TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"የትግራይ ህዝብ #ህጋዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት እንቅስቃሴ #ሊረበሽ አይገባም"--ዶክተር #ደብረጽዮን_ገብረሚካኤል

.
.
የትግራይ ህዝብ ህጋዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ሳይረበሽ #በልማቱ ላይ ሊያተኩር እንደሚገባ የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ገለጹ።

ምክትል ርዕሰ-መስተዳደሩ ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት የመከላከያ ሰራዊት ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ህጋዊና #ኃላፊነቱንም ለመወጣት የሚያስችል ነው።

በመሆኑም የክልሉ ህዝብ ይሄንን ተገንዝቦ ያለምንም መረበሽ የልማት ስራውን #በተረጋጋ መልኩ ማከናወን እንዳለበት አሳስበዋል።

ህዝቡ የሚያነሳው የህገ-መንግስት ይከበርልን ጥያቄ እራሱ ከማክበር የሚጀምር መሆኑንም ምክትል ርዕሰ-መስተዳደር በመግለጫቸው አመልክተዋል።

የክልሉን ሰላምና ጸጥታ የማስከበርን ጉዳይም ህዝቡ በፈጠረው አደረጃጀት አንድነቱን ማስቀጠል እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታት ባደረጉት የጋራ ስምምነት የሁመራ ኦምሃጀር መንገድ መከፈትም ለሁለቱ ህዝቦች ግንኙነት ጠቃሚ እንደሆነ ዶክተር ደብረጽዮን ተናግረዋል።

መንገዱ የሁለቱን ሃገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ከማሳደግ ባለፈው ቀጣይ ህጋዊ መስመር ለማስያዝም ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአማራ ክልል ሙሉ በሙሉ በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ እንደገለጹት፥ ከሰሞኑ በተፈጸመው ድርጊት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እጃቸው አለበት የተባሉ ተጠርጣሪዎችን የክልሉ የጸጥታ ኃይል ለህግ እያቀረበ ነው።

ድርጊቱ ከተፈጸመበት ቀን እስከ ትናንትናው ዕለት ድረስም ከ300 በላይ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኮሚሽነር አበረ ገልጸዋል። ግለሰቦችን ወደ ህግ ለማቅረብ በተደረገው እንቅስቃሴም ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም ነው ያሉት ኮሚሽነሩ።

የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንና ማጣራቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን የተናገሩት ኮሚሽነሩ፥ ከተያዙት መካከል ጉዳያቸው ተጣርቶ የሚለቀቁ እንደሚኖሩም አመላክተዋል።

በነባሮች እና አዲስ በሰለጠኑት የልዩ ኃይል አባላት መካከል ልዩነት እንዳለ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ክልሉ ጠንካራ የጸጥታ ኃይል እንዳይኖረው የተሰራ የፖለቲካ ሴራ እንጂ ምንም አይነት ልዩነት እንደሌለም ነው የተናገሩት።

ህጋዊ ትጥቅ ያላቸውን ግለሰቦች ትጥቅ የማስፈታት ስራ ተጀምሯል እየተባለ የሚሰራጨው ወሬ የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ ታስቦ የሚናፈስና ከእውነት የራቀ አሉባልታ መሆኑንም ኮሚሽነር አበረ ተናግረዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ ስጋት ውስጥ እንዳይገባም መልዕክት ያስተላለፉት ኮሚሽነሩ ፥ ክልሉ ሙሉ በሙሉ #በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

Via #EPA
🗞ቀን 22/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
'የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተረጋጋ ሁኔታ ትምህርታችሁን ተከታተሉ'

ከምርጫ ጋር በተገናኘ ትላትን የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለ @tikvahuniversity እንዳሳወቀው የዩኒቨርሲቱ ተማሪዎች በምን መልኩ በምርጫ ይሳተፉ ? በሚለው ላይ እስካሁን በሚኒስቴሩ ደረጃ ምንም የተወሰነ ውሳኔ የለም።

ነገር ግን የተለያዩ ኒቨርሲቲዎች በውስጥ ማስታወቂያ ከምርጫው በፊት 1 ሳምንት ከምርጫው በኃላ 1 ሳምንት ተማሪዎቻቸውን እንደሚበቱ እያሳወቁ ይገኛሉ።

ሌሎች ደግሞ በውስጥ ማስታወቂያቸው "ከምርጫው በፊት ተማሪዎች ይበተናሉ" ስለሚባለው ጉዳይ የሚያውቁት ነገር እንደለ እንዲሁም የሚናፈሰው መረጃም ውሸት እንደሆነ በመግለፅ ተማሪዎች ተረጋግተው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እያሳበቡ ይገኛሉ።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሆናችሁ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ተማሪዎች በምን መልኩ ነው በምርጫው የሚሳተፉት ? ለሚለው ጉዳይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ መረጃ ሲላክልን የምናሳውቃችሁ ይሆናል።

እስከዚያው ግን በተለያዩ የቴሌግራም ቻናሎች ላይ ሆነ የፌስቡክ ገፆች ላይ የሚወጡትን የተለያዩ መረጃዎች በመቀባበል ሳትረበሹ #በተረጋጋ ሁኔታ ትምህርታችሁን እየቀጠላችሁ ይፋዊ የሆነውን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ትጠብቁ ዘንድ አደራ እንላለን።

አዲስ የዩኒቨርሲቲ ተመዳቢ ተማሪዎች በተመለከተ አስፈላጊውን መረጃ ከሚመለከታቸው አካላት በጠየቅ እናሳውቃለን። በተጨማሪም የ2013 ሀገር አቀፍ ፈተና ሂደትን ከትምህርት ሚኒስቴር ጠይቀን እናሳውቃለን።

ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባሉበርካታ የተጣረሱ መረጃዎች እንዳትደናገሩ።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
#ምርጫ2013

በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ፦

- የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ መዘግየት ፣
- በድምፅ አሰጣጥ ላይ የሚታይ መደነጋገር፣
- ሰዓት አለማክበር፣
- የኮቪድ-19 ፕሮቶኮል አለመጠበቅ፣
- ረጃጅም ሰልፎች (በፍጥነት አለመሄድ) ፣
- የሰልፍ ተራ አለመጠበቅ፣
- የምርጫ ቁሳቁስ መቀያየር
- ቀልጥፍ ያለ መስተንግዶ ክፍተት
- መራጮች ምርጫ ካርዳቸውን የወሰዱበትን መታወቂያ ሳይዙ መሄድ
- "እከሌን ምረጡ" የሚል ቅስቀሳ ለማድረግ መሞከር የመሳሰሉት ችግሮች ከመስተዋላቸው በዘለለ የምርጫ ሂደቱ #በሰላም እየተካሄድ መሆኑን ከአዲስ አበባና ከክልል የምርጫ ጣቢያዎች የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።

የ Tikvah - Ethiopia አባላት በተመለከቷቸው የምርጫ ጣቢያዎች እድሜያቸው የገፋ ዜጎች ፣ እናቶች አባቶች ድምፅ ለመስጠት ተሰልፈው ተመልከተዋል። ነፍሠ ጡሮች፣ ልጅ የታቀፉ እናቶች ተሰልፈው ድምፅ ሲሰጡ አስተውለዋል።

በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ በፀጥታ እና በሰላም ረገድ ምንም ጥቆማ ከአባላቶቻችን አልተላከም፤ ሁሉም ሂደት #በተረጋጋ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገልፀውልናል።

Photo Credit : Tikvah Family (Addis Ababa)

@tikvahethiopia