TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሸዋሮቢት‼️

በሸዋሮቢት ከተማ የተከሰተው አለመረጋጋት ከተፈጸመው #አሰቃቂ_ግደያ ጋር ተያይዞ ማህበረሰቡ ብሶቱን ለመግለጽ እንጂ ከየትኛውም #የፖለቲካ ጉዳይ ጋር የተያያዘ አለመሆኑን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ኢ/ር #ሞገስ_ባየህ ለአማራ ብሁሃን መገናኛ ለ91.4FM በስልክ በሰጠው መግለጫ አስታውቀዋል።

የከተማው ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ለ91.4 FM እንዳገለጹት #ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውሏል አስፈላጊውን የምርመራ ስራ ተሰርቶና ተጣርቶ ህጋዊ #እርምጃ እንዲወሰድ ይደረጋል ውጤቱንም ለህዝብ እናሳውቃለን ህብረተሰቡ ከስሜታዊነት ወጥቶ በተረጋጋ መንግድ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጠይቀዋል።

እንደ ሀላፊው ገለጻ ከአካባቢው የሀይማኖት አባቶች፣ ሀገር ሽማግሌዎች እና ከከተማው ህብረተሰብ ጋር በመከካከር ወደ ነበረበት ሰላም ለመመለስ የምክክር ስራ ይሰራል ብለዋል። አሁን ከህብረተሰቡ የሚጠበቀው በሰላም ወደ እየቤቱ መመለስ እንዳለበት የተዘጉ መንገዶችን ከፍቶ መንገደኞችን #መሸኘት እንደለበት አሳስበው ድርጊቱ ግን ብሶትን /ቁጭትን/ ለመግለጽ እንጂ #የፖለቲካ_አጀንዳ እንደሌለው ሀላፊው ተናግረዋል። የጸጥታ ሀይሉም ጉዳዩ በህግና በህግ እንዲያልቅ የማረጋጋት ስራ እየሰራ ነው።

Via Shewa Robit City Administration Kentiba office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሸዋሮቢት ከተማ ፖሊስ‼️

ትላንት በሸዋሮቢት ከተማ ተፈጥሮ የነበረው #አለመረጋጋት ሙሉ በሙሉ ተወግዶ ዛሬ ሸዋሮቢት ወደነበረው ሰላሟ ተመልሳ ማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ መሆኑን #የሸዋሮቢት_ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ የጽ/ቤቱ ኃላፊ ኢንስፔክተር #ሞገስ_ባየህ እንደገለፁት ማህበረሰቡ በአሁን ሰአት በተሰማራበት የስራ መስክ በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጠቅሰው በከተማው አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ሙሉ በሙሉ በስራ ላይ ናቸው ብለዋል፡፡ #ከጉዳት_መጠን ጋር ተያይዞ #የሚናፈሱ አሉባልታዎች መሰረተ-ቢስ ናቸው በሰው ህይወት ላይም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት #የለም ስለዚህ ማህበረሰቡ ከአሉባልታ በፀዳ መንገድ የተለመደ ተግባሩን ማከናወን እንዳለበት ፖሊስ አስታውቀዋል፡፡

Via Shewa Robit City Administration Kentiba office
@tsegabwolde @tikvahethiopia