TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሀዋሳ እና አዲስ አበባ!!

ድምፃዊ #ቴዎድሮስ_ካሳሁን በአዲስ አበባ ስታዲየም #በነፃ የሙዚቃ ዝግጅቱን ለማቅረብ እየተዘጋጀ እንደሆነ ተሰምቷል። ለአዲስ አበባው ኮንሰርት ምንም አይነት ክፍያ እንደማይቀበል የተነገረ ሲሆን ለሙዚቃው ዝግጅት ከአዘጋጆቹ በተጨማሪ የተወሰነውን ወጪ እራሱ ይሸፍናልም ተብሏል። ህዝቡም ኮንሰርቱን በነፃ እንደሚታደምበት ነው የተገለፀው። ከአዲስ አበባው በአይነቱ የተለየ የሙዚቃ ዝግጅት በተጨማሪ ድምፃዊው #በሀዋሳ ከተማ የሙዚቃ ዝግጅት ለማቅረብ እቅድ እንዳለው ለመስማት ተችሏል። የሙዚቃ ዝግጅቶቹ መቼ ይካሄዳሉ?? የሚለው ግን የታወቀ ነገር የለም።

ምንጭ፦ ኢትዮፒካሊንክ የሬድዮ ዝግጅት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባውን በማካሄድ ላይ ነው። ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የድርጅትና የመንግስት የስራ አፈጻጸም እንዲሁም በሀገራችን ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ላይ ሲሆን አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። በ11ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈጻጸምም ይገመግማል። በስብሰባው በመስከረም ወር #በሀዋሳ በተካሄደው በ11ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የአጋር ፓርቲዎች ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሶሪያ ስደተኞች~ሃዋሳ‼️

በአሁኑ ወቅት #በሀዋሳ_ከተማ በልመና ስራ ተሰማርተው የሚገኙ ጥቂት የሶሪያ ዜጎች መኖራቸውን የኢሚግሬሽን የዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከጥር 19 እስከ 21 ለተከታታይ ሦስት ቀናት #በሀዋሳ_ከተማ ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ 4ኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበሩን በመምረጥ ተጠናቀቀ። በዚህም መሰረት ወጣት አስፋው ተክሌን በሠብሳቢነት እንዲሁም ወጣት አክሊሉ ታደሰን በምክትል ሰብሳቢነት መምረጡን የኢህአዴግ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvagethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 21/2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ መንግስት “የጤፍ ባለቤት ነኝ” ያለውን የሆላንድ ድርጀት በዓለም አቀፉ የግልግል ፍርድ ቤት ሊከስ ነው።
.
.
በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ሁለት አርሶ አደሮች በኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር "ኦነግ ታጣቂዎች" መገደላቸውንና አንድ አርሶ አደር መቁሰሉን የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር የሴፍቲና ሲኬዩሪቲ ዲፓርትመንት ባለሙያዎች በባቡሩ ላይ #ድንገተኛ የእሳት አደጋ ቢከሰት እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል የሚያሳይ ልምምድ አካሂደዋል።
.
.
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት የቀጠለውን የሚኒስትርና ተጠሪ መስሪያ ቤቶችን የ100 ቀን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መርተዋል።
.
.
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፓሬሽን/ሜቴክ/ይቅርታ መጠየቅና #እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ እንደሚያደርግ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #አህመድ_ሀምዛ አስታውቀዋል።
.
.
በሰቆጣ ከተማ ሦስት #ፓኪስታናውያን በሕገ ወጥ የሞባይል ሽያጭ ተሰማርተው እጅ ከፈንጅ ተይዘዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ሰርተፍኬት፣ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ፣ የልደትና ሞት ሰርተፍኬት እንዲሁም የጋብቻ እና ፍቺ ሰርተፍኬቶች በዲጂታል ሰርተፍኬት ሊቀየሩ ነው ተብሏል።
.
.
ኢ/ር #ታከለ_ኡማ ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የፈረሰውን መስጂድ በመጎብኘት የአከባቢውን የሙስሊም ማህበረሰብም አነጋግረዋል፡፡
.
.
#የፌዴራል_መንግሥት አመራሮች የድሬዳዋ ነዋሪዎችን በከተማዋ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ አወያይተዋል፡፡
.
.
በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና በማህበራዊ ፍትህ ላይ ያተኮረ የመጀመሪያውን አረንጓዴ የፖለቲካ ፓርቲ (Green Party) ለማቋቋም ጊዜያዊ አስተባባሪ ፓርቲ መሰየሙን ዋዜማ ራድዮ ዘግቧል።
.
.
ከሳውዲ አረቢያ ጋር በተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ መንገድ ለሚሄዱ ሰራተኞች የቪዛ አገልግሎት መሰጠት መጀመሩን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።
.
.
ግምታዊ ዋጋው 400 ሺህ ብር የሚያወጣ የባህርዛፍ አጠና ያለምንም ህጋዊ ሰነድ ከአገር ሊወጣ ሲል #በጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ከጥር 19 እስከ 21 ለተከታታይ ሦስት ቀናት #በሀዋሳ_ከተማ ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ 4ኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበሩን በመምረጥ ተጠናቋል።
.
.
ከጭናግሰን ከተማ የማርያምን ክብረ በዐል አክብረው ይመለሱ በነበሩ ምዕመናን ላይ ወጣቶች መንገድ መዝጋታቸውን ተከትሎ #በጅግጅጋ_ከተማ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት መረጋጋቱ ታውቋል። በግጭቱ የ2 ሰው ህይወት አልፏል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለተከታተሉበት የጎንደሩ ጻዲቁ ዮሐንስ 1ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የኮምፒዩተር ድጋፍ አድርገዋል፡፡
.
.
#በድሬዳዋ_ከተማ የትራንስፖርትና የግብይት #አድማ ለማድረግ ያቀዱ ነዋሪዎች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ #የምስራቅ_ዕዝ_ጠቅላይ_መምሪያ አስጠነቅቋል።
.
.
አቃቤ ሕግ የቀድሞ #የሜቴክ የስራ #ሀላፊዎች በነበሩት ሻለቃ #ክንደያ_ግርማይና ሌተናል ኮሎኔል #አሰፋ_ዮሐንስ ላይ ክስ መስርቷል።
.
.
የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) በዚህ ሳምንት ሐሙስ በይፋ ትጥቅ ይፈታል።
.
.
በቅርቡ በመንግስት እና ኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል በአምቦ በተደረገው ስምምነት መሠረት እርቁን ተግባራዊ ለማድረግ የተመረጠው የቴክኒክ ኮሚቴ ሥራውን በተግባር መጀመሩን የቴክኒክ ኮሚቴው አባል አቶ #ጀዋር_መሀመድ አስታውቀዋል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምናና የኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና ለሁለት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አድርገዋል።
.
.
#የኢፌዲሪ_አየር_ሃይል በሶማሊያ ከባይደዋ በስተምስራቅ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ቡርሃይቤ በተባለ የአልሻባብ ይዞታ ላይ ጥር 16 ቀን 2ዐ11 ዓ.ም ድብደባ በመፈፀም ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ ከተማ የተከሰተዉን #አለመረጋጋት ተከትሎ የከተማዉ ፖሊስ ኮሚሽን 308 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያካሄደ ነዉ፡፡

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ፣ etv፣ fbc፣ VOA፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት፣ የጠ/ሚ ፅ/ቤት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ አብመድ
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ🔝

በዛሬው ዕለት #የታክስ_ንቅናቄው አንድ አካል የሆነ ግማሽ ማራቶን የታላቁ ሩጫ #በሀዋሳ ከተማ ተካሄዷል፡፡

ፎቶ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደቡብ ክልል

በደቡብ ክልል እየተነሱ ያሉ #የአደረጃጀት ጥያቄዎችን በተመለከተ ሳይንሳዊ ጥናት ለማድረግ ዝግጅት ማጠናቀቁን ጥናቱን የሚያከናውነው ፎረም አስታወቀ።

ላለፉት ሶስት ወራት ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው ፎረሙ፤ በቀጣዮቹ አስር ቀናት መረጃ ሰብሳቢዎች ወደ ስራ ይገባሉ ብሏል።

ፎረሙ ጥናቱን ከአራት ወራት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለክልሉ መንግስት እንደሚያቀርብም ነው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ያስታወቀው።

ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች እና የሙያ መስኮች የተውጣጣ 20 አባላት ያለው የጥናት ቡድን፤ የጥናቱን አካሄድ በተለመከተ ንድፈ ሀሳብ አዘጋጅቷል። አለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ለማየት መሞከሩንም አንስቷል።

በዛሬው እለትም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተመለመሉ 22 የጥናቱ ሱፐርቫይዘሮች ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርጓል።

በቀጣዩ ሳምንትም #በሀዋሳ ከ150 የመረጃ ሰብሳቢዎች ጋር እንደሚመክር ነው በመግለጫው የተነሳው።

የጥናቱ ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅም ከሰው ሀይል ባሻገር #የሶፍትዌር ዝግጅት መደረጉን ፎረሙ የጥናትን መርህ እና አካሄድ ጠንቅቀው በሚያውቁ እስከ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ባላቸው የክልሉ ተወላጆች የሚደረገውን ጥናት ለክልሉ መንግስት እንደ ግብአት አቀርባለሁ ብሏል።

የጥናቱ ውጤት ውሳኔ ሰጪ ሳይሆን እንደ ምክረ ሀሳብ የሚቀርብ መሆኑንም ፎረሙ በመግለጫው አንስቷል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰልፉ በሰላም ተጠናቀል...

#በሀዋሳ_ከተማ ህገ መንግስታዊ #መብታችን ይከበር በሚል ሲደረግ የነበረው ሴቶች ብቻ የተሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ #በሰላም ተጠናቀዋል::

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሰላም ገብተዋል!

የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ወደተቋማቸው በሰላም ገብተዋል። በተመሳሳይ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ወደተቋማቸው በሰላም ገብተዋል። የወልቂጤው ልዕኩ በጉዞ ላይ ይገኛል።

ቅዳሜ እና እሁድ #በሀዋሳ_ዩኒቨርስቲ #የStopHateSpeech መድረክ መካሄዱ አይዘነጋም--ፎቶዎች እና ተያያዥ መረጃዎችን ቆየት ብዬ አቀርባለሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የወንደሰን አስክሬን ወደሀዋሳ እያመራ ነው...

ነቀምት ከተማ ተጫዋች የሆነው ወንድወሰን ዮሐንስ በትላንትናው ዕለት በነቀምቴ ከተማ በተነሳ ድንገተኛ #ግርግር በተተኮሰ ጥይት ህይወቱ አልፏል። ወንድወሰን ዮሐንስ ትውልድ እና እድገቱ #በሀዋሳ ኮረም ሰፈር አካባቢ ሲሆን በሀዋሳ ከተማ የተለያዩ የእድሜ እርከኖች ከተጫወተ በኋላ በስልጤ ወራቤ እና ኢትዮጵያ ውሀ ስራ (ኢኮስኮ) ሲጫወት ቆይቶ አሁን ወደሚገኝበት ነቀምት ከተማ አምርቶ እየተጫወተ የሚገኝ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ነበር። የተጫዋቹ አስከሬን ወደ ሀዋሳ እያመራ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በነገው ዕለትም በትውልድ ከተማው ሥርዓተ ቀብሩ ይፈፀማል ተብሎ ይጠበቃል።

Via SoccerEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኮማንድ_ፖስት

ሀምሌ 11 ቀን 2011 ዓም #በሲዳማ_ዞን እና #በሀዋሳ ከተማ የተከሰተውን የጸጥታ ችግር አስመልክቶ በክልሉ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት መደበኛውን የህግ ማስከበር ስርዓት ተከትሎ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ኮማንድ ፖስቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራትን አስመልክቶ ዛሬ በሀዋሳ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/CM-07-31
#Hawassa

ከሰሞኑ በሀዋሳ ከተማ የሚከሰተዉን የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት መቋረጥ ተከትሎ በርካቶች ስራችን ላይ እንቅፋት እየተፈጠረ ነው ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

እየተፈጠረ ላለው ችግር ኢትዮ ቴሌኮም አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ሲያስተካክለዉ ቢታይም አገልግሎቱ 24 ሰአት እንኳን ሳይቆይ መልሶ ሲቋረጥ ይስተዋላል።

በዚህም ተገልጋዮች ላልተገባ ወጭ እና እንግልት እየተዳረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም የደረሱትን ቅሬታዎች ይዞ የሚመለከተውን አካል አነጋግሯል።

በጉዳዩ ላይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው በኢትዮ ቴሎኮም ፤ የደቡብ ሪጅን ዳይሬክተሩ አቶ ጁነዲን አብዱልቃድር " ችግሩ መኖሩ ግልጽ ነው " በማለት አሁን ላይ እንዲህ ያለው የስርቆት ሁኔታ በሁሉም አካባቢ አሳሳቢ መሆኑን ያነሳሉ።

አቶ ጁነዲን አክለዉም ፤ ኬብሉ ከውጭ በውድ ገንዘብ ተገዝቶ  ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚውል በመሆኑ ችግሩን ለመቅረፍ ማህበረሰቡ ከፖሊስ ጋር ተጣምሮ ሊጠብቀው ይገባል ብለዋል።

በዚህ በኩል በሀዋሳም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች ትልቅ እንቅስቃሴ መኖሩን የገለፁት ደግሞ በሪጅኑ የህግ ጉዳይ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ተድላመድህን ቀለመወርቅ ፤ " እስካሁን በተደረጉ እንቅስቃሴዎችም በርካታ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

ስርቆቱ #በሀዋሳ እና #ሻሸመኔ ከፍ ያለ መሆኑን የሚገልጹት አቶ ተድላመድህን ካለፈዉ ሀምሌ 1 እስከ ታህሳስ 30 እንኳን በሀዋሳ ከተማ ብቻ 4 መዝገብ ላይ ውሳኔ ተሰጥቶ ከስድስት እስከ ሁለት አመት እስራት መፈረዱን አንስተዋል።

በሀገር ደረጃ  የመሰረተልማት እንቅስቃሴዎችን ለመጠበቅ ታስቦ የወጣዉን 464/67 የተባለ አዋጅ መሰረት አድርጎ ያለመክሰስ ያለመመርመርና ውሳኔ አለመስጠት ችግር ፈተና እንደሆነባቸው ገልጸዋል።

የሚሰጡ ውሳኔዎች እስከ 20 አመት የሚዘልቁ ቢሆኑም ያ እየሆነ አለመሆኑን የሚገልጹት ስራ አስኪያጁ " በዚህ ቻሌንጅ ውስጥ ሆነንም ቢሆን አስተማሪ የሆኑ ውሳኔዎች እንዲሰጡ እየሰራን ነው "  ብለዋል።

መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በሀዋሳዉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia