TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጥንቃቄ‼️ነገ በአዲስ አበባ ከተማ #ህጋዊ እውቅና የተሰጠው ሰላማዊ ሰልፍ የለም። የTIKVAH-ETH ቤተሰብ #አባላት ህጋዊ እውቅና ከሌለው ሰልፍ ላይ ከመገኘት #ተቆጠቡ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የትግራይ ህዝብ #ህጋዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት እንቅስቃሴ #ሊረበሽ አይገባም"--ዶክተር #ደብረጽዮን_ገብረሚካኤል

.
.
የትግራይ ህዝብ ህጋዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ሳይረበሽ #በልማቱ ላይ ሊያተኩር እንደሚገባ የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ገለጹ።

ምክትል ርዕሰ-መስተዳደሩ ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ህጋዊና #ኃላፊነቱንም ለመወጣት የሚያስችል ነው።

በመሆኑም የክልሉ ህዝብ ይሄንን ተገንዝቦ ያለምንም መረበሽ የልማት ስራውን #በተረጋጋ መልኩ ማከናወን እንዳለበት አሳስበዋል።

ህዝቡ የሚያነሳው የህገ-መንግስት ይከበርልን ጥያቄ እራሱ ከማክበር የሚጀምር መሆኑንም ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር በመግለጫቸው አመልክተዋል።

የክልሉን ሰላምና ጸጥታ የማስከበርን ጉዳይም ህዝቡ በፈጠረው አደረጃጀት አንድነቱን ማስቀጠል እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታት ባደረጉት የጋራ ስምምነት የሁመራ ኦምሃጀር መንገድ መከፈትም ለሁለቱ ህዝቦች ግንኙነት ጠቃሚ እንደሆነ ዶክተር ደብረጽዮን ተናግረዋል።

መንገዱ የሁለቱን ሃገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ከማሳደግ ባለፈው ቀጣይ ህጋዊ መስመር ለማስያዝም ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል #ህጋዊ የድንበር ላይ ንግድ ልውውጥ ለማስጀመርና ለመቆጣጠር አራት የንግድ ማስተላለፊያ ኬላዎችን ለመክፈት የልየታ ስራ ማጠናቀቁን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ። ከሚከፈቱት ኬላዎች መካከል ሁለቱ በዛላምበሳና ራማ የሚገኙ ናቸው። በአገሮቹ መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ሳቢያ ምጣኔ ኃብትን ጨምሮ አጠቃላይ ግንኙነታቸው ተቋርጦ ለሁለት አስርት ዓመታት ቆይቷል።

via ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በለገጣፎ ለገዳዲ ቤት ማፍረሱ ዛሬም ቀጥሏል‼️

የለገጣፎ -ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር አረንጓዴ ቦታዎችን፥ የወንዝ ዳርቻዎችን፥ ከፈቃድ ውጭ የተያዙ እና ካሳ ተከፍሎባቸው ግንባታ የተካሄደባቸው ናቸው ያላቸውን ቤቶች እያፈረሰ ነው።

ቤት ማፍረሱ በትናንት ማክሰኞ ዕለት የተጀመረ ሲሆን የከተማው ከንቲባ የሆኑት በ10 ሺህዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ፈርሰው የሕዝብ መናፈሻ ይሆናሉ ማለታቸው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

በዛ ያለ ቁጥር ያላቸው ተጨማሪ ቤቶች እንደሚፈርሱ የሚጠበቅ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎች እርምጃው ዱብ ዕዳ ሆኖብናል ይላሉ።

በ1990ዎቹ መጀመሪያ ከአርሶ አደር መሬት ገዝቶ፤ ጎጆ ቀልሶ በስፍራው መኖር ሲጀምር አካባቢው ከሞላ ጎደል በማሣዎች የተከበበ፣ መሠረት ልማት የናፍቀው እንደነበር የሚገልፀው አንዋር አህመድ ቤቶቻቸው በትናንትናው ዕለት ከፈረሱባቸው አባወራዎች አንዱ ነው።

እኛ ስንገባ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ራሱ አልተዋቀረም ነበር የሚለው አንዋር፤ ለቤቱ ካርታ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ ባይሳካም "ውሃና መብራት አስገብተናል፣ የቤት ቁጥር ተሰጥቶናል፣ የመሬት ግብር እንከፍላለን" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።

መንደሩን የሚያቋርጡ መንገዶች በሚቀየሱበት ወቅት ኗሪዎች ሁለት፣ ሦስት ጊዜ ቤቶቻቸውን እና አጥሮቻቸውን አፍረሰው መሥራታቸውን የሚያስታውሰው አንዋር፤ የአሁኑ እርምጃ ፈጣን እንዲሁም የነዋሪዎቹን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ እንደሆነ ይናገራል።

"ይህ የመኖሪያ መንደር እንደሆነ ይታወቃል፤ አረንጓዴ መናፈሻ ይሁን የሚለው አዲስ ማስተር ፕላን እዚያው ቢሮ ቁጭ ብለው የወሰኑት ነገር ነው። ምንም ሳያወያዩን ነው ድንገት ውሳኔ ይዘው የመጡት።"

በወርሃ የካቲት መባቻ የ'ውጡ' ትዕዛዝ እንደደረሰው ለቢቢሲ የገለፀው አንዋር፤ አስር አባላት ያሉትን ቤተሰቡን ይዞ የትም ለመሄድ እንዳልቻለ ይገልፃል።

እንደአንዋር ገለፃ ቤቶቻቸውን ያጡ አንዳንድ ነዋሪዎች በእምነት ተቋማት ተጠልለዋል።

"ያለምንም ቅደም ሁኔታ ነው ያፈረርሱብን። ዕቃችን እስክንሸክፍ እንኳ ጊዜ አልሰጡንም" ሲል ጨምሮ ለቢቢሲ ተናግሯል።

በአካባቢው መሬት ገዝታ መኖር ከጀመረች ስምንት ዓመት እንደሞላት ለቢቢሲ የገለፀች ሌላ ነዋሪ፤ የመኖሪያ ቤቷ ባይፈርስም በስጋት መወጠሯ እንዳልቀረ ታስረዳለች።

"ትናንትና ብዙ ሕፃናት ሜዳ ላይ ሲወድቁ አይቻለሁ" የምትለው ነዋሪ ይህም ያለፈቃድ የሚሠሩ ቤቶችን አስመልክቶ "ሰማይ ላይ ነው እንጅ ምድር ላይ ጨረቃ የለም" በሚል ከመንግሥት ተሰጥቷል የምትለውን ተስፋ እና መተማመኛን የናደ እንደሆነባት ትናገራለች።

"ዱብ ዕዳ ነው የሆነብን፤ የት እንሄዳለን?"

በስፍራው አስራ ዘጠኝ ዓመት መኖሩን ለቢቢሲ የነገረ ሌላ ነዋሪ በበኩሉ የከተማው አስተዳደር ለገበሬው ካሳ የተከፈለበት ቦታ ላይ የተሠሩ ቤቶችን ነው የማፈርሰው ማለቱን እውነት አይደለም ይላል።

"ይሄ ቤት የተሰራው በ1992 ነው። ማዘጋጃው የተሰራው ከዓመታት በኋላ ነው። የት ሆነው ነው የከፈሉት? ለገበሬው ካሳ የከፈልንበት መሬት ላይ ነው የሰፈራችሁት ነው የሚሉን። እዚህች መሬት ላይ ለአንድም ገበሬ ምንም አልተከፈልም። ግምት ሳይከፍሉ በነፃ ለመውሰድ ነው ለገበሬው ከፍለናል የሚሉት" ይላል።

አንዋር የራሱን ልጆች ዋቢ አድርጎ፥ የከተማው አስተዳደር ተማሪ ሕፃናት የጀመሩትን የትምህርት ዓመት እስኪጠናቀቅ ቢታገሳቸው መልካም እንደነበር ይገልፃል። መንግስት ተፈናቃዮችን ለማቋቋም፥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደግሞ የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለመሰብሰብ እየጣሩ እንዳሉ በሚናገሩበት ሰዓት እርሱ እና ጎረቤቶቹ ቤት አልባ የሆኑበትን እርምጃ ግራ የሚያጋባ ነው ይላል።

"እንደዜግነታችን እንኳ መጠለያ እንኳ አዘጋጅተውልን እዚህ ጋ እንኳ መቀመጥ ትችላለችሁ ባላሉበት ሁኔታ ነው ያፈረሱብን።

ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰብ ደግሞ የአካባቢው አስተዳደር "ለይዞታችን ካርታ እንሰጣችኋለን መረጃ አምጡ በማለት መረጃ ሲሰባሰብ ቆይቷል" በማለት ያስረዳሉ።

አንዳንድ ግለሰቦች እንደሚሉት ቤታቸው እንደሚፈርስ #ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ከ10 ቀን እንደማይበልጥና ይህም ቤት ፈልጎ ለመልቀቅ በቂ ጊዜ እንዳይደለ አስረድተዋል።

"መንግሥት በርቱ #ህጋዊ እናደርገላችኋለን እያለን እስካሁን ለመብራትና ውሃ የከፈልነው ብቻ ከመቶ ሺህ ብር ይበልጣል። ሆኖም ድንገት በሰባት ቀን ውስጥ ቤታችሁን አፍረሱ ተባልን። እኛ ማፍረስ ስላልቻልን መንግሥት እያፈረሰው ነው" ብለዋል።

ሌላኛዉ አስተያት ሰጭ እንደገለጹት ደግሞ "ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ። ከቤት ተባርራ ጎዳና ላይ ነች። ቤቱን ሲያፈርሱት እባካችሁ ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ ትንሽ ታገሱኝ ስል 'ምን አገባኝ ከእኔ #አልወለደች' ሲል አንደኛው ምላሽ ሰጠኝ። እኔም የሚሰማ መንግሥት ይኖራል ብዬ ለአቤቱታ ትቻት መጣሁ። ሜዳ ላይ በተወጠረ ሸራ ውስጥ ነው ያለችው። ምን እንደሆነች አላውቅም" ሲሉ የተሰማቸውን #ሐዘን ይገልፃሉ።

ትናንት ቤታቸዉ የፈረሰባቸዉ ግለሰቦች ዛሬ ጠዋት ተሰባስበዉ ወደ ኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሮ ቢያመሩም እሳቸዉን ማናገር አትችሉም ተብለው ወደ ክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ መላካቸውን ነግረውናል። ነገር ግን ከክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮም ያገኙት ምላሽ "ቤታችሁ ከመፍረስ አይድንም። ልንተባበራችሁ አንችልም" የሚል መሆኑን ገልጸውልናል።

አቤቱታ አቅራቢዎቹ በመቀጠል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ቢያመሩም "ጉዳያችሁን እዛዉ ጨርሱ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ጉዳይ ጣልቃ አይገቡም" የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸዉ ለቢቢሲ ተናገረዋል።

"መንግሥት ጎዳና የወጡትን #እንሰብስብ ሲል ደስ ብሎን እኛም ገንዘብ እያዋጣን ነበር። ነገር ግን በምትኩ ቤታችን የተቀመጥነውን #ወደጎዳና እያባረርን ነዉ። እቃ እራሱ ማውጣት አልቻልንም ከነቤታችን ነዉ እየፈረሰ ያለው" ብለዋል አስተያየት ሰጭዎቹ።

በዛሬው ዕለትም የማፍረስ ተግባሩ የቀጠለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰቦች በቤተ ክርስትያንና በመስኪዶች ተጠልለው ማደራቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ዙሪያ በኦሮሚያ ልዩ ዞን በሚገኙ ከተሞች የህገ ወጥ ግንባታ መስፋፋት እንዳለ በጥናት ማረጋገጡን የኦሮሚያ ክልል የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታወቆ እንደነበር ፋና ብሮድካስቲንግ ዘግቦ ነበር።

በዚህም በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር 67 ነጥብ 2 ሄክታር መሬት እና በቤት ደረጃ ከ12ሺ በላይ ቤቶች በህገወጥ መንገድ መገንባታቸውን መለየታቸውን ተገልጾ ነበር።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ህጋዊ_ሰነድ እና ማስረጃ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር 116 ደረሷል፦

ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር 116 መድረሱን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አሳወቀ።

እስከ ባለፈው ሳምንት ድረስ ህጋዊ ሰነድ እና ማስረጃዎችን ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ፣ ያላመሟሉ እና ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ በሚል የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ማሳወቁ ይታወሳል፤ ኤጀንሲው አያይዞም የተጠየቁትን ያላቀረቡ ተቋማትን በሚመለከት እስካላቀረቡ ድረስ የያዙትን ተማሪ ከማስጨረስ በቀር አዲስ ተማሪ መመዝገብ እንደማይችሉ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።

እስከ ባለፈው ሳምንት ህጋዊ ሰነድ እና ማስረጃ ሳያመሟሉ እና ምንም ሳያቀርቡ ቀርተው የነበሩት የተቋማት ቁጥር 74 እንደነበሩ ይፋ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 18 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ የተጠየቁትን ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ማቅረባቸውን ኤጀንሲው ገልጿል። ይህም ሙሉ ለሙሉ ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር ወደ 116 ደርሷል።

የቀሩት 58 ተቋማት ህጋዊ ሰነዶቹንና ማስረጃዎቹን እስቃላቀረቡ ድረስ አዲስ ተማሪ መመዝገብ እንደማይችሉ የተላለፈው ውሳን እንተጠበቀ መሆኑን እየገለጽን ያላቀረቡትን ለይተን ዝርዝራቸውን የምናሳውቅ ይሆናል።

የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከADEY የተሰጠ ምላሽ፦

🏷እኛ #Adey_Foreign_Employment_Agency የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚያውቀውን #ህጋዊ ኤጀንሲ ነን፤ ማንኛውም ህጋዊነታችንን ማረጋገጥ የሚፈልግ ሰው የምንሰራበት ቦታ ድረስ መጥቶ ማረጋገጥ ይችላል፤ የተባለው ነገር ስህተት ነው ሊታረም ይገባል ሲሉ ለTIKVAH-ETH ተናግረዋል።

ይህንንም መረጃ አያይዘው ልከዋል፦

PHON:-+251-11-551-70-80 or +251-11-551-83-79
email:-molsa_gov@yahoo.com
website:- www.mols.gov.et
Facebook:-Ministry of Labor and Social Affairs
Located in kirkos sub-city Wereda 8, Kazanchis

🏷ከአለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት በኩል የሚሰጥ ምላሽ ካለ ተከታትለን እናቀርባለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኮማንድ ፖስቱ ማስጠንቀቂያ!

<<በደቡብ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት እውቅና ሳይሰጣቸው ተሰቅለው የሚገኙ አርማዎችና ሰንደቅ ዓላማዎች በአስቸኳይ እንዲነሱ>> ሲል የደቡብ ክልል ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት #አስጠነቀቀ

ኮማንድ ፖስቱ ዛሬ በክልሉ መንግስት ራዲዮ ጣቢያ አማካኘነት ባስሳተላለፈው ማሳሰቢያ፤ ኮማንድ ፖስቱ በክልሉ አንዳንድ ዞኖች እና ወረዳዎች በህግ የማይታወቁ አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን፣ ባነሮችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) የሰቀሉ አካላት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሁለት ተከታታይ ቀናት ውስጥ በአስቸኳይ እንዲያነሱ ሲል አሳስቧል።

በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የክልሉን #ህጋዊ ሰንደቅ ዓላማ በማውረድና የመንግስት ተቋማት የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በመንቀል በምትኩ እውቅና የሌላቸውን የመትከል ሙከራዎች መከናወናቸውን ኮማንድ ፖስቱ በመግለጫው አስታውቋል።

በመሆኑም «ህገ ወጥ»ያላቸውን አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በተሰጠው የሁለት ቀናት የጊዜ ገደብ ውስጥ በማንሳት ህጋዊ» የሆኑትን በአስቸኳይ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ሲል ኮማንድ ፖስቱ አሳስቧል።

በተጨማሪም መግለጫው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በክልሉ ሁሉም ዞኖች ፣ ወረዳዎች ፣ በከተሞች አና በቀበሌዎች የመስተዳድር ክልል ውስጥ የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ የግል ተቋማት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች #ትክክለኛ የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) እና ህጋዊ የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ብቻ እንዲጠቀሙ አመልክቷል።

እንዲሁም በተለያዩ የህትመት ውጤቶች የተዘጋጁና በህግ የማይታወቁ አርማዎችንና ሰንደቅ ዓላማዎችን መልበስ ፣ ይዞ መዘዋወር ፣ መሰቀልም ሆነ መለጠፍ በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል አስታውቋል። በተጠቀሰው ቀናት ውስጥ መመሪያውን ተፈፃሚ በማያደርጉ ግለሰቦች፣ ተቋማት እና ድርጅቶች ላይ በየደረጃው በተዋቀሩ የኮማንድ ፖስት አማካኝነት #ህጋዊ_እርምጃ ይወሰዳል ሲል አስጠንቅቋል።

በደቡብ ክልል የሀዋሳ እና የወላይታ ሶዶ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በክልል መደራጀትን ለመጠየቅ በተዘጋጁ ሰልፎች ላይ ወደፊቱ ለሚመሰርቷቸው ክልሎች በሰንደቅ ዓላማነት ሊያገለግሉ ይችላሉ በሚል የዘጋጁቸውን አርማዎችን ሲያውለበልቡ እንደነበር አይዘነጋም። በተለይም በሲዳማ ዞን ከባለፈው ሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓም ወዲህ በዞኑ የሚገኙ አንዳንድ የወረዳዎች መስተዳድር ፅህፈት ቤቶች የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሚሉ የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በጎዳናዎች በመትከል በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴ አውታሮች እያሰራጩ እንደሚገኙ ይታወቃል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደቡብ ክልል ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት!
.
.
ኮማንድ ፖስቱ በክልሉ አንዳንድ ዞኖች እና ወረዳዎች በህግ የማይታወቁ አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን፣ ባነሮችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) የሰቀሉ አካላት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሁለት ተከታታይ ቀናት ውስጥ በአስቸኳይ እንዲያነሱ ሲል አሳስቧል።

በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የክልሉን #ህጋዊ ሰንደቅ ዓላማ በማውረድና የመንግስት ተቋማት የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በመንቀል በምትኩ እውቅና የሌላቸውን የመትከል ሙከራዎች መከናወናቸውን ኮማንድ ፖስቱ በመግለጫው አስታውቋል።

በመሆኑም «ህገ ወጥ»ያላቸውን አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በተሰጠው የሁለት ቀናት የጊዜ ገደብ ውስጥ በማንሳት ህጋዊ» የሆኑትን በአስቸኳይ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ሲል ኮማንድ ፖስቱ አሳስቧል።

በተጨማሪም መግለጫው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በክልሉ ሁሉም ዞኖች ፣ ወረዳዎች ፣ በከተሞች አና በቀበሌዎች የመስተዳድር ክልል ውስጥ የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ የግል ተቋማት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች #ትክክለኛ የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) እና ህጋዊ የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ብቻ እንዲጠቀሙ አመልክቷል።

እንዲሁም በተለያዩ የህትመት ውጤቶች የተዘጋጁና በህግ የማይታወቁ አርማዎችንና ሰንደቅ ዓላማዎችን መልበስ ፣ ይዞ መዘዋወር ፣ መሰቀልም ሆነ መለጠፍ በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል አስታውቋል። በተጠቀሰው ቀናት ውስጥ መመሪያውን ተፈፃሚ በማያደርጉ ግለሰቦች፣ ተቋማት እና ድርጅቶች ላይ በየደረጃው በተዋቀሩ የኮማንድ ፖስት አማካኝነት #ህጋዊ_እርምጃ ይወሰዳል ሲል አስጠንቅቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ልክ ጎንደር እንደተደረገው በደብረብርሃን ከተማም ክልከላዎች ተጣሉ።

ደብረ ብርሃን ከተማ ውስጥ #ህጋዊ_መታወቂያ ሳይዙ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን ህጋዊ መታወቂያ ሳይዝ የተንቀሳቀሰ ግለሰብም ሆነ ቡድን በህግ ቁጥጥር ስር ይውላል ተብሏል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኮማንድ ፖስት " የከተማዉን ሰላምና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ " እንዲቻል በሚል ክልከላዎችን መጣሉን አሳውቋል።

ክልከላዎቹ ምንድናቸው ?

1. በከተማው ያሉ ማንኛውም መጠጥ ቤቶችና ጭፈራ ቤቶች እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ዉጭ አገልግሎት መስጠት ተከልክለዋል።

2. በከተማው የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለ 3 እግር ባጃጆች ከንጋቱ 12:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2:00  ሰዓት ዉጭ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

3. በከተማ አስተዳደሩ ለጸጥታ ማስከበር ተልዕኮ ከተሠጠው   የፀጥታ ኃይል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

4. ድምፅ አልባ መሳሪያዎችን ስለታማ የሆኑ እንደ ጩቤ ፣ ገጀራ ፣ አንካሴ ፣ ጦርና ፌሮ ብረት ወዘተ የመሳሰሉትን ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

5. በህግ የሚፈለጉ ወይም ተጠርጣሪዎችን ሽፋን የሰጠ ፣ የደበቀ ፣ የሀሰተኛ መረጃ ሰጥቶ ያሰመለጠ ፣ የፀጥታ ሀይሎችን የህግ ማስከበር ተልዕኮ ማደናቀፍ ማወክ በህግ ተከልክሏል።

6. በማንኛውም ቦታና ስዓት ጥይትም ሆነ ሮኬት ርችት መተኮስ በጥብቅ ተከልክሏል።

7. በተከለከሉ ቦታዎች በእምነት ተቋማት፣ በገቢያዎች፣ ህዝብ በብዛት በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች ፣ በሆቴሎች፣ መጠጥ ቤቶችና ግሮሰሪዎች፣ ልዩ ልዩ መዝናኛ ቦታዎች ጦር መሳሪያ ይዞ መገኘትና መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

8. የሠራዊቱን ሚሊተሪ (አልባሳት) ከሰራዊቱ አባላት ውጭ መልበስ ተከልክሏል የልዩ ኋይል ፣ የፓሊስ ፣ የመከላከያ ሠራዊት ፣ የፌዴራል ፓሊስ ልብስ መልበስ ተከልክሏል።

9 . ያልተፈቀደ ስብሰባዎችን ያለ መንግስት እውቅና ውጭ ስብሰባ ማድረግ ፣ ያልተፈቀደ ሰልፍ ማድረግ ፣ መንገድ መዝጋት  ተከልክሏል።

10. አድማ መቀስቀስ፣ ማድረግና ማስተባበር እንዲሁም መደበኛ ስራን ማስተጓጎል በጥብቅ ተከልክሏል።

11. የአማራን ህዝብ ከጥቃትና ከውርደት ለመታደግ መስዋትነት የከፈሉ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ፣ የአማራ ልዩ ኃይል አባላት በተፈጠረው የመረጃ ክፍተት ከተለያየ አካባቢ ተነስተው ወደ ከተማው የገቡ በከተማው በተዘጋጀው ማረፊያዎች እንዲሰባሰቡ ማሳሰቢያ ተላልፏል። ከዚህ ውጭ በተናጠልም ሆነ በቡድን መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እና ጥይት መተኮስ ተከልክሏል።

12. ፀጉረ ልዉጥ/አጠራጣሪ ሰው ከቤቱ ያሳደረ ፣ያከራየ፣ በሆቴሉ አልጋ ያስያዙ  እንዲሁም ለሚመለከተዉ የፀጥታ አካል ጥቆማ ያልሰጠ በህግ የሚጠይቅ ይሆናል ተብሏል።

13. በከተማው ውስጥ ህጋዊ መታወቂያ ሳይዙ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው ህጋዊ መታወቂያ ሳይዝ የተንቀሳቀሰ ግለሰብም ሆነ ቡድን በህግ ቁጥጥር ስር ይውላል።

14. በከተማው በተፈናቃይ ካምፕ የምትገኙ ተፈናቃይዎች በማንኛውም ሰአት ወቅታዊ ሁኔታው እስከሚስተካከለ ድረስ ከካምፕ ውጭ መገኘት ፈጽሞ ተከልክለዋል።

መረጃው ደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር የጸጥታው ምክር ቤት ኮማንድ ፖስት ነው።

@tikvahethiopia