ደቡብ ክልል

በደቡብ ክልል እየተነሱ ያሉ #የአደረጃጀት ጥያቄዎችን በተመለከተ ሳይንሳዊ ጥናት ለማድረግ ዝግጅት ማጠናቀቁን ጥናቱን የሚያከናውነው ፎረም አስታወቀ።

ላለፉት ሶስት ወራት ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው ፎረሙ፤ በቀጣዮቹ አስር ቀናት መረጃ ሰብሳቢዎች ወደ ስራ ይገባሉ ብሏል።

ፎረሙ ጥናቱን ከአራት ወራት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለክልሉ መንግስት እንደሚያቀርብም ነው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ያስታወቀው።

ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች እና የሙያ መስኮች የተውጣጣ 20 አባላት ያለው የጥናት ቡድን፤ የጥናቱን አካሄድ በተለመከተ ንድፈ ሀሳብ አዘጋጅቷል። አለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ለማየት መሞከሩንም አንስቷል።

በዛሬው እለትም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተመለመሉ 22 የጥናቱ ሱፐርቫይዘሮች ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርጓል።

በቀጣዩ ሳምንትም #በሀዋሳ ከ150 የመረጃ ሰብሳቢዎች ጋር እንደሚመክር ነው በመግለጫው የተነሳው።

የጥናቱ ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅም ከሰው ሀይል ባሻገር #የሶፍትዌር ዝግጅት መደረጉን ፎረሙ የጥናትን መርህ እና አካሄድ ጠንቅቀው በሚያውቁ እስከ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ባላቸው የክልሉ ተወላጆች የሚደረገውን ጥናት ለክልሉ መንግስት እንደ ግብአት አቀርባለሁ ብሏል።

የጥናቱ ውጤት ውሳኔ ሰጪ ሳይሆን እንደ ምክረ ሀሳብ የሚቀርብ መሆኑንም ፎረሙ በመግለጫው አንስቷል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia