TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወገን! ሰከን ማለት ዋጋ አለው! #ሰላምን እስክታጣት ድረስ ምንም ላይስመስልህ ይችላል። ነገር ግን ሰላም አንዴ ከእጅህ ከወጣች የልጅ ልጅህን #ብትገብር እንኳን መልሰህ ላታገኛት ትችላለህ።

#ሶሪያ የቀደመው ገፅታዋን እና #አሁን ያለውን ገፅታዋን ከላይ ባለው ፎቶው ተመልከት። ያኔ በትንሽ በትልቁ አትባላም።

ሰላም ለኢትዮጵያ!
ተወያይተን ችግራችንን እንፍታ!
#ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወገን! ሰከን ማለት ዋጋ አለው! #ሰላምን እስክታጣት ድረስ ምንም ላይስመስልህ ይችላል። ነገር ግን ሰላም አንዴ ከእጅህ ከወጣች የልጅ ልጅህን #ብትገብር እንኳን መልሰህ ላታገኛት ትችላለህ።

#ሶሪያ የቀደመው ገፅታዋን እና #አሁን ያለውን ገፅታዋን ከላይ ባለው ፎቶው ተመልከት። ያኔ በትንሽ በትልቁ አትባላም።

ሰላም ለኢትዮጵያ!
ተወያይተን ችግራችንን እንፍታ!
#ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አረንጓዴ_አሻራ በሀገር ደረጃ እስካሁን በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ቀን 232 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ይህንን ያስታወቁት በወላይታ ሶዶ ከተማ ከአካባቢው የህብረተስብ ክፍሎች ጋር እየተወያዩ ባሉበት ወቅት ነው።

#አሁን በደረሰን መረጃ በማለት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት ከተተከሉት ችግኞች ውስጥ በኦሮሚያ 132 ሚሊዮን ፣ በደቡብ 45 ሚሊዮን፣ በትግራይ ስምንት ሚሊዮን 400ሺህ አማራ 38ሚሊዮን እና አዲስ አባባ ከሶስት ሚሊዮን በላይ የተከናወኑ ይገኙበታል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ዛሬ ጥዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ ለመትከል የታቀደው 200 ሚሊዮን ቢሆንም እስካሁን የተከናወነው ከዚህ በላይ መድረሱን ነው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ ለማወቅ የተቻለው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሁን

"የኢትዮጵያ ዳር ድንበር ያልተቋጨ የቤት ሥራ" በሚል ርዕስ በዶክተር በለጠ በላቸው ይሁን ተፅፎ በ "ኢትዮጵያ አካዳሚክ ፕሬስ" የታተመ መፅሐፍ በሂልተን ሆቴል የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ፣ ሙሁራን ፣ የሚዲያ ባለሞያዎችና የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት በመመረቅ ላይ ይገኛል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የመክፈቻና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት የተላለፈ ሲሆን በደንበር ጉዳዮች ዙርያ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች የሚመረምሩና የሚያጠኑ እንዲሁም በተግባር ስራ የሚሳተፉ ባለሞያዎች በመፅሐፉ ዙርያ ግመገማ ቀርቦ ውይይት በመከናዎን ላይ ይገኛል።

Via Bereket H.

@tikvahethiopia
#አሁን

በአሁን ሰዓት በቤንች ሸኮ ዞን የሠላምና ፀጥታ ኮማንድ ፖስት ወይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ በዞኑ የተገኘውን አንፃራዊ ሠላም በማጠናከር ዘላቂ ለማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ይመከርበታል ተብሏል።

ከቤንች ሸኮ ዞን ኮሚኒኬሽን ቢሮው ባገኘነው መረጃ በውይይቱ የሸኮ ፣ የጉራፈርዳ ፣ የደቡብ ቤንችና የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር አመራሮችና የሚመለከታቸው የፀጥታ ዘርፍ አካላት ተገኝተዋል።

@tikvahethiopia
#አሁን

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከህዝብ ተወካዮች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት በምክር ቤቱ ተገኝተዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል። አቶ ታገሰ ፥ ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች 632 የእጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቅረባቸውንና አብዛኛዎቹ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ልምድና ዕውቀት ያላቸው መሆኑን መገንዘብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ አዋጁ ለአፈ-ጉባኤውና ለአፈ…
#አሁን

በቅርቡ ለተሾሙ የሚሲዮን መሪዎች የተዘጋጀ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ በቅርቡ በተለያዩ ሀገራት ለተሾሙ የሚሲዮን መሪዎች እንዲሁም በዋናው መ/ቤት በተለያዩ የስራ ኃላፊነት ላይ ለተመደቡ የስራ ኃላፊዎች ያዘጋጀው ስልጠና ዛሬ መሰጠት መጀመሩን ገልጿል።

በቅርቡ ጄነራል ባጫ ደበሌ ፣ ጄነራል ሀሰን ኢብራሂም ፣ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ፣ አቶ ደሴ ዳልኬ እና አቶ ተፈራ ደርበውን ጨምሮ ሌሎችም ግለሰቦች የባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ሹመት እንደተሰጣቸው እንዲሁም ሌሎችም ግለሰቦች በአምባሳደርነት ሹመት እንደተሰጣቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የሥራ ፈጠራ ውድድር !

የ2ኛ ዙር " አሁን/Ahun " የዲጂታል አንተርፕነሮች የሀሳብ ማበልፀጊያ ፕሮግራም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (#UNDP) አጋዥነት ጀምሯል።

በመጀመሪያ ዙር ተካሂዶ በነበረው ውድድር አሸናፊዎችን ለሥራ ያበቃው ይኸው መርሃግብር #አሁን ሁለተኛ ዙር የሥራ ፈጠራ ውድድር በይፋ መጀመሩን ተነግሯል።

ፕሮግራሙ የ4 ወር የሀሳብ ማበልፀጊያ ድጋፍና የሥራ ማስጀመሪያ ሽልማት ያካትታል፡፡

አዳዲስ እና ችግር ፈቺ የሆኑ የዲጂታል የሥራ ሃሳብ ያላችሁ አመልካቾች በውድድሩ መሳተፍ ትችላላችሁ ተብሏል።

የማመልከቻ ቅጹን ለማግኘት ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ : https://enkopa.org/high-growth/ አለያም በመልዕክት ሳጥን ቁጥር 25534 ቅፁን ሞልቶ መላክ እንደሚቻል ተገልዬ።

ምዝገባው የሚጠናቀቀው ሐምሌ 24, 2014 ዓ/ም ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት የሀገር በቀልና የውጭ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር 60 ልዑካንን በመያዝ መቐለ ገብቷል። የጉዞው ወነኛ አላማዎች በትግራይ ያለው የሰብአዊ እና መልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም ፈተናዎችና ሁኔታዎች በክልሉ ካሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለመስማትና ለመረዳት ነው። የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በስፍራው ስለሚገኙ ሂደቱን እየተከታተሉ ያሳውቁናል።…
#አሁን

አሁን በመቐለ ከተማ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት ልዑክ ከትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ምክክር እያደረገ ይገኛል።

የትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ህብረት / ACSOT የቦርድ ሊቀመንበር እና የትግራይ ልማት ማህበር ዋና ዳይሬክተር ተስፋይ ገብረ እግዚያብሔር ውይይቱን ሲከፍቱ ከተናገሩት ፦

" ስለደርሰብን ስብራት ኣብዝተን በማውራት የምንቀይረው ብዙ ኣይኖርም።

በትንሹ ከተግባባን፣ በብዙ ከሰራን በመከራ ላይ ላለው ህዝባችን ልንደርስለት እንችላለን።

ሁኔታው ልትገነዘቡ የመጣቹህ እንግዶች፣ ትላንት ዕዱልን ኣጥታቹህ ሞራላዊና ህጋዊ ግዴታቹ ሳትወጡ ለቀራቹህ ሁሉ፣ ዛሬም ህዝባችን ስቃይ ኣለበቃም እና፣ ድምፃቹህ፣ እውቀታቹህ፣ ጉልበታቹህ ያስፈልገዋል እና

✓ መጠልያ ውስጥ ያሉት ወደ ቀያቸው፣ የተሰድዱትም ወደ ኣገራቸው

✓ ተማሪዎች ወደ ናፈቃቸው ትምህርታቸው፣ ሰራቶኞችም ወደ ስራቸው፣

✓ ህመምተኞች የሚፈልጉት መድሃኔት እንዲያገኙ፣ የተማላ የምግብ ኣቅርቦት እንዲኖር፤

✓ ነፃ የዜጎችና የሸቀጦች እንቅስቃሴ እንዲኖር፣ የባንክ ኣገልግሎት እንዲጀመር በፍፁም ቅንነት ድምፃቹ እንድታሰሙ፣ የምትችሉትን ሁሉ እንድትሰሩ በታላቅ ትህትና እጠይቃቸዋለሁኝ፣ ትችላላቹም። "

(ሙሉ ንግግራቸው ከላይ ተያይዟል)

Photo : Tikvah Family (Mekelle)

@tikvahethiopia
#EOTC #አሁን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ እየሰጠች ነው።

ቤተክርስቲያኗ ፤ ከሃያ (20) ዓመታት በላይ በጅማ የም ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን የሚያገለግሉት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ዛሬ በጅማ ዞን  ፖሊስ ታስረው መዋላቸውን ገልጻ ድርጊቱን በፅኑ አውግዛለች።

በአሁኑ ሰዓት ሊቀ ጳጳሱ #በግዳጅ ከጅማ እንዲወጡ መገዳቸውን እና ከሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያን የሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሐፊ ጋር ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ መሆናቸውን ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ፤ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ከክልል የተሰጠ ትዕዛዝ ነው በማለት በነገው እለት በጅማ የቅድስት ድንግል ማርያም ሕንጻ ቤተመቅደስ ቡራኬ ቤተክርስቲያን ሳያከናውኑ በፀጥታ ኃይሎች ወደ አዲስ አበባ  እንዲመለሱ የተገደዱት ብሏል።

በተጨማሪ ቤተክርስቲያኗ በሰጠችው መግለጫ " በሕገ ወጥ ከተሾሙ አባቶች መካከል ይቅርታ ጠይቀው የተመለሱትና ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታቸውን የተቀበለው መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋዘአብ አዱኛ ከመንበረ ፓትርያርክ ማረፊያ ተይዘው ወዳልታወቀ ሥፍራ ተወስደዋል " ስትል ገልፃለች።

በመግለጫው መንግሥት ሕግ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጠየቀች ሲሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ በሚገኙበት ግቢ አፈና መፈጸሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኦርቶዶክሳውያንን ያሳዘነ ነው ብላለች።

#Update : መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ታፍነው ከተወሰዱበት ተለቅቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አሁን

የኢፌዴሪ ብሄራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ከባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር የቀድሞ ተዋጊዎችን የመልሶ ማቋቋም ሂደት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በመቐለ እያካሄደ ይገኛል።

ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን / ድምፂ ወያነ

@tikvahethiopia
#አሁን

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው።

የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

እስካሁን ፦

- ከኦነግ ሸኔ፣
- ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣
- ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣
- ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣
- ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ስለተከለከሉ ዜጎች፣
- አርሶ አደሩ ምርቱን ለመሸጥ ከመቸገሩ ጋር በተያያዘ፣
- ወደ አዲስ አበባ ምርት እንዳይገባ ከመከልከሉ ጋር፣
- ከክልሎች የርስ በርስ መናበብ አለመቻል፣
- የሱዳን ወታደሮች ወረው የያዙትን የኢትዮጵያ መሬትና ያወደሟቸውን ንብረቶች የተመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

አሁንም የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን በማቅረብ ላይ ናቸው። 

#ኢፕድ

@tikvahethiopia