TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሳዛኝ_ዜና⬇️

በሶማሊያ የፑንትላንድ የንግድ ከተማ በሆነችው ቦሳሶ ውስጥ ሦስት #ኢትዮጵያዊያን #በአይሲስ ታጣቂዎች #ሲገደሉ ቢያንስ አንድ መቁሰሉ ተዘገበ።

ስለጥቃቱ በቀዳሚነት የወጡ ዘገባዎች እንዳመለከቱት ታጣቂዎቹ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ይኖሩበታል በሚባለው ሳንቶስ ተብሎ በሚጣራው የከተማዋ ክፍል ውስጥ ባገኟቸው አራት ኢትዮጵያዊያን ላይ #ተኩስ ከፍተው ነው ጥቃቱን የፈፀሙት።

አንድ ስማቸውን ያልጠቀሱ የአካባቢው ባለስልጣን ኢትዮጵያዊያኑ በተፈፀመባቸው ጥቃት መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ለቢቢሲ ሲያረጋግጡ፤ አፍቃሬ አይኤስ የሆነ ቡድንም በትዊተር ገጹ ላይ ስለጥቃቱ አስፍሯል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ ሃገራት የኤደን ባህረ ሰላጤን በትናንሽ ጀልባዎች በማቋረጥ ወደ የመንና የመካከለኛው ምሥራቅ ሃገራት በህገ ወጥ መንገድ ለመሻገር የሚፈልጉ ስደተኞች #የቦሳሶን የባህር በር ይጠቀማሉ።

በአካባቢውም በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንደሚገኙ ተገልጿል።

እነዚህ በጥቃቱ የሞቱትና የቆሰሉት ኢትዮጵያዊያንም በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች አማካይነት ባህሩን ተሻግረው በጦርነት ወደ የምትታመሰው #የመን ለመጓዝ በቦታው የነበሩ ስደተኞች እንደሆኑ ይታመናል።

አይሲስ ከቅርብ ወራት ወዲህ በጉልህ የሚታዩ በርካታ ጥቃቶችን በሶማሊያ ውስጥ እየፈፀመ ሲሆን በተለይ ደግሞ በፑንት ላንድ ግዛት ውስጥ የአይኤስ ቡደን ከሌሎች አካባቢዎች በበለጠ ሰፊ እንቅስቃሴ ያደርጋል ተብሎ ይታመናል።

ፑንትላንድ በሰሜን ሶማሊያ የምትገኝ ከፊል ራስ ገዝ የሆነች ግዛት ናት።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ታንዛኒያ በእስር ላይ የሚገኙ #ኢትዮጵያዊያን በምህረት እንዲለቀቁ ተጠየቀ ወደደቡብ አፍሪካ ሲያመሩ በታንዛኒያ የተያዙ 224 ኢትዮጵያዊያን በአስር ላይ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ የዜጎቿን ደንነት መጠበቅ ቀዳሚ አጀንዳዋ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ አስታውቀዋል። ዶክተር ወርቅነህ ገበየህ ከአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጎን ለጎን ከታንዛኒያ አቻቸው ዶክተር አውጉስቲን ማሂጋ ጋር በሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው ይህንን ያስታወቁት።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
450 #ኢትዮጵያዊያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ #ሀገር_ቤት ተመለሱ!

በሳውዲ አረቢያ ከእስር በምህረት የተፈቱ 450 ኢትዮጵያን ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያውያኑ የተፈቱት ከሳውዲ አረቢያ መንግስት ጋር በተደረገ ማግባባትና ድርድር እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በያዝነው ሳምንት የዛሬዎቹን ጨምሮ 2 ሺህ 400 ዜጎች በምህረት የተፈቱ ዜጎች ወደ አገራቸው ይመለሳሉ ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡

በዛሬው ዕለትም የሳውዲ ህግ በማይፈቅዳቸው ተግባራት ላይ በመሳተፋቸው በተለያዩ የአገሪቱ ማረምያ ቤቶች በእስር የቆዩ 450 ኢትዮጵያውያን አገራቸው ገብተዋል፡፡

ተጨማሪ 450 ደግሞ የፊታችን አርብ ወደ አገራቸው እንደሚመለሱ ይጠበቃል፡፡
በተጨማሪም ባለፈው ሳምንት ህይወታቸውን ለአደጋ ባጋለጠ ሁኔታ ቀይ ባህርን አቋርጠው ሳውዲ አረቢያ የገቡ 1500 ኢትዮጵያውያን በዚህ ሳምንት ወደ አገር ቤት ይመለሳሉ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሳውዲ አረቢያ ጀዳህ በሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ በኩል ለተመላሾቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑ ተመልክቷል፡፡

ሚኒስቴሩ ባለፈው ሳምንት ከ410 በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው መመለሱ ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ከጥቂት ወራት በሗላ የአፋር፣ የቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ የሶማሌ፣ የኦሮሞ፣ የአማራ...ፓርቲ እያልን አንሄድም። እንደ ኢህአዴግ ከጫፍ ጫፍ ያሉ ሁሉም #ኢትዮጵያዊያን በነፃነት የሚሳተፉበት አንድ ሀገራዊ ፓርቲ #እንመሰርታለን!!" ጠ/ሚ ዶ/ር #አብይ_አህመድ - ከተለያዩ ክልል ተወካዬች ጋር ሲወያዩ የተናገሩት

@tsegabwolde @tikvahethiopia
“እኛ #ኢትዮጵያዊያን እርስ በርስ የሚያስተሳስሩ በርካታ ማንነቶች ያሉን፣ ለዘመናት የቆየ የሐይማኖት መከባበር ልምድ፣ የአኩሪ ባህል ባለቤቶች፣ አንገትን ከፍ አድርገን እንድንራመድ የሚያደርጉን የታሪክ ባለቤቶች መገኛ ነን፡፡ ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ እየተነሱ ያሉ #የዘርና #የጎሳ ግጭቶች ለእንደኛ አይነት ህዝቦች #ማይመጥኑ አስነዋሪ ተግባራት በመሆናቸው ሁላችንም በቃ ልንላቸው ያስፈልጋል” የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዶ/ር #ሂሩት_ካሳው

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ትላንት ማምሻውን ለፕሬዝዳንት #ኡሁሩ_ኬንያታ በተዘጋጀ የእራት ግብዣ ላይ ፕሬዚዳንቱ በንግግራችው አዲስ አበባ #የኬንያኖችም የሁሉም ከተማ መሆንውን ገልጸዋል። በተያያዥነትም የሸገርን ማስዋብ ፕሮጀክት #እንደሚደግፉ ገልጸው የኬንያ ባለሀብቶች በገበታ ለሸገር ከጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድና #ኢትዮጵያዊያን ጎን እንደሚቆሙ #ቃል_ገብተዋል

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikbahethiopia
Audio
መጤ-ጠል ጥቃት በደቡብ አፍሪካ‼️

በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ አካባቢ ከሌሎች የአፍሪካ ሃገሮች የገቡና እዚያው የሚኖሩ ሰዎችን ዒላማ ባደረገ ጥቃት #ኢትዮጵያዊያን ላይ ጉዳት መድረሱን የከተማዪቱ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ተናግረዋል።

ባለፈው ሣምንት በጀመረው በዚህ ጥቃት ማንዲኒ በምትባል ቦታ ያሉ የኢትዮጵያዊያን ሱቆች መዘረፋቸውን ገልፀዋል። ፕሪቶሪያ የሚገኘው በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጉዳዩን እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል።

#ቪኦኤ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ከአለም ሀገራት ቀዳሚ ተባለች! በምን ያላችሁ እንደሆነ፦ ኢትዮጵያ ከአለም ሀገራት ቀዳሚ የተባለችው #በተፈናቃይ ቁጥር ነው!!
.
.
/BBC/

በባለፈው የፈረንጆች ዓመት በዓለም ዙሪያ አዲስ ከተፈናቀሉ ሰዎች መካከል #ኢትዮጵያዊያን ከፍተኛውን ቁጥር እንደሚይዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያወጣው መረጃ አመልክቷል።

የተፈናቃዮቹ ቁጥር 1.5 ሚሊዮን ሲሆን ከእነዚህም መካከል 98 በመቶዎቹ እዚያው ሃገር ውስጥ የተፈናቀሉ ናቸው። ይህ አሃዝ ቀደም ሲል ከነበረው ከእጥፍ በሚበልጥ ቁጥር የጨመረ ሲሆን ከዚያም በኋላ ቁጥሩ ጨምሯል።

ለዚህ መጠኑ ከፍተኛ ለሆነው የሃገር ውስጥ መፈናቀል ተጎራብተው በሚኖሩ የተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል ባለፈው ዓመት ባጋጠሙ ግጭቶች ምክንያት እንደሆነ ተጠቅሷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert “ኢትዮጵያ ውስጥ #ጥላቻና ብጥብጥ ከሚቀሰቅሱ የዳያስፖራ አባላት የተወሰኑት ዩናየትድ ስቴትስ የሚገኙ ናቸው” ሲሉ አዲስ አበባ የሚገኙት የአሜሪካ አምባሳደር ተናግረዋል።

“ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሚገኙበት ምቾትና ደኅንነት ውስጥ ሆነው እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ጥላቻና ብጥብጥ ያነሳሳሉ” ብለዋል አምባሳደር ማይክ ራይነር።

ሰሞኑን በተመሣሣይ ጉዳይ ላይ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ “ጥላቻና ብጥብጥ ያነሳሳሉ” ያሏቸውን “አንዳንድ” የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት “የእውነት አምላክ ይፍረድባቸው” ሲሉ አማርረዋል።

የሚባሉትን #ኢትዮጵያዊያን አስመልክቶ በሁለቱ ሃገሮች መካከል የተደረገ ንግግር ስለመኖር አለመኖሩ የታወቀ ነገር የለም።

Via #VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
”የኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ለእኛ #ኢትዮጵያዊያን ክብራችን ናት” ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ #ETH

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-07-14
#ኢሬቻ2012

"አዲስ አበባ የሁሉም #ኢትዮጵያዊያን ከተማ እንደመሆኗ መጠን የኦሮሞ ህዝብም በከተማው የኢሬቻን በዓል ለማክበር በመቻሉ የተሰማኝ ደስታ ከፍ ያለ ነው፡፡ በቀጣይነትም ከተማችን አዲስ አበባ ኃላፊነት ወስዳ የኢሬቻን በዓልን ጨምሮ ሌሎችን የሃገራችን በዓላት እና እሴቶች በሃገር ደረጃ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ እና በዓለም መድረኮች ሁነቶችን በመጠቀም ታስተዋውቃለች። ከተማ አስተዳደራችን እና ነዋሪዎቿ በታሪክ አጋጣሚ የዚህ ታሪካዊ ኃላፊነት አስተናጋጅ በመሆናችን ደስታ ይሰማናል፡፡ በመጨረሻም የኢሬቻ በዓል በአዲስ አበባ በዚህ ደረጃ በተቀናጀ እና ባማረ መልኩ እንዲከበር አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ የከተማችን ነዋሪወች እና ባለሃብቶች ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡" ኢንጂነር ታከለ ኡማ

@tsegabwolde @tikvahethiopia