TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbabaUniversity

ዛሬ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀን እና በማታ ያሰለጠናቸውን 4,087 ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።

ከተመራቂዎቹ መሀከል ፦

• 48ቱ በ3ኛ ዲግሪ በቀን የሰለጠኑ
• 809 በመጀመሪያ ዲግሪ በማታ ፕሮግራም
• 3,039 በቀን
• 18 በርቀት የሰለጠኑ ናቸው።

ዛሬ ከሚመሩቁ መካከል በህክምና ስፔሻሊቲ 26 ተማሪዎች ይገኙበታል።

የዛሬዎቹ ተመራቂዎች 2,635 ወንዶች ሲሆኑ 1452 ሴቶች ናቸው፡፡ (ኤፍ ቢ ሲ)

@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት የተለያዩ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን አስመርቀዋል ፦

#DireDawaUniversity

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለ12ኛ ጊዜ በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸው 2 ሺህ 93 ተማሪዎችን አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ መካከል ከ700 በላይ ሴቶች መሆናቸ ተገልጿል።

#Yekatit12_Hospital_Medical_College

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ4ኛ እና በ5ኛ ዙር በተለያዩ የህክምና ዘርፍ ያስተማራቸውን 127 ዶክተሮች አስመርቋል።

#AddisAbabaUniversity

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር አንበሳ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ 484 የሕክምና ባለሙያዎችን አስመርቋል። ከምሩቃኑ 209 በስፔሻሊስት፣ ሁለት በዶክትሬት እና 273 በ2ተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ የሕክምና ባለሙያዎች ናቸው።

#MetuUniversity

የመቱ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ ትምህርት ዘርፎ ያሰለጠናቸው 252 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ አስመርቋል።

ከሰለጠኑባቸው የትምህርት መስኮች ውስጥ ነርሲንግ፣ ፋርማሲ፣ ህብረተሰብ ጤና እና አዋላጅ ነርሲንግ ይገኙበታል።

ከመካከላቸው 93 ሴቶች ናቸው።

#CateringandTourismTrainingCenter

የሆቴልና ቱሪዝም ስራ ማሰልጠኛ ማዕከል (CTTC) በተለያዩ የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 425 ተማሪዎችን አስመርቋል።

በዘንድሮ መርሀ ግብር በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ በድግሪ 16 ተመራቂዎች ፣ በደረጃ 3 በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ 202 ተመራቂዎች ፣ በደረጃ 4 በሆቴል እና ቱሪዝም 157 ተመራቂዎች እንዲሁም በደረጃ 5 በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ 53 ተማሪዎች ነው የተመረቁት።

@tikvahethiopia
#AddisAbabaUniversity

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ነፃ እና እራሱን የቻለ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ለማድረግ የተደራጀው ግብረ ሀይል ወደ ስራ መግባቱ ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሥራ አመራር ቦርድ ጋር የግብረ ሃይሉን የሥራ ማስጀመሪያና ትውውቅ መድረክ አካሂደዋል፡፡

መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነጻነት ተጎናፅፈው መስራት እንዲችሉ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቋማዊ ነፃነት ኖሮት መልሶ እንዲደራጅ በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ተቋማዊ ነጻነት መስጠት ከመንግስትም ከማህበረሰቡም ስምምነት የተደረሰበት መሆኑን ገልፀዋል።

ይህ የለዉጥ ስራ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቃማዊ ነጻነትን ማምጣት ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ተቋማዊ ነጻነት የሚሰጥ መሆኑንም አሳውቀዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነፃነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተጀምሮ ወደ ሌሎች ከፍተኛ ተቋማትም የሚስፋፋ መሆኑም ተገልጿል።

#MoE

@tikvahethiopia
#AddisAbabaUniversity

የፀጥታ ችግር ካለባቸው ምዕራብ እና ደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች የመጡ መደበኛ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎች የክረምት እረፍት ጊዚያቸውን በዩኒቨርሲቲው እንዲቆዩ ጥያቄ አቅርበው ምላሽ በመጠበቅ ላይ ናቸው።

ቲክቫህ በጉዳዩ ዙሪያ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና የተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑትን ማቲዎስ እንሰርሙ (ዶ/ር) ጠይቋል።

"የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች የመጡ ተማሪዎች ጥያቂያቸውን ለተማሪዎች አገልግሎት በማመልከቻ በማቅረብ ምላሽ እንደሚሰጣቸው" ምክትል ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

"ከተማሪዎች ዲን ጋር በመሆን እያንዳንዱን ጥያቄ ኬዝ በኬዝ በማየት እና አመልካቾቹን ቃለመጠይቅ በማድረግ ምላሽ ይሰጣል" ብለዋል።

በተጨማሪም አካል ጉዳተኛ የሆኑ እና የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸው ተማሪዎችንም በመለየት ምላሽ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች በግቢው ስለሚቆዩ እና የክረምት ተማሪዎች ወደ ተቋሙ ስለሚገቡ የዶርም እጥረት መኖሩን በመግለጽ የተማሪዎቹ ጥያቄ ኬዝ በኬዝ እንደሚታይ ተናግረዋል።

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia