TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳሳቢ ጉዳይ‼️

የአደንዛዥ እፅ ተጠቃሚ ተማሪዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ #እየጨመረ መምጣቱ ተገለፀ።

ባለፉት ዓመታት በተለይ የአደንዛዥ እፅ ተጠቃሚ የከፍተኛ ትምህረት ተቋማት ተማሪዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ተገለፀ፡፡

የኢትዮጵያ የፋርማሲ ባለሙያዎች ማህበር የተመሰረተበትን 44ተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ዛሬ በጎንደር ከተማ ውይይት አድርጓል፡፡

‘የአደንዛዥ እፅ ተጠቃሚዎች ቁጥር መጨመርና የፋርማሲስቶች ሚና’ በሚል መሪ ቃል ነው ውይይቱ የተደረገው፡፡

በውይይቱ ላይ እንደተገለፀው ባለፉት ዓመታት በተለይ የአደንዛዥ እፅ ተጠቃሚ የከፍተኛ ትምህረት ተቋማት ተማሪዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ይህም ችግሩን እጅግ አሳሳቢ አድርጎታል፡፡

ውይይቱም ይህንን ቁጥር ከመቀነስና ወጣቱን አምራች ዜጋ ከማድረግ አኳያ የፋርማሲ ባለሙያዎች የሚጠበቅባቸውን ሚና መርምሯል፡፡

የአልኮል፣ የሲጋራ፣ የጫትና የአደንዛዥ እፅ ተጠቃሚነት በዓለም እና አገር አቀፍ ደረጃ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝም በውይይቱ ተዳሷል፡፡

በውይይቱ ወቅት እንደተገለፀው በኢትዮጵያ የተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል:: ለዚህ ደግሞ እንደዋነኛ ምክንያ የተጠቀሱት የአቻ ግፊትና የፖሊሲ መላላት ናቸው፡፡

መንግስት የሚያደርገው ቁጥጥር አነስተኛ መሆኑ የአደንዛዥ እፅ ተጠቃሚዎች ቁጥር እንዲጨምር አስተዋፅኦ አድርጓል። የግለኝነት መስፋፋት ወይም የማህበራዊ ግንኙነት መላላትም በተመሳሳይ ችግሩን አባብሶታል ነው የተባለው፡፡

በፊልምና በድራማ የሚሳተፉ ታዋቂ ግለሰቦችና አማላይ የመጠጥ ማስታወቂያዎችም የሚፈጥሩት ተፅዕኖም በቀላሉ የሚታይ አይደለም
ነው የተባለው፡፡

የችግሩ መፍትሄም በመንስዔነት የተዘረዘሩትን አስቻይ ሁኔታዎች ማስወገድ መሆኑ ነው የተጠቆመው፡፡

የኢትዮጵያ የፋርማሲ ባለሙያዎች ማሀበር በአሁኑ ወቅት ከ1ሺህ በላይ የሚሆኑ አባላት ያሉት ሲሆን የተመሰረተው የዛሬ 44 ዓመት ህዳር
25/1967 ዓም ነው፡፡ ውይይቱ በሁለት ከተሞች ጎንደርና መቀሌ ላይ በተመሳሳይ ሰዓት ተካሂዷል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኢትዮጵያ በመንገድ ላይ የሚደርሰው የትራፊክ አደጋ ከመቀነስ ይልቅ ከጊዜ ወደ ጊዜ #እየጨመረ መምጣቱን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ በብሔራዊ የመንገድ ደህንነት ምክር ቤት 5ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ተገኝተው እንደገለፁት፤ በሀገሪቱ የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአሳሳቢ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል፡፡

Via~EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

የውጭ አገራት የጉዞ ታሪክ ሳይኖራቸው የኮሮና ቫይረስ የሚገኝባቸው ሰዎች ቁጥር #እየጨመረ መሆኑ ተጠቆመ!

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ #ለኢዜአ እንደተናገሩት ፤ ኅብረተሰቡ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር "አነስተኛ ነው" በማለት እየተዘናጋ ነው።

የውጭ አገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸውና ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ሳይኖራቸው በቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር በመጨመሩ መዘናጋት አይገባም ብለዋል።

በጎረቤት አገራት በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ ሆኑንም ገልጸው ይህም ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል።

ሳይንሳዊ ምርምሮችም የቫይረሱ ስርጭት ሊጨምር እንደሚችል እያሳዩ መሆኑን ጠቁመው ኅብረተሰቡ ሳይዘናጋ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ምክራቸውን ለግሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLaiTadesse

ኅብረተሰቡ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር #እየጨመረ መምጣቱን ከግምት በማስገባት አሁንም የሚያደርገውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ዶክተር ሊያ ታደሰ አሳሰቡ።

ባለፉት 24 ሠዓታት ብቻ 17 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ያሳዘናቸው የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ፤ ''በዚህም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር አስመዝግባለች'' ብለዋል።

እስከሁን የተመዘገቡትና የተገለጹት ቁጥሮች ትክክለኛ አሃዝ እንደማያሳይ ገልጸው ፤ "የምናውቀው የመረመርነውን ብቻ ነው፣ የመረመርነው ደግሞ ትንሽ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

ስለዚህ ወረርሽኙን መርሳትና መዘናጋት እንደማይገባ እና ኅብረተሰቡም ቁጥሩ "ያነሰው በሽታው እኛ ጋር ስላልመጣ ወይንም ስለማይመጣ" እንዳልሆነ ሊገነዘብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በኬንያ እና በሱዳን በመጀመሪያዎቹ ቀናት ትንሽ ቁጥር ማስመዝገባቸውን ተከትሎ መዘነጋት መታየቱን አስታውሰው ፤ ''ዋጋ አስከፍሏቸዋል'' ብለዋል።

ሕዝቡም ከጎረቤት አገሮች መዘናጋት ትልቅ ችግር ሊያመጣ እንደሚችል በመማር የሚደረጉትን ጥንቃቄዎች ማጠናከር እንደሚገባም አሳስበዋል።

"ትክክልኛ ትምህርትና እርምጃ ለመውሰድ ፣ በብዙ ቁጥር መያዝ ፣ በብዙ ቁጥር መሞት የለብንም" ያሉት ሚኒስትሯ ፤ ያለው #ብቸኛ አማራጭ #መጠንቀቅ በመሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#DrLiaTadesse

ኮሮና ቫይረስ ሁሉንም የእድሜ ክልል ነው የሚያጠቃው!

(በዶክተር ሊያ ታደሰ - የጤና ሚኒስትር)

በሀገራችን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎችን የእድሜ ስብጥር ብንመለከት እስካሁን በቫይረሱ ከተያዙት 272 ሰዎች ከህፃናት እስከ አረጋዊያን ድረስ በሁሉም የእድሜ ክልል ያሉ ተይዘዋል።

ትልቁ ቁጥር 99 ሰዎች ከ15-24 የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ናቸው ፤ ከዛ የሚቀጥለው ከ25-34 የእድሜ ክልል ውስጥ (75 ሰዎች) የሚገኙ ሲሆን ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ ሰዎች ቁጥርም 19 ነው። በህፃናት ላይ አነስተኛ ቁጥር ቢታይም ህፃናትም በሽታው እንደሚይዛቸው ያሳያል።

ይህ በሽታ የማያጠቃው የእድሜ ክልል የለም። በዓለም አቀፍ ደረጃ #ወጣቶች አይጠቁም የሚል #የተሳሳተ ግንዛቤ አለ ፤ በተለይ በእኛ ሀገር ያለው ስርጭት ትልቁ ቁጥር በወጣቶች ላይ የታየ ነው። ስለዚህ እያንዳንዳችን የምንወስደው ጥንቃቄ እጅግ አስፈላጊ ነው።

የዚህ በሽታ ስርጭት #እየጨመረ የሚሄድ ሊሆን ቢችልም ምን ያህል ይጨምራል የሚለውን የምንወስነው በየዕለቱ በምንወስናቸው ውሳኔዎች ፣ በየዕለቱ በምንመርጣቸው ምርጫዎች እንዲሁም በምንወስዳቸው እርምጃዎች ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ATTENTION

በአዲስ አበባ የኮቪድ-19 ስርጭት በእጅጉ #እየጨመረ ነው። ከሚያዚያ 29 እስከ ዛሬ ግንቦት 11 ባሉት ቀናት #ብቻ አንድ መቶ ሃያ (120) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

• ሚያዚያ 29/2012 ዓ/ም - ሃያ አንድ (21) ሰዎች
• ሚያዚያ 30/2012 ዓ/ም - ሶስት (3) ሰዎች
• ግንቦት 1/2012 ዓ/ም - አስራ ሶስት (13) ሰዎች
• ግንቦት 2/2012 ዓ/ም - ሃያ አንድ (21) ሰዎች
• ግንቦት 3/2012 ዓ/ም - አምስት (5) ሰዎች
• ግንቦት 6/2012 ዓ/ም - አምስት (5) ሰዎች
• ግንቦት 7/2012 ዓ/ም - ስምንት (8) ሰዎች
• ግንቦት 8/2012 ዓ/ም - ሁለት (2) ሰዎች
• ግንቦት 9/2012 ዓ/ም - አራት (4) ሰዎች
• ግንቦት 10/2012 ዓ/ም - ሃያ ዘጠኝ (29) ሰዎች
• ግንቦት 11/2012 ዓ/ም - ዘጠኝ (9) ሰዎች

አሁንም ስርጭቱ ከዚህ በላይ እንዳይባባስ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ በድጋሚ መልዕክት ለማስተላለፍ እንወዳለን። የጤና ባለሞያዎችን ምክር የማናዳምጥ ከሆነ፣ የሚወጡትን መመሪያዎች የማናከብር ከሆነ ይህ ወረርሽኝ 'ከቁጥጥር ውጭ' ሊወጣ ይችላል።

መዘናጋትና ቸልተኝነት ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍላል!

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#HAWASSA

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ዛሬ በሰጠው መግለጫ #ሁሉም አሽከርካሪዎች እና ተሳፋሪዎች ከመጪው ሰኞ ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የፊትና የአፍ መሸፈኛ ማስክ የማድረግ ግዴታ እንደሚኖርባቸው አሳውቋል።

ይህን መመሪያ በሚተላለፉ አሽከርካሪዎች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ መምሪያው በጥብቅ አስታውቋል፡፡

መመሪያው በመላው ሀገሪቱ #እየጨመረ የሚገኘውን ፤ እንዲሁም ወደ ከተማው የመግባት አዝማሚያ እያሳየ ያለውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመከላከል ይረዳል ተብሎ የተዘጋጀ ነው ተብሏል።

የባለ 2 እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎችን እንዲሁም የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎች ረዳቶችና ተሳፋሪዎችን ፤ እንዲሁም የግልና የመንግስት መኪና አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎችን፤ ባጃጅና የመሳሰሉትን አነስተኛ የትራንስፖት ዘርፎች የሚያካትት ነው።

አሽከርካሪዎች ይህንን አውቀው በቀጣይ ሁለት (2) ቀናት ውስጥ ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የፊት ማስኮችን አድርገው መንቀሳቀስ እንደሚኖርባቸው ተገልጿል፡፡

#SRTA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መንግስት በኮቪድ-19 ዙሪያ እርምጃዎችን እያላላ ነው ?

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባስተላለፉት መልዕክት በቅርቡ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መመሪያው ላይ የተደረጉት ማሻሻያዎች መንግስት በኮቪድ-19 ዙሪያ እርምጃዎችን እያላላ ነው የሚል #የተሳሳተ ግንዛቤ በማህበረሰቡ ውስጥ እየተሰራጨ እንደሆነ ተናግረዋል።

ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ማሻሻያዎቹ የተደረጉት በሀገር አቀፍ ደረጃ ወረርሽኙ #እየጨመረ በመምጣቱ መንግስት ያለውን ውስን ሃብት የት ላይ ማፍሰስ አለበት የሚል ለወረርሽኙ ምላሽ የስትራቴጂክ ለውጥ አስፈላጊ በመሆኑና ይበልጥ ለወረርሽኙ ጠንከር ያለ ምላሽ ለመስጠት የተደረጉ እንጂ እርምጃዎችን የማላለት እቅድ እንደሌለ አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Alert🚨

የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከዕለት ወደ ዕለት #እየጨመረ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳውቋል።

ትላንት ለ5,916 ግለሰቦች የኮቪድ-19 ምርመራ ተደርጎ 511 ግለሰቦች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል። ይህ ማለት ናሙና ከሰጡ 100 ግለሰቦች 9ቱ (9%) የኮቪድ-19 ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል።

ትላንት በኮቪድ-19 የመያዝ ምጣኔ ከ68 ቀናት በኋላ የመጀመሪያው ከፍተኛ ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል።

በኮቪድ-19 ቫይረስ ተይዘው ህይወታቸውን የሚያጡ ግለሰቦች ቁጥርም እየጨመረ ይገኛል። በትላንትናው ዕለት ብቻ 8 ግለሰቦች በኮቪድ-19 ቫይረስ ህይወታቸውን አጥተዋል። ይህ ቁጥር ከ47 ቀናት በኋላ ከፍተኛው የሞት ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል።

ወደ #ፅኑ ህሙማን ክፍል የሚገቡ ግለሰቦች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እያሻቀበ በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ 25 ግለሰቦች ወደ ፅኑ ህሙማን ክፍል የገቡ ሲሆን በአጠቃላይ 308 ግለሰቦች አሁን ላይ በፅኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ ይገኛሉ፤ ይህም ከ53 ቀናት በኋላ ከፍተኛው ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል።

አሁንም ይህ ወረርሽኝ ችላ ሊባል የሚገባው ጉዳይ አንዳልሆነ ያስገነዘበው የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ወረርሽኙ የብዙዎችን ህይወት እየነጠቀ ብዙዎችን ደግሞ አካላዊ እና ማህበረሰባዊ ቀውስ ውስጥ እየከተተ ይገኛል ብሏል።

@tikvahethiopia
#GujiZone

• " እስከ ሃምሌ 15 ቀን 2014 ባለው ጊዜ የ12 ሰዎች ህይወት አልፏል ፤ ቁጥሩ ግን ሊጨምር ይችላል " - የሰባ ቦሩ ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ

• " የሞቱት ዜጎች ምናልባት በፀጥታ ችግር ምክንያት ሊሆን ይችላል " - የጉጂ ዞን ኮሚኒኬሽን

በኦሮሚያ ክልል፣ በጉጂ ዞን ፤ ሰባ ቦሩ ወረዳ በድርቅ ምክንያት የወገኖቻችን ህይወት እያለፈ መሆኑ ተገለፀ።

በኦሮሚያ ክልል፣ በጉጂ ዞን በሰባ ቦሩ ወረዳ ረሃብ ተከስቶ 12 ሰዎች መሞታቸውን የወረዳው ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ ማስታወቁን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ቢሮው፤ እስከ ሃምሌ 15 ቀን 2014 ዓ/ም ባለው ጊዜ ብቻ የ12 ሰዎች ህይወት ማለፉን ገልጾ ቁጥሩ ግን ሊጨምር እንደሚችል አሳውቋል።

በወረዳው 35,442 ዜጎች አስቸኳይ ምግብ እርዳት ያስፈልጋቸዋል የተባለ ሲሆን እነዚህ ዜጎች በንሳ ፣ በደጋላልቻ ፣ ሰባሎሌማሞ ፣ በኡቱሉ፣ ኦዴ ፣ ሀራጌሳ ቀበሌዎች ያሉ ናቸው ተብሏል።

የወረዳው ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት መኮና ሀጤሳ ፤ ለወረዳው አልፎ አልፎ የምግብ እርዳታ ቢመጣም ምግብ ከሚያስፈልጋቸው ዜጎች ጋር የሚመጣጠን አይደለም ብለዋል።

በወረዳው የሟቾች ቁጥር በየቀኑ #እየጨመረ ሲሆን ባለፉት 2 ወራት የምግብ እና መሰል እርዳታቸዎች መቋረጣቸው ማህበረሰሙ ለከፋ የምግብ እጥረት መጋለጡን ገልፀዋል።

የጉጂ ዞን የኮሚኒኬሽን ቢሮ በበኩሉ ፤ በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች 5 ወረዳዎች ድርቅ ተከስቷል ብሏል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ኦልኮ፤ " በረሃብ ምክንያት ስለሞቱ ሰዎች መረጃ የለኝም " ብለዋል። ነገር ግን " በአካባቢው የፀጥታ ችግር አለ " ሲሉ መግለፃቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Guji-Zone-08-04

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IOM በጅቡቲ የባህር ዳርቻ የ38 ሰዎች አስክሬን ተገኘ። በጀልባ መስጠም አደጋ የህፃናትን ጨምሮ አጠቃላይ 38 ሰዎች ሞተው አስክሬናቸው መገኘቱን የዓለም አቀፉ የስድተኞች ድርጅት አሳውቋል። 6 ሰዎች የገቡበት ያልታወቀ ሲሆን ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተነግሯል። ከሞት የተረፉ 22 ሰዎች በጅቡቲ እርዳታ እየተደረገለቸው ይገኛል። @tikvahethiopia
" 38 #ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸው አልፏል " - በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ

በጅቡቲ የባህር ዳርቻ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ #የመን በመጓዝ ላይ በነበረች ጀልባ ላይ በደረሰ የመስጠም አደጋ 38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸውን እንዳጡ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።

ትላንትና ሰኞ በጅቡቲ ሰሜን ምስራቅ " #ጎዶሪያ " በሚባል የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ስልሳ (60) ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ #የመን ትጓዝ የነበረች ጀልባ ላይ በደረሰው የመገልበጥ አደጋ የ38 ፍልሰተኞች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

በጅቡቲ የኢፌዴሪ ሚሲዮንም አደጋው ከደረሰ በኋላ ወደ ስፍራው በመጓዝ የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ኤምባሲው ፥ በየዓመቱ ከ200 ሺህ የሚበልጡ ፍልሰተኞች ከጅቡቲ ባህር ዳርቻ የኤደን ባህረ ሰላጤ በመነሳት መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመድረስ በየብስና በባህር አደገኛ ጉዞ ያደርጋሉ ብሏል።

ባለፉት አምስት ዓመታት #በጀልባ_መስመጥ አደጋ ብቻ የ189 ዜጎቻችን ሕይወት እንዳለፈ ጠቁሟል።

በየጊዜው የሚደርሰው አደጋ እንዳለ ቢሆንም የፍልሰተኞቹ ቁጥር ግን አሁንም #እየጨመረ እንደሆነ ገልጿል።

ዜጎች በህገ ወጥ #ደላሎች የሀሰት ስብከት በመታለል ውድ ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው በዚህ አደገኛ የጉዞ መስመር ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

የፍትህ አካላት ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን #ከገጠራማ የአገራችን አካባቢዎች ዜጎችን በመመልመል ለስደት በሚዳርጓቸው ግለሰቦች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳስቧል።

@tikvahethiopia