TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Djibouti #DrAbdelaHamdok #IGAD

የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር እና የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር አብደላ ሀምዶክ በ38ኛው የኢጋድ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ዛሬ ጅቡቲ ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ጅቡቲ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ አቀባበል ተቀብለዋቸዋል።

የኢጋድ ስብሰባ ነገ ይጀምራል።

በኢጋድ ስብሰባ ላይ ዶ/ር አብይ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ለአባል ሀገራት መሪዎች ሪፖርት እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያን ውስጣዊ ጉዳይ ጨምሮ የኬንያ እና ሶማሊያ አለመግባባት ዋነኛ የውይይት አጀንዳዎች ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የደቡብ ሱዳን የሰላም ሂደት የደረሰበትን ሁኔታ እንደሚዳሰስ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል ኢጋድ እየሰጠ ያለውን የወረርሽኙ የሁለተኛ ዙር ምላሽ በማስመልከት ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ ፦ ኢጋድ፣ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ፣ አል ዓይን
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot