TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የብሮድካስት ባለስልጣን ማስጠንቀቂያ...

የብሮድካስት ባለሥልጣን በኢኦተ ቤተክርስቲያን ጉዳይ ለኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ማስጠንቂያ ሰጠ። ባለስልጣኑ ጣቢያው በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅና፣ በተመጣጣኝ ስፋት እና በተመሣሣይ የሥርጭት ሰዓት የቤተክርስቲያኗን ቅሬታ እንዲያስተላልፍም አዟል።

ባለስልጣኑ ውሳኔውን ያስተለፈው፣ ኃሚካኤል ታደሰ የተባሉ ግለሰብ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በፍቸና በገብረ ጉራቻ ከተሞች ባዘጋጃቸው መድረኮች የተናገሩትን ንግግር ጣቢያው ማስተላለፉን ተከትሎ ነው።

ደብዳቤውን ከላይ ተመልከቱ!

#EotcTV #ELU
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
'ምህላ ታውጇል'

ዛሬ 3 በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸውን ተከትሎ ምእመናን በጤና ሚኒስቴር በኩል የሚሰጡ መመሪያዎችን እንዲተገብሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አሳስበዋል።

የቤተክርስትያኗ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በቀሪው የዐቢይ ፆም ጊዜያት በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አድባራት እና ገዳማት የምህላ ጸሎት እንዲደረግም አውጀዋል፡፡

#EOTCTV
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬ ጠዋት ውሎው የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትትን የመክፈቻ መልእክት ያዳመጠ ሲሆን፦ - ብጹዕ አቡነ ኤልያስ - ብጹዕ አቡነ ማቴዎስ - ብጹዕ አቡነ ማርቆስ - ብጹዕ አቡነ አብርሃምን - ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ - ብጹዕ አቡነ ፊልጶስ - ብጹዕ…
#Update

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባዔ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የግንቦት 19/2013 ክንውን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡ ሲሆን ፤ በመግለጫቸው ተከታዮቹ ነጥቦች ተነስተዋል ፦

- በትናንትናው ዕለት ውሳኔ የሰጠባቸውን 2 አጀንዳዎች ቃለ ጉባዔ ቀርቧል፡፡ በዚህም የቅዱስነታቸውን የመክፈቻ ንግግር ቅዱስ ሲኖዶስ #አጽድቆታል፡፡

- ሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክቶ በሀገሪቱ በሚታዩት ወቅታዊ ችግሮች የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ስደትና መፈናቀል ዙርያ በሰፊው ተወያይቶ የመፍትሔ ሐሳብ የያዘ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ውሳኔው በዝርዝር በሚሰጠው መግለጫ ይገለፃል ብለዋል።

- የቤተክርስቲያን የአምልኮ ሥፍራ የሆኑት የመስቀል እና የጥምቀት ቦታዎች አስመልክቶ ሰፊ ውይይት በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ችግሩ የሚፈታበት ውሳኔ አሳልፏል፤ የውሳኔው ዝርዝር በአጠቃላይ መግለጫው ይቀርባል ብለዋል።

- በሀገሪቱ በተለያዩ ጊዜያት እደረሱ ያሉ ችግሮችን አስመልክቶ ሦስት ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ለቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ አዘጋጅተው እንዲያቀርቡ መርጧል፡፡

- በመላው ሀገሪቱ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ባሉት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት በሙሉ ስለ ሀገሪቱ ሰላም ጸሎተ ምኅላ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ : telegra.ph/EOTC-TV-05-27 #EOTCTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከቀናት በፊት ስምምነት ላይ የደረሱት አባቶች ስምምነቱን እንዲሁም ቀኖናውን ደግመው መጣሳቸውን አሳወቀች። ይህንን በተመለከተ ዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ ፅህፈት ቤት መግለጫ ሰጥቶ ነበር። በመግለጫው ብፁዕ አቡነ አብርሃም ተከታዩን ብለዋል ፦ " ከሁለት ቀናት በፊት ሰላም መፈጠሩን ማወጃችን ይታወሳል። በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ የምንሰማቸው ነገሮች…
#Update

ዛሬ የካቲት 11 ቀን 2015 ዓ.ም እነ ብፁዕ አቡነ ሣዊሮስ ስምምነቱን ሳይሸራረፍ እንደሚቀበሉና ተግባራዊ እንደሚያደርጉ በቅዱስ ሲኖዶስ በመገኘት ቃላቸውን ሰጥተው አረጋግጠዋል ስትል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አሳውቃለች።

እነ ብፁዕ አቡነ ሣዊሮስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር አብይ አሕመድ በተገኙበት የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ/ም በተደረገው ውይይት የተስማሙባቸውን (10) ዐሥር ነጥቦች ያለመሸራረፍ ለመፈጸም እንዲሁም ቀጣዩን ተግባር በተመለከተ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት ለማከናወን ተስማምተናል ሲሉ በቅዱስ ሲኖዶስ ፊት በመገኘት ቃላቸውን መስጠታቸው ተገልጿል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በውግዘት የተለዩ 17 "የቀድሞ" አባቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት በተደረሰው ስምምነት መሰረት 10ሩን የስምምነት ነጥቦች መቀበልላቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ለብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) አስገብተዋል ሲል የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል። ደብዳቤውን ያስገቡት 17 ሲሆኑ አንዱ…
#ሰበር_ዜና

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  የሦስቱን አባቶችና የ20ቹን መነኮሳት ውግዘት ከዛሬ 21/07/2015 ዓ/ም ጀምሮ ማንሳቱን በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

ውግዘቱ የተነሳላቸው ቤተ ክርስቲያን በሰጠቻቸው ማዕረግ እንዲጠሩም ገልጿል።

በዚህ መሠረት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ተብለው እንደሚጠሩና ወደ ነበረ የአባትነት ኃላፊነታቸው የሚመለሱ ሲሆን በይቅርታ የተመለሱት በቁጥር 20ዎቹ መነኮሳትም ቤተ ክርስቲያን በሰጠቻቸው የክህነት አገልግሎት እንዲያገለግሉ ሆኖ በምንኩስና ስማቸው እንዲጠሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወደፊት ዕርቀ ሰላም እንዲፈጠር ተስፋችን ብርቱ ነው " - ቅዱስ ፓትርያርኩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በመቐለ ምን አሉ ? ቅዱስ ፓትርያርኩ ፦ " በትግራይ ላይ የተፈፀመው ፤ የወረደው መቅሰፍት አዲስ ነገር ነው የሆነብን ሁላችንም ፤ እንጃ በዓለም ተደርጓል፣ አልተደረገም እስከማለት ድረስ ነው…
ፎቶ፦ በትላንትናው ዕለት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተመርቶ ወደ መቐለ ያቀናው የሰላም ልኡክ ዛሬ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል።

ልኡኩ አዲስ አበባ ቦሌ ኢንተርናሽናል ኤርፖርት ሲደርሱ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተከህነትና ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የመምሪያ ሓላፊዎች ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ካህናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የኢኦቴቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት እንደዘገበው ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ ክልሉ ሲደርሱ በትግራይ ክልል በሚገኙ ብፁዓን አባቶች፣ ካህናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ምንም ዓይነት መንፈሳዊ የአቀባበልም ይሁን የሽኝት ሥነ ሥርዓት እንዳልተደረገላቸው ጠቅሷል።

ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ጭምር የኪዳን ጸሎትን በተዘጋ የቤተክርስቲያኒቱ ደጅ ላይ ለማድረግ ተገደዋል ሲል በዘገባው ጠቅሷል።

በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራው ልዑክ ፥ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን እንዲሁም አትሌት ደራርቱ ቱሉና ሌሎች አባላትን አካቶ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሰረት በጦርነት ምክንያት ለተፈናቃሉ ወገኖች ድጋፍ ለማድረግና በክልሉ ከሚገኙ የሃይማኖቱ መሪዎች ጋር ለመወያየት ወደ ትግራይ ክልል መቐሌ ያቀናው በትላንትናው ዕለት እንደነበር ይታወሳል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia
" ይዞ መገኘት የሚቻለው የፌዴራል እና የቤተ ክርስቲያን አርማ ያለበትን ሰንደቅ ዓላማ ብቻ ነው " - ብፁዕ አቡነ አብርሃም

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የደመራ በዓልን አስመልክቶ መልእክት አስተላለፉ።

ብፁዕነታቸው " በበዓሉ ላይ የሚፈትኑ ጉዳዮች ሊገጥሙን ስለሚችሉ በትዕግስት ማለፍ አለብን " ብለዋል።

በዕለቱ በይበልጥ ሰዓትን ማክበር ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጠው አሳስበዋል።

ብፁዕነታቸው የመግቢያ ባጅ እደላው በሕግና በሥርዓት ትኩረት ተሰጥቶት የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል።

ሰንደቅ ዓላማን በተመለከተም የፌዴራል እና የቤተ ክርስቲያን አርማ ብቻ ያለበት መሆን እንደሚገባውና ርችት መተኮስ የቤተ ክርስቲያን ሥርዐት ባለመሆኑ እንደማይፈቀድ ገልጸዋል።

የቲሸርት አለባበስ በተመለከተም " ተንኳሽ መልእክት መጠቀም አይገባም " ያሉት ብፁዕነታቸው በየመንደሩና በየአጥቢያው በሚከበሩ በዓላት ላይም ጥንቃቄ ያስፈልጋል ብለዋል።

በበዓሉ ላይ የተፈቀደለት አስተናባሪ ብቻ የሚያስተናግድ ሲሆን ያልተፈቀደለት አካል ሲንቀሳቀስ ቢገኝ በወንጀል ያስጠይቃል ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ ባለፈ በመርሐ ግብሩ ላይ መሪዎች እና ተናጋሪዎች በተፈቀደላቸው ሰዓት እንዲጠቀሙ አሳስበዋል።

በመጨረሻም ለመርሐ ግብሩ መሳካት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አባታዊ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በዕለቱ የሙስሊም ወገኖቻችን የሚያከብሩት በዓል ስላላቸው በመከባበር እና በመተባበር በዓላቱን ማክበር ይገባል ሲሉም ጨምረው አሳስበዋል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በዓሉን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት ፤ በዓሉ መንፈሳዊ ስለሆን በመንፈሳዊነት ልናከብረው ይገባል እንደዚሁም በታዛዥነት እና በእምነት በበዓሉ ላይ ልንታደም ይገባል ብለዋል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC " ሀገራችን ሰላም ትሁን፤ የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው " - ብፁዕነታቸው ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ምን አሉ ? - የማይደፈር ሲደፈር አይተናል፤ ቤተክርስቲያን ስትደፈር ዝም አንልም። - " ፖለቲካው የፖለቲካው መስመር ሲደፈር ዝም እንደማይል ሁሉ እኔም ደግሞ የመጀመሪያዋም የመጨረሻዋም…
#ጥምቀት

" በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፈ ያለውን የበዓል አከባበር ክልከላን የሚገልጹ የሐሰት ዜናዎች ቤተክርስቲያንን አይወክሉም " - ብፁዕ አቡነ አብርሃም

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልእክቶች የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮሩ እንዲሆኑ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው በተለያዩ ቋንቋዎች ለተለያዩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ቃለ መጠይቅና ምላሽ እንዲሰጡ ለተመረጡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በሰጡት አባታዊ መመሪያ የቅድስት ቤተክርስቲያን መልእክት የሚተላለፈው በማእከል በመሆኑ የማእከሉን መልእክት ብቻ እንዲያስተላልፉ መመሪያ የሰጡ ሲሆን ከግል አስተያየት መቆጠብ እንደሚገባም አበክረው አሳስበዋል።

ቤተክርስቲያኗ የሰላም ሰባኪ እንደመሆኗ መጠን የቤተክርስቲያን መልእክት ሲተላለፍ ሰላም ላይ ማተኮርና በዓል ለማክበር የሚወጡ ምእመናን በዓሉ በሰላም አክብረው እንዲመለሱ መልእክት ማስተላለፍ እንደሚገባ ግልጽ መመሪያ ሰጥተዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያዊ ሁሉም ሃይማኖቶች ተከባብረው የሚኖሩባት ሀገር መሆኗ ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ ይህ በዓል የሚከበርባቸውን ቦታዎች ለማጽዳትና ሥርዓት ለማስከበር ጥረት እያደረጉ ያሉ የሌሎች ሃይማኖት አባላትን በአባትነት ያመሰገኑት ብፁዕነታቸው ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች የሚገኙ የሌሎች ቤተ እምነቶችን ማክበር እንደሚገባ ለሁሉም ካህናትና ምእመናን አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፈ ያለውን የበዓል አከባበር ክልከላን የሚገልጹ የሐሰት ዜናዎች ቤተክርስቲያንን የማይወክሉና ቤተክርስቲያናችን በዓሉን በሰላም ለማክበር ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር እያደረገች ያለውን ጥረት ከግንዛቤ ያላስገባ መሆኑን ብፁዕነታቸው አሳውቀዋል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC የግንቦት 2016 ዓ/ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ፦ በቤተ ክርስቲያኗ በሀገራዊ እንዲሁም በወቅታዊ ዐበይት ጉዳዮች ላይ ለተከታታይ ቀናት ተወያይቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የማጠቃለያ መግለጫ ነገ ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ከጧቱ 4፡00 ሰዓት እንደሚሰጥ ተነግሯል። #የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን #ኢትዮጵያ…
#ኢትዮጵያ

ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት 2016 ዓ/ም የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ እና የግብረ ሰዶማዊነትን #ኃጢአት በተመለከተ አጀንዳ አድርጎ መወያየቱ ተሰምቷል።

በዚህም፥ የቅድስት ቤተ ክርስቲያኗን አቋም በሚገልጽ መልኩ ራሱን ችሎ #ዓለም_አቀፋዊ ይዘቱን ባገናዘበ ሁኔታ ዝርዝር የሆነ መግለጫ እንዲሰጥ ወስኗል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia