TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Awi : አቶ እንግዳ ደኛው የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ በመሆን ተሾሙ።

ዛሬ እየተካሄደ በሚገኘው የአዊ ብሔረሰብ ምክር ቤት 5ኛ ዙር 22ኛ መደበኛ ጉባዔ አቶ እንግዳ ደኛው የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል።

አቶ በላይነህ የኔሰው ደግሞ ምክትል አስተዳዳሪ እና የገጠር መሬት አስተዳደር መምሪያ ኃለፊ ሆነው ተሹመዋል።

መረጃው የአዊ ኮሚኒኬሽን ነው።

@tikvahethiopia
#AWI

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ጫት ቤቶች እንዲዘጉ ተወሰነ።

ብሔረሰብ አስተዳደሩ ወቅታዊ አገራዊ ጉዳይን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

ከውሳኔዎቹ መካከል የመጀመሪያው ጫት ቤቶች እንዲዘጉ የሚል ነው።

በተጨማሪም ከየትኛውም ከተማ ከምሽቱ 2:00 በኋላ መንቀሳቀስ እንደማፈቀድ (በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሠረት) ተገልጿል።

የመንግሥት እና የግል መሳሪያ የያዙ ግለሰቦች ወደ ግንባር እንዲዘምቱ ተወስኗል።

መኝታ ቤት የሚያከራዩ ሰዎች ማንነትን እንዲያረጋግጡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ በተከራይ ችግር ቢፈጠር ተጠያቂ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

ማንም ሰው ተኩስ ከተኮሰ መሳሪያውን እንደሚቀማ ውሳኔ ተላልፏል።

ማንኛውም ግለሰብ በየአካባቢው ተደራጅቶ በሮንድ አካባቢውን የመጠበቅ ግዴታ እንዳለበት የማይተባበር ከሆነ በህግ እንደሚጠየቅ ተወስኗል።

ከመንግስት በተቀመጠ አቅጣጫ መሰረት ድጋፍ ያላደረጉ አካላት እንዲደግፍ ፣ እንዲከፍሉ ካልከፈሉ ድርጅታቸው ታሽጎ አገልግሎት እንዳያገኙ እንዲደረግ ተወስኗል።

(አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ከላይ በዝርዝር ተቀምጧል)

#StateofEmergencyEthiopia

@tikvahethiopia