TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NewsAlert

የሱዳን ጦርና ተቃዋሚዎች የሽግግር መንግስት ለመመስረት #ከስምምነት ደረሱ። ከአልበሽር መውደቅ በኃላ በአፍሪካ ህብረት እና #በኢትዮጵያ አደራዳሪነት በሱዳን ወታደራዊ አመራሮችና ተቃዋሚዎች መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ዛሬ ላይ ህገ መንግስታዊ ስምምነት በመድረስ ተቋጭቷል።

የአፍሪካ ህብረት እንዳስታወቀው ከሆነ ሁለቱ አካላት ሱዳንን አዲስ ህገ መንግስታዊ የሽግግር መንግስት አቋቁመው ወደ አዲስ ምሽራፍ ለማሻገር ተስማምተዋል።

የህብረቱ አደራዳሪ #ሞሐመድ_ሀሰን ለመገናኛ ብዙሃን እንዳሉት ከሁለቱም ወገን በስምምነቱ ዝርዝር አፈፃፀሞች ላይም ወይይቱን ለመቀጠል ተስማምተዋል። የሁለቱ ወገኖች ስምምነት ሰነድም የሽግግር መንግስቱና የመንግስት መዋቅሮች የስልጣን ግንኙነትና ክፍፍልንም ያማላከተ ነው ተብሏል።

ሱዳን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷ #ኦማር_አልበሽር በህዝባዊ ተቃውሞ ከስልጣን ከተወገዱ በኃላ ካለፈው ሚያዚያ ጀምሮ በከባድ ቀውስ ውስጥ ለመሰንበት ተገዳለች። ወታደራዊ ኃይሉና የተቃዋሚዎች ጎራ የሽግግር መንግስት መስርተው ወደፊት ለመራመድ ከስምመነት መድረሳቸውን ተከትሎ ሱዳናዊያን በዛሬው ዕለት በካርቱም አደባባዮች ወጥተው ደስታቸውን እየገለፁ መሆኑ ተዘግቧል።

ምንጭ፦ #አልጀዚራና #ቢቢሲ/#etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia