TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BREAKING

" ከፓርቲው ፕሬዝዳንት (የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ) ጀምሮ ወደ ግንባር ሄደን እኛ መስእዋት ሆነን ኢትዮጵያን ለማዳን ወስነናል " - ዶ/ር አለሙ ስሜ

የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክሮ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ኢትዮጵያ በአሁን ሰዓት በውስጥም በውጭም የተከፈተባት ጥቃት የተቀናጀ መሆኑን ገልጾ፤ ሽብረተኛ ተብሎ የተፈረጀው ህወሓትና ግብረአበሮቹ በኢትዮጵያ እስካሁን ለደረሰው ጥፋት ተጠያቂ ናቸው፤ ተጠያቂነቱም ይረጋገጣል ብሏል።

ውጊያው አሁን ካለው የበለጠ ኪሳራ እንዳያደርስ ከነገ ጀምሮ ሁሉም የፀጥታ አካላት ወደተለየ እርምጃ እንደሚሸጋገሩ ተገልጿል።

ዶ/ር አብርሃም በላይ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ፥ " መከላከያ ሰራዊት እና ሌሎች የፀጥታ አካላት በቅንጅት ተዘጋጅተው ወደተለየ እርምጃ ይገባሉ ፤ ይህ ምንም ጥያቄ የለውም፤ ለውጥ ይኖራል " ብለዋል።

በተጨማሪ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በስብሰባው ላይ ከዚህ በኃላ ሁሉም አመራር በየጦር ግንባር እየተገኘ የህልውና አደጋውን ለመቀልበስ ከፊት ሆኖ እንደሚሰለፍ አሳውቋል።

ዶክተር አለሙ ስሜ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል፥ " የብልፅግና ስራ አስፈፃሚ ከፓርቲያችን ፕሬዜዳንት (ከሀገሪቱ ጠ/ሚኒስትር) ጀምሮ ወደ ግንባር መግባት እንዳለብን በእርግጥ ሌሎች ስራዎች እንዳይስተጓጎሉ የተወሰነ የልማቱን ስራ ፣ የዲፕሎማሲውን ስራ፣ ከቢሮ የሚሰራውን ስራ እንድንሰራ ሌሎች ከዚህ ውጭ ያለን ከፓርቲያችን ፕሬዜዳንት ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ ወደ ግንባር ሄደን እኛ መስእዋት ሆነን ኢትዮጵያን ለማዳን ወስነናል፤ ይሄንንም በተግባር ከነገ ጀምሮ በመንቀሳቀስ የምናሳየው ይሆናል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#BREAKING

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከነገ ጀምሮ ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ አሳወቁ።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ዛሬ ምሽት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰራጩት ፅሁፍ ኢትዮጵያ አሁን እያደረገችው ያለው ትግል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ትግል ነው ብለዋል።

"ትግሉ ልጆቻችን ሀገር እንዲኖራቸው የሚደረግ ትግል ነው። ልጆቻችን ክብርና ነጻነትን ለብሰው፣ በዓለም አደባባይ በኩራት ቀና ብለው እንዲሄዱ የሚደረግ ትግል ነው፤ በዓለም ላይ በክብር የምንጠራበት ስም እንዲኖረን የሚደረግ ትግል ነው። መኖር ወይም አለመኖራችንን የሚወስን ትግል ነው። ያለ ጥርጥር ግን እናሸንፋለን። ኢትዮጵያን ጠርቶ መሸነፍ ፈጽሞ የማይታሰብ ነው" ነው ሲሉ ገልፀዋል።

"ጊዜው ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት የሚያስፈልግበት ጊዜ ነው" ያሉት ዶ/ር ዐቢይ፥ " ከእንግዲህ እኔ መከላከያን በግንባር ሆኜ ለመምራት ከነገ ጅምሮ ወደ ትግሉ ሜዳ እዘምታለሁ። ታሪክ ከሚያደንቃቸው የኢትዮጵያ ልጆች አንዱ ለመሆን የምታስቡ ሁሉ ለሀገራችሁ ስትሉ ዛሬውኑ ተነሡ፤ ግንባር ላይ እንገናኝ" ብለዋል።

ዶ/ር ዐቢይ፥ "የእኛ መዝመት የሚፈጥረውን ክፍተት ከግንባር የቀሩት በሙሉ ዐቅማቸው ሸፍነው ይሠራሉ" ያሉ ሲሆን "በግንባር ያልተሰለፉ የክልልና የፌደራል አመራሮች ከመቼውም ጊዜ በላይ የልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሙሉ ዐቅማቸው ይከውናሉ" ብለዋል።

"ጎልማሶች በዘዴና በብልሃት አካባቢያቸውን እየጠበቁ፣ አረጋውያን እናትና አባቶች በጸሎት እየተጉ፣ ሁሉም ሰው ተባብሮ የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያረጋግጣል" ያሉት ዶ/ር ዐቢይ "ከዚህ በኋላ በሩቁ ተቀምጠን ተቺና አራሚ የምንሆንበት ጊዜ አይደለም። መደረግ ያለበትን እኛው ራሳችን እናድርገው። ለኢትዮጵያ ከእኛ በላይ ከየትም አይመጣም" ሲሉ ገልፀዋል።

* ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
#BREAKING

ኢትዮጵያ 4 የአየርላንድ ዲፕሎማቶችን አባረረች።

ዲፕሎማቶቹ አዲስ አበባ አየርላንድ ኤምባሲ ይሰሩ የነበሩ ሲሆን ኢትዮጵያን በሳምንት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ መወሰኗን ኢትዮጵያ አስታውቃለች፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለአል ዓይን በሰጡት ቃል፥ " በኢትዮጵያ ይሰሩ የነበሩ አራት የአየርላንድ ዲፕሎማቶች በሳምንት ውስጥ ሃገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ተወስኗል " ብለዋል።

ምንጭ፦ አል ዓይን

@tikvahethiopia
#Breaking

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ካሳጊታ መያዙን እንዲሁም ዛሬ ደግሞ ጭፍራ እና ቡርቃ እንደሚያዙ ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ በግንባር ሆነው ለኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) በሰጡት ቃል ነው።

በቴሌቪዥን ጣቢያው የተላለፈው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የቪድዮ መግለጫ በግንባር ሆነው ሰራዊቱን ሲመሩ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#BREAKING

ብሔራዊ ባንክ የብድር ክልከላውን ሙሉ በሙሉ አነሳ።

ለባለፉት አራት ወራት ተግባራዊ የነበረው የብድር ክልከላ ሙሉ በሙሉ መነሳቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ አስታወቀ።

ብሔራዊ ባንክ ባንኮች ብድር አገልግሎት ለሁሉም ደንበኞቻቸው እንዲሰጡ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ክልከላው የተጣለው "የኢኮኖሚ አሻጥርን" ለመከላከል እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ተግባራዊ ተድርጎ የነበረው በትይዩ እና በህጋዊ የውጭ ምንዛሬ ግብይት ላይ ያለው ልዩነት መስፋቱን ተከትሎ ነበር።

ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ

@tikvahethiopia
#BREAKING

የሱዳን ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ ስልጣን ሊለቁ ነው።

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ በሚቀጥሉት ሰዓታት ውስጥ ስልጣን ለመልቀቅ እንዳሰቡ ለፖለቲከኞች ቡድን መናገራቸውን ሮይተርስ ለሃምዶክ ቅርብ ከሆኑ ሁለት ምንጮች መስማቱን ዘግቧል።

ቡድኑ በቦታቸው ላይ እንዲቆዩ ቢጣይቃቸውም እሳቸውን ግን ስልጣናቸውን እንደሚለቁ ነግረዋቸዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር አብደላ ሀምዶክ በጥቅምት ወር በሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን በሚመራው ጦር መፈንቅለ መንግስት ተደርጎባቸው ለቁም እስር መዳረጋቸው በኃላም በተደረገ ስምምነት ከሳምንታት በፊት ወደ ስልጣናቸው መመለሳቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ ስልጣን ሊለቁ ነው ? የቱርክ መንግስት ዜና ወኪል የሆነው አናዶሉ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣን ሊለቁ መሆኑን ዘግቧል። የዜና ወኪሉ መረጃውን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት ዛሬ መስማቱን ገልጿል። ለሚዲያ ማብራሪያ መስጠት ያልተፈቀደላቸው አንድ ምንጭ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዳላ ሀምዶክ የቢሮ ሰራተኞቻቸውን አደራ እንዲያስረክቡ ማዘዛቸውን ፤ ሰራተኞቹም ይህን ከእሁድ ማታ ጀምሮ መተግበር…
#BREAKING

ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ ስልጣን ለቀቁ።

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሃምዶክ ስልጣን መልቀቃቸውን በይፋ አሳውቀዋል።

አብደላ ሀምዶክ ከጦር ኃይሉ ጋር በተደረገው የፖለቲካ ስምምነት ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣናቸው ከተመለሱ ከ6 ሳምንታት በኋላ ነው ስልጣናቸውን በገዛ ፍቃዳቸው የለቀቁት።

ከጥቂት ቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን ሊለቁ መሆኑን የቱርክ መንግስት ዜና ወኪል የሆነው አናዶሉ ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ምንጭ መስማቱን መዘገቡ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#BREAKING

የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ከእስር መፈታታቸውን ፓርቲው አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#BREAKING

ከእስር በምሕረት እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ፦

1. አቶ ስብሐት ነጋ

2. ወ/ሮ ቅዱሳን ነጋ

3. አቶ ዓባይ ወልዱ

4. አቶ አባዲ ዘሙ

5. ወ/ሮ ሙሉ ገብረ እግዚአብሔር

6. አቶ ኪሮስ ሐጎስ

7. አቶ ጃዋር መሐመድና በእርሳቸው መዝገብ የተከሰሱ ሁሉ

8. አቶ እስክንድር ነጋና በእርሳቸው መዝገብ የተከሰሱ ሁሉ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING በመላ ሀገሪቱ ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ያሳለፈው ውሳኔ ከዛሬ ጀምሮ ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን በ48 ሰዓታት ውስጥ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይፀድቃል። @tikvahethiopia
#BREAKING

የጠ/ሚኒስትር ፅ/ቤት ፦

" የሚኒስትሮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የሃገር ህልውና እና ሉዐላዊነት ላይ የተደቀነን አደጋ ለመከላከል የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 5/2014 ቀሪ የሚሆንበትን ጊዜ በሚመለከት በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

ሕውሃት እና ግብረአበሮቹ በሃገራችን ህልውና እና ሉአላዊነት ላይ ከፍተኛ አደጋ የደቀኑ በመሆኑ እና ይህን አደጋ በመደበኛው የህግ ማስከበር ስራ መከላከል የማይቻል ሆኖ በመገኘቱ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2014 የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 5/2014ን ያወጀ ሲሆን፣ ይህ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ በአዋጅ ቁጥር 1264/2014 ፀድቆ በስራ ላይ የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ሆኖም ግን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማውጣት የግድ አስፈላጊ እንዲሆን አድርጎ የነበረው ሁኔታ የተቀየረ በመሆኑ እና ስጋቱን በመደበኛው የሕግ ማስከበር ስራ መከላከልና መቆጣጠር የሚቻልበት ደረጃ ላይ በመደረሱ ለስድስት ወራት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ ማሳጠር አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

በመሆኑም በአዋጅ ቁጥር 1264/2014 አንቀጽ 11(2) በተደነገገው መሰረት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስድስት ወራት የጊዜ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መታወጅ ምክንያት የሆኑ ሁኔታዎች ከተቀየሩ እና በመደበኛው የሕግ ማስከበር ስርዓት ሊከሰቱ የሚችሉ ጉዳዮችን መቆጣጠር ይቻላል ብሎ ካመነ የስድስት ወር ጊዜው ሳይጠናቀቅ ጊዜውን የማሳጠር ስልጣን ያለው በመሆኑ የአዋጁን ተፈጻሚነት ቀሪ እንዲያደርገው የሚጠይቅ የውሳኔ ሃሳብ ቀርቦ በውሳኔ ሃሳቡ ላይ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በጥልቀት ተወያይቶ በማጽደቅ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡ "

@tikvahethiopia