#DrLiaTadesse

ኮሮና ቫይረስ ሁሉንም የእድሜ ክልል ነው የሚያጠቃው!

(በዶክተር ሊያ ታደሰ - የጤና ሚኒስትር)

በሀገራችን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎችን የእድሜ ስብጥር ብንመለከት እስካሁን በቫይረሱ ከተያዙት 272 ሰዎች ከህፃናት እስከ አረጋዊያን ድረስ በሁሉም የእድሜ ክልል ያሉ ተይዘዋል።

ትልቁ ቁጥር 99 ሰዎች ከ15-24 የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ናቸው ፤ ከዛ የሚቀጥለው ከ25-34 የእድሜ ክልል ውስጥ (75 ሰዎች) የሚገኙ ሲሆን ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ ሰዎች ቁጥርም 19 ነው። በህፃናት ላይ አነስተኛ ቁጥር ቢታይም ህፃናትም በሽታው እንደሚይዛቸው ያሳያል።

ይህ በሽታ የማያጠቃው የእድሜ ክልል የለም። በዓለም አቀፍ ደረጃ #ወጣቶች አይጠቁም የሚል #የተሳሳተ ግንዛቤ አለ ፤ በተለይ በእኛ ሀገር ያለው ስርጭት ትልቁ ቁጥር በወጣቶች ላይ የታየ ነው። ስለዚህ እያንዳንዳችን የምንወስደው ጥንቃቄ እጅግ አስፈላጊ ነው።

የዚህ በሽታ ስርጭት #እየጨመረ የሚሄድ ሊሆን ቢችልም ምን ያህል ይጨምራል የሚለውን የምንወስነው በየዕለቱ በምንወስናቸው ውሳኔዎች ፣ በየዕለቱ በምንመርጣቸው ምርጫዎች እንዲሁም በምንወስዳቸው እርምጃዎች ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia