TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የፍርድ ቤት ውሎ! ከ38ቱ ተከሳሾች መካከል...

31ኛ ተከሳሽ ጌታቸር እሼቴ
32ኛ ተከሳሽ ቶፊቅ ሽኩር
33ኛ ተከሳሽ ሸምሱ ሰኢድ
34ኛ ተከሳሽ ፍፁም ጌታቸው በቂሊንጦ ቃጠሎ ሰበብ በተገደሉት ሰዎች ነፍስ እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል።

6ኛ ተከሳሽ አብዱሉሂ አልዩ
7ኛ ተከሳሽ እስማኤል በቀለ
11ኛ ተከሳሽ ቃሲም ገንቦ
18ኛ ተከሳሽ አንጋው ተገኘ
21ኛ ተከሳሽ ሰይፈ ግርማ
27ኛ ተከሳሽ ዲንሳ ፉፉ
28ኛ ተከሳሽ ናስር ደጉ
29ኛ ተከሳሽ ናኦል ሻሜሮ #በነፃ እንዲሰናበቱ ተበይኗል።

መቶ አለቃ ማስረሻ፣ ዶክተር ፍቅሩ ማሩ፣ አሸናፊ አካሉ፣ አግባው ሰጠኝ፣ ወልዴ ሞቱማ፣ ሚስባህ ከድር፣ ፍቅረማርያም አስማማው፣ ደረጀ መርጋ፣ ከበደ ጨመዳ፣ ደሴ አንዳርገው፣ ፍፁም ቸርነት ጨምሮ 28 ተከሳሾች እስር ቤት ውስጥ አመፅ በማደራጀት፣ በመምራት፣ በመሳተፍ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ አንቀፅ 464/2/ሀ፣ ለ፣ 461/ሀ እና 494 /2 ስር እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል።

ምንጭ፦ አቶ ጌታቸው ሽፈራው
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ እና አዲስ አበባ!!

ድምፃዊ #ቴዎድሮስ_ካሳሁን በአዲስ አበባ ስታዲየም #በነፃ የሙዚቃ ዝግጅቱን ለማቅረብ እየተዘጋጀ እንደሆነ ተሰምቷል። ለአዲስ አበባው ኮንሰርት ምንም አይነት ክፍያ እንደማይቀበል የተነገረ ሲሆን ለሙዚቃው ዝግጅት ከአዘጋጆቹ በተጨማሪ የተወሰነውን ወጪ እራሱ ይሸፍናልም ተብሏል። ህዝቡም ኮንሰርቱን በነፃ እንደሚታደምበት ነው የተገለፀው። ከአዲስ አበባው በአይነቱ የተለየ የሙዚቃ ዝግጅት በተጨማሪ ድምፃዊው #በሀዋሳ ከተማ የሙዚቃ ዝግጅት ለማቅረብ እቅድ እንዳለው ለመስማት ተችሏል። የሙዚቃ ዝግጅቶቹ መቼ ይካሄዳሉ?? የሚለው ግን የታወቀ ነገር የለም።

ምንጭ፦ ኢትዮፒካሊንክ የሬድዮ ዝግጅት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስደሳች ዜና!

#ህብር_የኢትዮጵያዊያን_ፌስቲቫል
🗓ሃሙስ ህዳር 27
🕗ከ8፡00 ጀምሮ
🔹#በጊዮን_ሆቴል

#መግቢያ፡ ኢትዮጵያዊ የባህል ልብስ መልበሰ (#በነፃ)

ተማሪዎች እና መላው የአዲስ አበባ ህዝብ በተበታተነ ቦታ ያከበር የነበረውን የባህል ቀን( #CultureDay) በህብረት እናክብር! ተወዳጆቹ የሃገራችን ድምጻውያን #አሊ_ቢራ #ሚካኤል_በላይነህ #ዳዊት_ነጋ #አቡሽ_ዘለቀ #ሰለሞን_ጋጋ እና #ሮፍናን ስራቸውን ያቀርባሉ።

ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ቀመው ይገኙ! ባህላዊ አልባሳትን #ላልለበሰ ሰው ቦታ የለንም!

አዘጋጅ፦ ጆርካ ኢቨንት፣ አዲስ አበባ መስተዳድር እና ፈታ ሾው / info 0975 070707 /
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስደሳች ዜና!

#ህብር_የኢትዮጵያዊያን_ፌስቲቫል
🗓ሃሙስ ህዳር 27
🕗ከ8፡00 ጀምሮ
🔹#በጊዮን_ሆቴል

#መግቢያ፡ ኢትዮጵያዊ የባህል ልብስ መልበሰ (#በነፃ)

ተማሪዎች እና መላው የአዲስ አበባ ህዝብ በተበታተነ ቦታ ያከበር የነበረውን የባህል ቀን( #CultureDay) በህብረት እናክብር! ተወዳጆቹ የሃገራችን ድምጻውያን #አሊ_ቢራ #ሚካኤል_በላይነህ #ዳዊት_ነጋ #አቡሽ_ዘለቀ #ሰለሞን_ጋጋ እና #ሮፍናን ስራቸውን ያቀርባሉ።

ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ቀመው ይገኙ! ባህላዊ አልባሳትን #ላልለበሰ ሰው ቦታ የለንም!

አዘጋጅ፦ ጆርካ ኢቨንት፣ አዲስ አበባ መስተዳድር እና ፈታ ሾው / info 0975 070707 /
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስደሳች ዜና!

#ህብር_የኢትዮጵያዊያን_ፌስቲቫል
🗓ሃሙስ ህዳር 27
🕗ከ8፡00 ጀምሮ
🔹#በጊዮን_ሆቴል

#መግቢያ፡ ኢትዮጵያዊ የባህል ልብስ መልበሰ (#በነፃ)

ተማሪዎች እና መላው የአዲስ አበባ ህዝብ በተበታተነ ቦታ ያከበር የነበረውን የባህል ቀን( #CultureDay) በህብረት እናክብር! ተወዳጆቹ የሃገራችን ድምጻውያን #አሊ_ቢራ #ሚካኤል_በላይነህ #ዳዊት_ነጋ #አቡሽ_ዘለቀ #ሰለሞን_ጋጋ እና #ሮፍናን ስራቸውን ያቀርባሉ።

ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ቀመው ይገኙ! ባህላዊ አልባሳትን #ላልለበሰ ሰው ቦታ የለንም!

አዘጋጅ፦ ጆርካ ኢቨንት፣ አዲስ አበባ መስተዳድር እና ፈታ ሾው / info 0975 070707 /
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የደንብ ልብስ(ዩኒፎርም) #በነፃ ለማቅረብ በወሰነው መሠረት በዛሬው ዕለት #በፋሽን ዲዛይነሮች የተዘጋጁ ዲዛይኖች ቀርበው ምክክር ተደርጎባቸዋል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ አስተባባሪነት በባለሞያዎቹ በቀረቡ የዲዛይን ስራዎች ላይ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች፣ የስነ-ልቦና ባለሞያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየት ሰጥተውበታል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ለKG ተማሪዎች ፤ ከ1ኛ-4ኛ ላሉ ተማሪዎች ፤ ከ5ኛ-8ኛ እና ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች በአራት ዘርፍ ዩኒፎርሞችን አዘጋጅቶ ለተማሪዎች በነፃ ለማቅረብ እየሰራ ነው፡፡

ለመጪው የትምህርት ዘመን የከተማ አስተዳደሩ ለ 600ሺ የመንግስት ት/ቤት ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ እና የደንብ ልብስ ለማቅረብ እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

Via @mayorofficeAA
🗞ቀን ሃምሌ 1/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮ- አሜሪካ ዶክተሮች ቡድን ለኢትዮጵያ ስፖርተኞች የቀዶ ህክምና አገልግሎቴን እየሰጠሁ ነው ብሏል:: የኢትዮ- አሜሪካ ዶክተሮች ቡድን አባላት ለእግር ኳስ ተጫዋቾች እና ሌሎች ያለምንም ክፍያ የቀዶ ህክምና አገልግሎት በአቤት ሆሰስፒታል (AaBET) እየሰጠ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ዶክተሮቹ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ #በነፃ የ15 የአጥንት ህሙማንን ቀዶ ጥገና የከወኑ መሆናቸው ተነግሯል፡፡

አቤት ሆስፒታል ውስጥ ወደ 200 የሚጠጉ ህሙማን የአጥንት ቀዶ ጥገናውን የሚጠብቁ ሲሆን ለህክምናው እያንዳንዱ ሰው በትንሹ 200 ሺ ብር ይጠየቃል ተብሏል፡፡ የኢትዮ- አሜሪካ ዶክተሮች ቡድን አባላት በአጥንት ቀዶ ጥገና ባለሙያው ዶ/ር ክብረት ከበደ እየተመሩ አገልግሎቱን እየሰጡ ነው፡፡

የህክምና ቡድኑ የአጥንት ጡንቻ መዛባት ያለባቸውን ኢትዮጵያውያን የስፖርት ሰዎችን ደርሸላቸዋለሁም ብሏል፡፡ በተጨማሪም በዘርፉ ታዋቂ ባለሙያዎችን ማካተቱንም አስታውቋል፡፡ ቡድኑ አባላቱን ለማገዝ የህክምና መሳሪያዎችን እና ባለሙያዎች አቀናጅቶ ይዞ እንደመጣ ገልጧል፡፡ ከመጡት መሳሪያዎች ውስጥ አቤት ሆስፒታል ውስጥ መትከሉን ተናጋሯል፡፡

የኢትዮ- አሜሪካ ዶክተሮች ቡድን ከ340 በላይ አባላትን የያዘ ሲሆን በየዓመቱ ያልተቋረጠ የህክምናና እና ቀዶ ጥገና ትምህርቶችን ለሀገር ቤት የህክምና አባላት ከመስጠቱ በተጨማሪ በ110 ሚሊዬን ዶላር በጀት ዓለም አቀፍ ቴሪሸሪ ሆስፒታል እያስገነባ መሆኑን እወቁልኝ ብሏል፡፡

ምንጭ፦ አርትስ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የEBS ስፖርት አዘጋጁ ትንሳኤ መልካም ስራዎች👆

ወጣት ትንሳኤ ይባላል የስፓርት አሰልጣኝ ነው። ኢ.ቢ.ኤስ ቲቪ ማለዳ 12:30--1:30 በድጋሚ 02:00---03:00 ከሰኞ እስከ ሰኞ የሚታይ የቲቪ ፕሮግራም አለው።

ወጣት ትንሳኤ ከስፖርቱ በተጨማሪ የሚወዳትን ሀገርና ህዝቦቿን በመልካም ስራ ያገለግላል ይህን በጥቂቱ ልበላችሁ፦

•በየወሩ መንገድ ለሰው የሚባል "ከመኪና ነፃ ቀን" አለ በበጎ ፍቃድ #በነፃ ስፓርት ያሰራል።

•በተለያዩ መስቀል አደባባይ በሚዘጋጁ ፌስቲባሎች ላይ በነፃ ያገለግላል።

•ሜቆዶንያም በሳምንት አንድ ቀን እየሄደ አረጋዊያንን በነፃ በስፓርት ያዝናናቸዌ

ከሰሞኑን ደግሞ በራሱ ተነሳሽነት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አዘጋጅቶ ነበር፦

• ወጣቱ ስፖርተኛ ትንሳኤ ለTIKVAH-ETH ሲናገር፦ "ይህንን ችግኝ ለመትከል የተነሳውበት አላማ የጠቅላይ ሚኒስተራችንን ሐሳብ በመደገፍ ነው" ይላል! የተሰሩትንም ስራዎች እንዲህ ዘርዝሮ ነግሮናል።

1.የአከባቢውን ነዋሪዎችን የእምነት አባቶችን፤ የቀበሌ ሊቀመንበሮችን፣ የወንጂ ከንቲባን በማነጋገር ደብዳቤም በመላክ ጥሪ አደረገላቸው እነሱም ተስማምተው አብረውት ተከሉ።

2. ለእምነት ተቁአማት በሙሉ ችግኞችን በግቢያቸው በመትከል እንደሚንከባከቡት ቃል ገብተውለታል።

3. በወንጂ ሸዋ ስካር ፍብሪካ ድርጅቱን በፈለገው ቦታ አስቆፍሮ ወጣት ትንሳኤ ችግኞችን ገዝቶ በመረጡት ቦታ ተክለዋል።

4. ለግሪን ኤሪያ በታጠረ ቦታም ተተክሏል
ወንጂ ገፈርሳ ከንቲባው በተገኙበት ይህ የተከናወነው።

5. ከሀይስኩል ት/ቤትናኢሊመንተሪ ት/ቤት ተማሪዎች ጋር ችግኝ ተከላው ተከናውኗል።

ወጣት ትንሳኤ ይዞት የተነሳውት መሪ ቃል "አንድ ችግኝ መትከል ለመንደራችን፤ ለሐገራችን፤ ለአለምልችን" የሚል ነው።

ከችግኝ ተከላው በተጨማሪ...

ወላጆቻቸው ለሞቱባቸው ልጆች የድብተር እስክርቢቶ፣ እርሳስ በመግዛት አበርክቷል፤ ለወጣቶችም ካሶችን ሸልሟል።

በስራዎቹ ማን እንዳገዘውም ነግሮናል፦

•የበቆጂ ውሃ ባለቤት 500 ችግኞችን ገዝተው አብረው በመትከልም ተባብረውታል።

• አልባር አስመጪና ላኪ ድርጅት 500 ችግኞችን ገዝቶለታል

የሚገርመው ግን ...

ወጣት ትንሳኤ ሰለሞን 5000 ሺህ ችግኞችን ገዝቷል። የአንዱ ችግኝ ዋጋ ከ 50--80 ብር ደርሳል።

በመጨረሻም እንዲህ ብሏል፦

"በጎ ስራ በአንድ ቀን ተሰርቶ የሚያልቅ ነገር አይደለም። የሚቀጥል ስራ ገና ይጠብቀኛል።...ሌላው ብዙ ወጣቶች ውልግዜ ከመንግስት መጠበቅ የለብንም እኛም ባለን ነገር ማገዝ መነሳሳትን ለመፍጠር ነው። ተቀባይ ብቻ ሳንሆን ሰጪም መሆን እንዳለብን ለማመልከት ነው።"

እኛም በርታልን ብለናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ችሎት!

ዛሬ ፍርድ ቤት የኢ/ር ይልቃል ጌትነትን ጉዳይ ተመልክቷል።

የዛሬው ቀጠሮ መርማሪ ፖሊስ ባለፈው በነበረው ቀጠሮ ተጠርጣሪዎችን ከወንጀሉ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለብቻ ነጥሎ ለማቅረብና የደረሰበትን አጠቃላይ ሁኔታ ለፍርድ ቤት ለማሳወቅ ነው።

መርማሪ ፖሊስ ሰራዋቸው ያለው ስራ ፦

- ተጨማሪ ምስክሮችን ሰምቻለሁ፣ከወንጀሉ ጋር የተያዙ እቃዎቻቸውን ለምርመራ ለፌደራል ፖሊስና ለብሄራዊ ደህንነት ልኪያለሁ ውጤት እየጠበኩ ነው ብሏል።

- የንብረት ግምት እንዲላክ ፣ የአስክሬን ምርመራ ሪፖርት እንዲላክልኝ ለሚመለከታቸው አካላት ልኪያለሁ ብሏል ፤ እነዚህ ስራዎች ስለሚቀሩኝ 14 ቀን ይሰጠኝ ብሏል።

የኢንጂነር ይልቃል ጠበቃ አዲሱ ጌታነህ ፦

ኢንጂነር ይልቃል ከወንጀል ጋር ያላቸው ግንኙነት ፣ በምን ሁኔታ፣ እንዴትና መቼ እንደተፈፀመ ፖሊስ እንዲያቀርብ ነበር የታዘዘው።

የ14 ሰው ህይወት አልፏል ለዛም ውጤት እጠብቃለሁ ፣ ንብረት ወድሟል ከማለት ያለፈ ተለይቶ የተሳትፎ ደረጃቸው ስላልተገለፀ ለ27 ቀናት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ ሲያደርግ ነበር ተጨማሪ ጊዜ አያስፈልግም መዝገቡ ተዘግቶ #በነፃ ይለቀቁ ብለዋል።

ፍርድ ቤት ፦

- የተጠርጣሪ ጠበቃን አቤቱታ ሰምቶ ፣ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን ጥያቄ ተመልክቶ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ አስፈላጊነው ፣ አይደለም የሚለውን ለመወሰን ለሐምሌ 24 ቀጠሮ ሰጥቷል #DW

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጦቢያ የቤተሰብ ቀን ልዩ ፌስቲቫል !

ውድ የጦቢያ ቤተሰቦች እሁድ ጥር 8/2014 " በጊዮን ግሮቭ ጋርደን ዎክ " ከቀኑ 6ሰአት ጀምሮ

- በማርሽ ባንድ ኢትዮጵያን ይዘምራሉ!
- በድንቅ ገጣሚያን የግጥም ጥምዎን ያረካሉ!
- በፍራሽ አዳሹ ፍራሽዎ ይታደሳል!
- በመረዋ ኳየር የተቀነባበረ ስልተ ድምፅ ይደመማሉ!
- በኢትዮጵያነት የውዝዋዜ ቡድን አዲስ ስራዎች ይዝናናሉ። በዚህ ሁሉ ውስጥ ኢትዮጵያችን አለች!!

#በነፃ_ሃሳብና_በሰከነ_መንፈስ_ኢትዮጵያንና_ኢትዮጵያዊነትን_እናድምቅ!

የመግቢያ ትኬቱ በሁሉም የቡና ባንክ ቅርንጫፎች ይገኛል።
ለመረጃ 0919787878
#ጥቆማ

ለሰሜን ወሎ ዞንና አጎራባች ማህበረሰብ ክፍሎች ፦

የወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከሀረር ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ችግር እንዲሁም ከአንገት በላይ እባጭ ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች #በነፃ_የህክምና አገልግሎት ለመስጠት አቅዷል።

በሆስፒታሉ ቢሮ ቁጥር 12 ላይ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ 0333311680 / 0920218203 በመደወል ከ1/09/2014 ዓ/ም ጀምሮ በመመዝገብ የእድሉ ተጠቃሚ መሆን ይቻላል።

(ላልሰሙትም አሰሙ)

@tikvahethiopia
ቴሌግራም ፕሪሚየም / Telegram Premium

ቴሌግራም አሁን #በነፃ እየሰጠ ያለው አገልግሎት #እንደተጠበቀ ሆኖ ተጨማሪ አገልግሎት የሚሰጥበትን እና ድርጅቱም ገቢ የሚያገኝበትን በክፍያ የሚሰጥ " ቴሌግራም ፕሪሚየም " የተሰኘ አገልግሎት በዚህ ወር ያስጀምራል።

ክፍያውን በተመለከተ ለጊዜው የተባለ ነገር የለም።

(የቴሌግራም ዋና ስራ አስፈፃሚ እና መስራች ፓቬል ዱሮቭ የተላለፈ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia