TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ጦላይ ማሰልጠኛ ጣቢያ ሥልጠና ላይ ያሉ ከ150 በላይ የኦነግ የቀድሞ ታጣቂዎች መመረዛቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ችግሩ የተከሰተው ትናንት በቁርስ ሰዓት በሚጠጡት ሻይ ነው፡፡ 129ኙ ትናንቱን ለሕክምና ወሊሶ ሆስፒታል የገቡ ሲሆን 20ዎቹ ደሞ ዛሬ እንደገቡ የሆስፒታሉን ሐኪም ተናግረዋል፡፡ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት እንደታየባቸውም ተገልጧል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ኮምኒኬሽን ቢሮ ዛሬ ከቀትር በኋላ ባወጣው መግለጫ ሁሉም ታማሚዎች በጥሩ ጤንነት ሁኔታ እንደሚገኙ ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ የህመማቸው መንስዔ እየተጣራ ቢሆንም የምግብ መመረዝ እንደሆነ የተወራው ግን #የተሳሳተ መረጃ ነው ሲል አስተባብሏል፡፡

በተያያዘ ዜና ...

ዛሬ ማለዳ የወሊሶ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን ሪፖርተር አስነብቧል፡፡ የአድማው መንስዔ ጦላይ ማሰልጠኛ ጣቢያ ያሉ የኦነግ የቀድሞ ታጣቂዎች ተመርዘዋል የሚል ዜና መሰራጨቱ ነው፡፡ በአድማው ሳቢያ ከወሊሶ-አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ-ወሊሶ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል፡፡ ወጣቶች መንገዱንም ዘግተዋል፡፡ በከተማዋ የመንግሥት ተቋማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጭ ተቋማትም አገልግሎታቸውን አቋርጠዋል፡፡

Via #BBC(#WAZEMA)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዐለም ዐቀፉ ድንበር የለሽ ሐኪሞች ቡድን ለጌዲዖ ተፈናቃዮች አስቸኳይ ሰብዓዊ አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡ ድርጅቱ ባሰራጨው መግለጫ ሌሎች ነፍስ አድን ድርጅቶች ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቋል፡፡ ባለፈው መጋቢት በጌዲዖ ተፈናቃዮች ባደረገው ጥናት ከ5 ዐመት በታች ያሉ ሕጻናትና ነፍሰ ጦሮች የገጠማቸው ከባድ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት አስቸኳይ የሚባለውን ወለል ያለፈ መሆኑን አረጋግጧል፡፡ አሁን ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የተመጣጠነ ምግብ እያቀረበ መሆኑን ገልጧል፡፡ ለ200 ከ5 ዐመት በታች ሕጻናትም ሕክምናና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቧል፡፡ በቀጣይ በስደተኛ መጠለያዎች የንጽህና ንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ላይ ይሰራል፡፡

Via #wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መንግስት ላገለገሉ ተሽከርካሪዎች ያደርግ የነበረውን የግብር ቅናሽ አቆመ‼️
.
.
መንግስት ያገለጉሉ መኪናዎች ከውጭ ሲገቡ ያደርግ የነበረውን #የቀረጥ_ስሌት ቅናሽ ከትላንት ጀምሮ አቆመ።

መንግስት ከዚህ ቀደም ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ላለማበረታታት እንደሚሰራ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል። ከትላንት ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል በተባለ የገቢዎች ሚኒስቴር አዲስ መመሪያም ያገለገሉ መኪናዎች ሀገር ውስጥ ሲገቡ ለመኪናዎቹ ቀረጥ ሲከፈል ፣ ከተሽከርካሪዎቹ ዋና ዋጋ ላይ የአገልግሎት ዋጋ ተብሎ እስከ 30 በመቶ ተቀንሶ የይደረግ የነበረውን የቀረጥ ስሌት እንዲተው አድርጓል።

በዚህም መሰረት ከአሁን በሁዋላ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ሀገር ውስጥ ሲገቡ የሚከፍሉት ቀረጥ የሚሰላው ከዋና ዋጋቸው ላይ መኪናው ላገለገለበት እስከ 30 በመቶ ተቀንሶ ሳይሆን በዋና ዋጋቸው ይሆናል ማለት ነው። ይህም ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡበት የነበረውን ማበረታቻ በእጅጉ ይጎዳዋል። የሀገር ውስጥ የመኪና ዋጋም ላይ ከፍተኛ ጭማሬን ሊያስከትል እንደሚችል ይጠበቃል።

መመሪያው ከመውጣቱ በፊት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን አዘው መመሪያው እስኪወጣ ያልገባላቸው አስመጪዎች በምን እንደሚታዩ ገና ግልጽ አልሆነም። መንግስት ይህን የታክስ አሰራር በማስቀረት ለነዳጅ ግዥ የሚያወጣውን ምንዛሬ ለመቀነስ እንዳሰበም ይነገራል።

Via #wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከውጭ ከሚገቡ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ላይ የተነሳው የ30 በመቶ የዕርጅና ግብር ቅነሳ መመሪያው ከመውጣቱ በፊት የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን አይመለከትም- ብሏል የገቢዎች ሚኒስቴር፡፡ መመሪያው ከመውጣቱ በፊት ተገዝተው ወደ ሀገር ውስጥ እየተጓጓዙ ያሉትንና ለመጓጓዝ ዝግጁ የሆኑትን እንደማይመለከትም አስታውቋል፡፡ የባንክ ፈቃድ ማረጋገጫ ያገኙ ያገለገሉ እቃዎችን እንዲሁም ያለውጭ ምንዛሬ ክፍያ ተገዝተው ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት የተጫኑ ያገለገሉ እቃዎችም መመሪያው እንደማይመለከታቸው ተሰምቷል። አንዳንድ አስመጭዎች እንደሚሉት መመሪያው ተግባራዊ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወደ ሀገር ውስጥ በሚገቡ ያገለገሉ መኪናዎች ላይ በትንሹ የጨመረው ቀረጥ ከ80 ሺህ ብር በላይ ደርሷል።

Via የገቢዎች ሚኒስቴር/#wazema/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዐቃቤ ሕግ በሙስና ተከሳሾቹ እነ ጀኔራል ክንፈ ዳኛው ላይ ምስክሮችን ለችሎት ሲያሰማ ውሏል፡፡ ትናንት የጀመረው የምስክሮችን ቃል የማድመጥና ማስረጃዎችን የመመርመር ሂደት ለመጭዎቹ 10 ቀናት ይቆያል- ብሏል ዐቃቤ ሕግ በፌስቡክ ገጹ ባሰፈረው መረጃ፡፡ ኮሎኔል በርሃ ወ/ሚካዔል፣ ሌ/ኮሎኔል ስለሺ በዛና ወ/ሮ ሲሳይ ገ/መስቀል በሌሉበት ነው ምስክሮች እየተሰሙባቸው ያሉት፡፡ ችሎቱ ምስክር እሰማባቸው ካሉት ተከሳሾች መካከል በኢምፔሪያል ሆቴል ሽያጭ የተከሰሱት ባለሃብቱ ኤርሚያስ አመልጋ ይገኙበታል፡፡

Via #wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና...

አምቦ ዩኒቨርስቲ ባለፈው ሳምንት ለሞተው ተማሪ ቤተሰቦች ሐዘኑን በይፋ መግለጡን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል፡፡ ተማሪው ባለፈው ሐሙስ ጉዳት የደረሰበት በተማሪዎች መካከል በተነሳ ጠብ ሲሆን በሆስፒታል ሲረዳ ቆይቶ ቅዳሜ ዕለት ነው ሕይወቱ ያለፈው፡፡ ሟቹ በወሊሶ ካምፓስ የፐብሊክ አድሚንስትሬሽንና ዲቨሎፕመንት ማኔጅመንት 2ኛ ዐመት ተማሪ ነበር፡፡

Via #wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ያሬድ ዘሪሁንን ጨምሮ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት የቀድሞ ሃላፊዎችና ሠራተኞች በዐቃቤ ሕግ የቀረቡባቸው ምስክሮች ቃል ውድቅ እንዲያደርግላቸው ችሎቱን ጠይቀው ተቀባይነት አላገኙም፡፡ ተከሳሾቹ ዐቃቤ ሕግ የምስክሮች ጥበቃ አዋጅን ያላግባብ ስራ ላይ አውሏል፤ ለምስክሮች ጥያቄ እንዳናቀርብ ታግደናል፤ የቀድሞ ተቋማችን ባልደረቦች ከሕግ ውጭ በእኛ ላይ ምስክርነት መስጠታቸው ስህተት ነው ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ ችሎቱ ግን አቤቱታው በይግባኝ ለመቅረብ የሚገባው አይደለም በማለት ጉዳዩን እንደዘጋው ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በፌስቡክ ገጹ አስፍሯል፡፡

Via #wazema/የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ/
🗞ቀን 13/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሌላ በኩል...

ባለፈው ሐምሌ #በሱማሌ_ክልል በተከሰተው ሁከት ከከሰስኳቸው ተከሳሾች መካከል ከድር አብዲ እስማኤልን #በስህተት ነው የከሰስኳቸው- ብሏል ዐቃቤ ሕግ፡፡ ተከሳሹ አርሶ አደር እንጅ የመንግሥት ባለስልጣን እንዳልነበሩ ባላፈው ለችሎቱ ካስረዱ በኋላ ዐቃቤ ሕግ ባደረገው ማጣራት ነው፡፡ ችሎቱም ተከሳሹ እንዲለቀቁ ማዘዙ ተሰምቷል፡፡ ተከሳሽ አብዲኑር መሐመድ አሕመድ በበኩላቸው የአያቴ ስም የሱፍ ነው ያሉ ሲሆን ሃኒ ሀሰን ደሞ ስማቸው ዘምዘም መሆኑን ጠቅሰው ተከራክረው ነበር፡፡ ሀሰን አይዲድ በደል ራጌ ማዕረጌ ሻምበል አይደለም፤ ምክትል ኢንስፔክተር ነኝ ሲሉ በስህተት መከሰሳቸውን አቤት ብለው ነበር፡፡ ዐቃቤ ሕግ ግን ስማቸውን ሆን ብለው ስለሚቀይሩ ነው በማለት ተከራክሯል፡፡ የችሎቱ ብያኔ ሐምሌ 11 ይጠበቃል፡፡

Via #wazema/የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ/
🗞ቀን 13/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በርካቶች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው...

ፖሊስ በአዲስ አበባ በርካታ ሰዎችን በቁጥጥር እያዋለ መሆኑን DW የከተማይቱን ነዋሪዎች ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ/አብንና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትህ ፓርቲ/አዜማ አባላት እንደታሰሩም ተጠቁሟል፡፡ ጸጥታ ሃይሎች በከተማዋ #ጥብቅ ቁጥጥር እያደረጉ እንደሆነ የዐይን እማኞች ገልጸዋል፡፡

Via #dw/#wazema
🗞ሰኔ 20/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን መዝጋቷ በቀን 4.5 ሚሊዮን ዶላር ያሳጣታል ብሏል- ኔት ብሎክስ የተሰኘው የሀገራትን ኤንተርኔት መቋረጥ የሚከታተለው ዐለም ዐቀፍ ድርጅት፡፡ ከቅዳሜ ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ የተቋረጠው ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ አልተለቀቀም፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የንግግር ነጻነትን የሚያበረታቱ እርምጃዎችን መውሰድ በጀመሩ ልክ በዐመቱ ኢንተርኔት ማቋረጣቸውን እንደሚያወግዙት የድርጅቱ ዋና ሃላፊ አልፕ ቶከር ለአልጀዚራ ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በሰሞኑ የባለ ሥልጣናት ግድያ በቂ መረጃ አግኝተው ሐዘናቸውን መግለጽ ሲገባቸው፣ የመረጃ ምንጮችን መዝጋት ክብራቸውን ማሳጣት ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

Via #wazema
🗞ሰኔ 20/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia