TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ...

እኔ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነኝ!

#የዚችን_ሀገር_ችግር_የምቀርፈው_በመማር_ነው!

#መብቴን_የማስከብረው_በማወቅ_ነው

#ከምማርበት_ጊዜ_ቀንሼ_ለወንድሜ_ድንጋይ_አላነሳም!

#ይልቅስ_ጊዜ_ተርፎንም_ከሆነ_በጎ_ፈቃደኞች_ነን!

ትዝታዎቼን ከጥላቻ ጋር ማስተሳሰር አልሻም።ሰዎችን በመደገፍ ግን የተሻለ አለም ለወገኖቼ መፍጠር እሻለሁ! ጓደኞቼም እንደዛው!

ቀኖቻችንን ፍቅር በመስጠት ውስጥ እያሳለፍን ነው! ብዙ ፍቅራችንን የሚፈልጉ ወገኖች አሉ!

በመገፋፋት በታሪካችን ላይ የምናሰፍረው አንዳች መልካም አሻራ የለም!

እኛ ጋር ብትመጡ የምናወራችሁ እና የምናሳያችሁ መልካም ነገር እንጂ የተሰበረ መስታወት ፥የተጠቃ ተማሪ ፥ አይደለም እኛ በጎ ፍቃደኞች ነን!

#ጣሊታ_ራይዝ_አፕ #ሀምሊን_የፌስቱላ_ማዕከል
#ሀዋሳ_ዩኒቨርስቲ #አዋዳ_ካሞፓስ
#ቅን_ዲል_ክበብ

©ሀና ሀይሉ(አዋዳ TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እናመሰግናለን!!

#ሀዋሳ_ዩኒቨርስቲ ላደረጋቹልን #ደማቅ አቀባበል እናመሰግናለን!! ድካማችሁ ድካማችን ነው። እውነትም የሰላም ተምሳሌት የሰላም አምባሳደሮች ናችሁ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ👆የዕለተ እሁዱ የማጠቃለያ ዝግጅት እጅግ ደማቅ እና በርካታ ቁም ነገሮች የተነሱበት ብዙ ሀሳቦች የተንሸራሸሩበት በተለያዩ የኪነ ጥበብ ስራዎች ስለጥላቻ ንግግር የማስገንዘብ ስራ የተሰራበት ነበር። እንደተለመደው በወጣት ነብያት አማካኝነት የውይይት ሀሳብ ተነስቶ ተሳታፊዎች ሀሳብ ሰንዝረዋል። የዚህ ሳምንት የመወያያ ጉዳይ የነበረው የኢትዮጵያ ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ነበር። የሀዋሳ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ህብረት #StopHateSpeech በሚል ወደተቋሙ ለመጡት የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት የክብር ሰርተፊኬት አበርክቷል።

የሀዋሳ ዩንቨርስቲ ሀሳቡን በመደገፍ እስከመጨረሻው ከTIKVAH-ETH #ጎን እንደሚቆም ገልጿል!

#ሀዋሳ_ዩኒቨርስቲ #StopHateSpeech
@tsegabwolde @tikvahethiopia