TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ከሁለት ሺ በላይ ምሁራንን የሚያሳትፈው የመጀመሪያው የአማራ ክልል የምሁራን መማክርት ጉባኤ በባህር ዳር ከመስከረም 9 እስከ 10 እንደሚካሄድ ተገለፀ፡፡ የመማክርት ጉባኤው በክልሉ እና በአገሪቷ በሚታዩ #ማህበራዊ#ፖለቲካዊና #የኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሳይንሳዊ ጥናቶችን በማቅረብ ተወያይቶ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጋምቤላ . . . ኦሮሚያ

" በአካባቢው #ሰላም አስፍኛለሁ " - የሀገር መከላከያ ሰራዊት

ይህ ከጋምቤላ ወደ ሸበል ደንቢዶሎ የሚወስደው መንገድ ላለፉት 3 ዓመታት በፀጥታ ችግር ተዘግቶ ቆይቷል።

በዚህም ምክንያት ፤ ዜጎች ከፍተኛ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ችግር ሲገጥማቸው ነበር።

አሁን ላይ ግን ሀገር መከለከያ ሰራዊት መንገዱ ለኅብረተሰቡ አገለግሎት መስጠት እንዲችል የሰላም ማስከበር በመስራት መንገዱ እንዲከፈት ማድረጉን አሳውቋል።

የሀገር መከላከያ ሠራዊት " በቀጠናው የተሰጠኝን የሰላም ማስከበር ግዳጅ በአግባቡ በመወጣት በአካባቢው ሰላም አስፍኛለሁ " ብሏል።

ማኅበረሰቡ በስፋት የሚገናኝበት እንዲሁም የገበያ ትሥሥሩን የሚያጠናክርበት መንገድ ዳግም በሰላም መደፍረስ እንዳይዘጋ የመንግሥት ኃላፊዎች ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የመከላከያ ሰራዊቱ አስገንዝቧል።

በዚህ ቀጠና ባለፉት 3 ዓመታት በነበረው ግጭት ሕዝቡ ክፉኛ የተጎዳ ሲሆን በተለይ የመንገዱ መዘጋት በሕዝቡ  #የኢኮኖሚያዊ እና #ማኅበራዊ ሕይወት ላይ ከፍተኛ ቀውስ አስከትሏል።

#GambellaPressSecretariat

@tikvahethiopia