TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የተመድ የፀጥታው ም/ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ምን ተወያየ ?

በትግራዩ ጦርነት ለተጎዳዉ የክልሉ ሕዝብ ተጨማሪ ሰብአዊ ርዳታ እንዲደርስ የተባበሩት መንግስታት (UN) የፀጥታው ጥበቃ ም/ቤት አባል ሃገራት ጠይቀዋል።

አስራ-አምስቱ የምክር ቤቱ አባላት ትግራይ ዉስጥ ስላለዉ ስብአዊ ሁኔታ በዝግ ተነጋግረዋል።

የፈረንሳዩ ዜና አገልግሎት አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበዉ ምክር ቤቱ በይፋ ያወጣዉ መግለጫ የለም።

ይሁንና ዜና አገልግሎቱ የጠቀሳቸዉ ዲፕሎማት እንዳሉት የርዳታ ድርጅቶች ለትግራይ ሕዝብ ተጨማሪ ሰብአዊ ርዳታ ለማቅረብ ይበልጥ ይፈቀድላቸዉ ዘንድ ሁሉም ተሰብሳቢዎች ጠይቀዋል።

የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤትን ስብሰባ የጠሩት አየርላንድ ፤ ኢስቶንያ ፈረንሳይ፣ ኖርዌ፣ ብሪታንያ እና ዩናይትድ ስቴትስ ናቸዉ።

ከስብሰባው በኃላ ይፋዊ መግለጫ ባይወጣም ስብሰባውን አስመልክቶ ዲፕሎማቶች ባደረጉት ገለፀ ኬንያ ፣ ቱኒዝያ፣ ቻይናና ሩሲያ አሁን ባለው ደረጃ ኢትዮጵያ ላይ ጫና ማሳደር አይገባም ብለዋል/ፍቃደኛ አልሆኑም።

#DeutscheWelle #AFP #Bloomberg

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia