኘው መሣሪያ #አንድ ብቻ መሆኑን ነው።

በዚህ ዓመት ብቻ በተደረገው ማጣራት የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠበባቁ 5,000 ታካሚዎች ሲኖሩ፣ በማዕከሉ በቀን በአማካይ ከ300 በላይ ታካሚዎች ይስተናገዳሉ።

ከእነዚህ የካንሰር ታካሚዎች መካከል 70 በመቶ የጨረር ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ፣ ኬሞ ቴራፒ የሚያስፈልጋቸው የታካሚዎች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም ።

በማዕከሉ አገልግሎት ለማግኘት የ2014 ዓ.ም. እና በ2015 ዓ.ም. ሕክምና ለማግኘት የተመዘገቡ ደግሞ ከ10,000 በላይ ናቸው። "

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ_ስፔሻላይዝድ_ሆስፒታል

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክሊኒካል ኢንኮሎጂስት ዶ/ር አማረ የሺጥላ ምን አሉ ?

"  በሆስፒታሉ የሚሰጠው የካንሰር ሕክምና ኬሞ ቴራፒና ቀዶ ጥገና ነው።

የጨረር ሕክምና ለመጀመር የማሽን ተከላ ላይ እንገኛለን። 60 በመቶ የሚሆነው የካንሰር ታካሚ እስኪጠናቀቅ እየተጠባበቁ ነው።

በሆስፒታሉ ካንሰር ሕሙማን ሕክምና አንዱ የሆነው ኬሞ ቴራፒ ሕክምና ለማግኘት ወረፋ በዛ ከተባለ ከሳምንት አይበልጥም።

ይሁን እንጂ ለካንሰር ሕሙማን የሚሰጠው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለመጠባበቅ ከስድስት ወራት እስከ አንድ ዓመት ያስፈልጋል። "

#በሐሮሚያ_ዩኒቨርሲቲ_ሕይወት_ፋና_ሆስፒታል

በሐሮሚያ ዩኒቨርሲቲ ሕይወት ፋና ሆስፒታል በካንሰር ሕክምና ረዳት ፕሮፌሰር ሚካኤል ሻውል (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" በሆስፒታሉ የኬሞ ቴራፒና የጨረር ሕክምና ለካንሰር ሕሙማን እየተሰጠ ነው።

የጨረር ሕክምና ከተጀመረ ስድስት ወራት አስቆጥሯል ፤ የታካሚዎች መጠነ መጠበቅ ከሦስት ወራት አይበልጥም።

በሆስፒታሉ በዓመት እስከ 6000 የካንሰር ታካሚዎች ሕክምና ያገኛሉ። በተለይ ደግሞ ጨረር ሕክምና ከተጀመረ በኋላ የታካሚዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።

ሆስፒታሉ በምሥራቅ ኢትዮጵያ እስከ ቅርብ ጊዜያት ብቸኛው የካንሰር ሕክምና መስጫ በመሆኑ ከሶማሌላንድና ከሌሎች አገሮች እየመጡ አገልግሎት የሚያገኙ ነበሩ። "

Via Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia