TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን ፦ - ከኦነግ ሸኔ፣ - ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣ - ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣ - ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣ - ወደ አዲስ…
#ፓርላማ

" እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ?

#አቶ_ክርስቲያን_ታደለ (የህ/ተ/ም/ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?

" የጥያቄዬ መንደርደሪያ የሚሆን ማስታወሻ ብዬ ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለ እርሶ እና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብቦት ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ አለፍ ሲል ተጠየቅ የቀረበቦት የወጡበትን ብሄር በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ ሲሰጡ የቅርብ ትዝታችን ነው።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ጥያቄ የማቀርብልዎ እኔ በብሄሬ አይደለም፤ ይህን ጥያቄ ሳቀርብልዎ እርሶ የሚወክሉትን ብሄር በመጥላት አይደለም ምላሽ እና ማብራሪያ ሲሰጡም ለጥያቄዬ ብሄርዎን እና ምናልባት የመንግስት ግልበጣ ሴራ ነው ከሚል ምላሽ እና ማብራሪያ እንዳይሰጡ ከወዲሁ አደራ ማለት እፈልጋለሁ።

ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ ...

የዜጎችን ደህንነት እና የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛው የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፣ ቤታቸው ይፈርሳል፣ ንብረታቸው ይወድማል የሀገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት ሀገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ፣ እና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርከታ ኪሎ ሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈፅመዋል።

... የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ ደጋግሞ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚገደሉ ዜጎች፣ ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ወንጀሎች ፣ መፈናቀሎች፣ ግድያዎች ፣ ቤት መፍረሶች በሪፖርቱ ያቀረበው ነው።

አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደህንነት እና የሀገር ልዑላዊነት ዋና ስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው እርሶ የሚመሩት መንግስትን ነው።

እርሶ በአፍዎ ኢትዮጵያ አትፈርስም ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው።

የበርካታ ሀገራት መሪዎች መሰል ኃላፊነትን በወጉ አለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ህዝብን ይቅርታ ጠይቀው ስልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል፤ በሀገራችንም የቀድሞ ጠ/ሚ ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ህዝባዊ ተጠየቅነት ሲቀርብባቸው ስልጣን መልቀቃቸውን እናስታውሳለን እርስዎም ወደ ስልጣን የመጡት በዚሁ ተጠየቅ ምክንያት ነው፤ እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? አመሰግናለሁ !! "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን ፦ - ከኦነግ ሸኔ፣ - ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣ - ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣ - ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣ - ወደ አዲስ…
#ፓርላማ

" እነኚህ ሰዎች ሰላም ቢኖር ምን ያጣሉ ? #ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? #ከኦነግ_ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? "

ዶክተር ከፈና ኢፋ (የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?

" .... በኦሮሚያ ክልል ጦርነት በኢኮኖሚ ላይ በፖለቲካ ላይ ፣ በማህበራዊ ህይወት ላይ ያስከተለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት እና ጉዳት ዘርዝሬ መጨረስ አልችልም፤ ህዝብ ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።

ህዝባችም በጣም እየተንገላታ ነው፤ በቅርቡ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በኦሮሚያ ክልል ታጥቆ ለሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪ አቅርቦላቸዋል፤ ይሄ የሰላም ጥሪ ምን ላይ ደርሷል ? ጅምሩ ምን ይመስላል ? ህዝባችን በአሁን ጊዜ በጉጉት አይደለም እየጠበቀ ያለው ይሄን የሰላም ድርድር በፀሎት ጭምር ነው በፆም በፀሎት ጭምር የዚህን ድርድር መጀመር እየጠበቅን ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው።

ስለዚህ #ሰላም ለተጠማው ህዝባችን ሰላም ለማውረድ በዚህ ረገድ መሬት ላይ ምን እየተሰራ ነው ?

ከኦነግ ሸኔም ጋር ይሁን ከህወሓት ጋር ለተደረገው የተሳካ ስምምነት ኢትዮጵያውያን ሆነው የሚቃወሙ ሰዎች አሉ፤ ይሄን የሚያደርጉት ከውሥጥም ከውጭም ነው።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ ሰላም ከምንም በላይ ብሄራዊ ጥቅማችን ነው ፤ ኢትዮጵያውያን ሆነው ከራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም በተፃራሪነት መቆም ትርጉሙ ምንድነው ? ምን ለማግኘት ነው ? ምን ለማጣት ነው ?

እነኚህ ሰዎች ምን ያጣሉ ሰላም ቢኖር ? ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? ከኦነግ ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? መፈናቀል ነው የሚቀረው ፣ ተጨማሪ የሰው ስቃይ ነው የሚቀረው ፣ የንብረት መውደም ነው የሚቀረው፣ የመሰረተ ልማት መውደም ነው የሚቀረው ይሄን የሚቃወም ኢትዮጵያዊ ምን አይነት ኢትዮጵያዊ ነው ? ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ አመሰግናለሁ !! "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓርላማ " እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? #አቶ_ክርስቲያን_ታደለ (የህ/ተ/ም/ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ? " የጥያቄዬ መንደርደሪያ የሚሆን ማስታወሻ ብዬ ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ። ክቡር…
#ፓርላማ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ስልጣን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል አይሆኑም ወይ ?  ለሚለው ጥያቄ ምን መለሱ ?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦

" ስልጣን ብትለቅ የተባለው በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው ፤ ግን ጥሩ የሚሆነው ስልጣን ብንለቅ ነበረ ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ ማለት አይደለም።

ህግ አውጪ መንግስት ነው፣ ህግ ተርጓሚ መንግስት ነው ፣ አስፈፃሚ መንግስት ነው እኛ እዚህ ያለን ሰዎች የመንግስት ባለስልጣኖች ነን።

ይልቁኑንም የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ደግሞ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው የአንድ ሚኒስትር አለቃ ናቸው እና በጋራ ብንለቅ ቢሆን ምክንያቱም እርሶም እንደሚገነዘቡት የሁሉ ችግር ምንጭ እና ባለቤት እኔ ብቻ ልሆን አልችልም።

ኃላፊነት ከወሰድንም በጋራ ቢሆን ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።

ነገር ግን ይሄን ጥያቄ እሳቸው ቢያነሱትም እሳቸው ላይም ይነሳ ነበር በውጭ ያሉ እንደሳቸው ፓርላማ አሸንፈው መግባት ያልቻሉ ሰዎች ለምንድነው እኚህ ሰውዬ የቋሚ ኮሚቴ ኃላፊነት ላይ የተቀመጡት አይለቁም እንዴ ? እያሉ ከዚህ ቀደም በሚዲያ እንደምትሰሙት ብዙ ይተቻሉ፤ እርሶ ምርጫ አሸንፈው ነው የገቡት እዚህ ተቀምጠው የህዝቡን ጥያቄ ማንሳትዎ ተገቢ ነው ብዬ ማስበው መቆጣጠሩም የሚያደርጉት ጥረትም።

ግን ከስልጣን ጋር ተያይዞ ያለውን ጉዳይ በአንድ ቀላል ምላሴ ለማስረዳት በደቡብ ህንድ ጦጣን የማጥመድ ቴክኒክ አለ ጦጣን እንደምታውቁት ቁንጥንጥ ናት፣ ቅብዝብዝ ናት  ለአደን አትመችም እና በደቡብ ህንድ ያሉ አዳኞች ጦጣን ለማጥመድ የኮኮናት ፍሬ በጦጣ እጅ ልክ በቀጭኑ ይቀዱና ከውሥጥ ሩዝ ያስቀምጣሉ ሲቀዱት የጦጣ እጅ ቀጭን ስለሆነ በዚያ ልክ ይቀዱትና ውስጥ ግን ሰፋ አድርገው ሩዝ ያስቀምጣሉ፤ሊይዟት ስለማይችሉ ጦጣ ሩዝ አየሁ ብላ እጇን ሰዳ ካፈሰች በኃላ ልውጣ ስትል የተሰራው ለቀጭኑ ስለሆነ ከጨበጠች በኃላ አይለቃትም።

ይቺ ጦጣ የሰው ሩዝ ነው የያዝኩት የማይገባኝን ሩዝ ነው የያዝኩት ይዤው ከቆየሁ ልያዝ እችላለሁ በትኜው ልሂድ አትልም እንደጨበጠች ትታገላለች በዚህ ጊዜ ያን የኮከናት ፍሬ መውሰድ ስለማትችል አዳኙ መጥቶ ይይዛታል። ጦጣዋን ያደናት የያዛት ምንድነው ያላችሁ እንደሆነ ሃሳቧ ነው እንጂ ወጥመዱ አይደለም፤ እዛው በትና በትለቅ ትወጣለች በሀሳብ ግን ሩዝ አፍሼ ካልወጣሁ ስላለች ሀሳቧ አጥምዶ ያስቀራታል እዛው።

ዶሮ ብታልም ጥሬዋን እንደሚባለው ቁጭ ብለው የሚያልሙ ሰዎች አሉ ሁል ጊዜ በዚያ መንገድ ጥሩ አይሆንም።

ሁለተኛ ቢጨበጥ ጥሩ የሚሆነው ስልጣንን በሚመለከት በእኔ እና በተከበሩ አቶ ብናልፍ መካከል የሚደረግ ድርድር የለም።

የስልጣን ባለቤት ህዝብ ነው፤ስልጣን ሰጪም ነፋጊም ህዝብ ነው፤እኔ ና አቶ ብናልፍ ማድረግ ያለብን የተሻለ ሃሳብ ይዘን ህዝባችን ጋር መቅረብ እና የኔን ሃሳብ ምረጥልኝ ብለን በሰጪው ነው የምንመረጠው እንጂ በምክር ቤት ውስጥ ስጠኝ ልቀቅልኝ በሚል አይሆንም።

ሰጪው ጋር ሃሳብ የተሻለ ይዞ መቅረብ ታስፈልጋል፤ ስለዚህ ስልጣን በኮሮጆ እንጂ በመናጀ አይያዝም እና ሶስት ዓመት ይቅራል ለምርጫ በውጭም አሉ ይሄ የኦሮሞ መንግሥት ይሄ የኦሮሞ መንግስት እያሉ የሚዘፍኑ ዘፋኞች አሉ እነሱን ጨምሮ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ አጠናክሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማቅረብ ነው እኛ ለኢትዮጵያ ህዝብ እንደተባለድ የተገባውን ቃል ካልመለስን የኢትዮጵያ ህዝብ በእኛ አስተዳደር ካልረካ በምርጫ ከጣለን በተደጋጋሚ እንዳልነው በደስታ እናስረክባለን።

ፓርቲዎች መዘጋጀት ያለባቸው ሃሳብ ይዘው መምጣት ነው፤ አሁን ሃሳብ የለም፤ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ ይዞ ያን ወደ ህዝብ አቅርቦ ለመመረጥ እና ለማሸነፍ የሚደረግ ጥረት ለሁላችን የሚጠቅመን ይሆናል "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓርላማ " እነኚህ ሰዎች ሰላም ቢኖር ምን ያጣሉ ? #ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? #ከኦነግ_ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? " ዶክተር ከፈና ኢፋ (የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ? " .... በኦሮሚያ ክልል ጦርነት በኢኮኖሚ ላይ በፖለቲካ ላይ ፣ በማህበራዊ ህይወት ላይ ያስከተለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት እና ጉዳት ዘርዝሬ መጨረስ አልችልም፤…
#ፓርላማ

መንግሥት ከ " ኦነግ ሸኔ " ጋር የሚደረግን የሰላም ድርድር የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ ዛሬ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለፓርላማ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ "  ኦነግ ሸኔ " ምን አሉ ?

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦

" ሸኔን በሚመለከት ለተነሳው ጥያቄ ... ላለፉት አራት ፣ አምስት ዓመታት ወለጋ አካባቢ ልማት እንዳይሰራ ሰዎች እንዲፈናቀሉ እንዲገደሉ ብዙ መጎሳቀል ግጭት ነው።

ይሄ ግጭት በሰላም እንዲፈታ መንግሥት ከፍተኛ ፍላጎት አለው። ከፍተኛ ፍላጎት አለው ብቻ ሳይሆን በባለፈው በማዕከላዊ ኮሚቴ ተወያይቶ በፓርቲያችን ምክትል ፕሬዜዳንት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሟል። የሰላም ድርድሩን የሚመራ።

ከቤኒሻንጉል ጋር የተሻለ ውጤት ተገኝቷል፣ ከጋምቤላ ጋር የተሻለ ውጤት ተገኝቷል፣ ከቅማንት ጋርም እንዲሁ የተሻለ ውጤት ተገኝቷል የሚቀሩ ጉዳዮች ቢኖሩም ሸኔን በሚመለከት ባለፉት አንድ / ሁለት ወር ገደማ ከ10 በላይ ሙከራዎች ተደርገዋል ያስቸገረው ነገር አንድ የተሰባሰበ ኃይል ባለመሆኑ ምንነጋገርባቸው ኃይሎች የተለያየ ሃሳብ እና አቋም ይዘው ስለሚመጡ ነው።

የሆነው ሆኖ በእኛ በኩል የኦሮሚያ መንግስት ያቀረበው የሰላም ጥሪ የሚባለው የኦሮሚያ መንግስት ያቀረበው ሳይሆን እንደ ፓርቲ ተወያይተን ወስነን በምክትል ፕሬዜዳንት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁመን የዛን ተቀጥያ ነው የኦሮሚያ መንግሥት የገለፀው/ ያብራራው።

ሰላሙን የሚጠላው ሰው ይኖራል ብዬ አላስብም ኢትዮጵያዊና ጤነኛ ሰው ከሆነ ምክንያቱም ብዙ ሰው እየተጎዳ እየተፈናቀለ ስለሆነ ሰላሙን ሁሉም ይፈልገዋል የሚል ተስፋ አድርጋለሁ በእኛ በኩል ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ አበክረን እንሰራለን። ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ አበክረን እየሰራን ተጨማሪ ደግሞ ማፈናቀል እና መግደል እንዳይፈጠር / እንዳይቻልም ኃይሎቻችን በስፋት እዛ አካባቢ ጠንከር ያለ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።

ለሰላሙ ግን ጥርጣሬ መኖር የሌለበት ለአገው ሸንጎም፣ ለቅማንትም፣ ለTPLFም ፣ ለኦነግም ለሁሉም የታጠቁ ኃይሎች የኢትዮጵያ መንግስት የሚፈልገው ጉዳዩን በንግግር ፣ በምክክር ፣ በውይይት መፍታ ነው። መገዳደል አይጠቅምም የሚል የፀና አቋም አለን የሚያዋጣንም መንገድ እሱ ይመስለኛል።

በዚህ አግባብ ቢታይ የሸኔ ጉዳይ እየተመራ እንደሆነ ኮሚቴዎች ተቋቁመው እየተነጋገሩ እንደሆነ ውጤቱን ደግሞ በጋራ የምናይ ይሆናል ። "

@tikvahethiopia
#ፓርላማ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛውን፣ 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 28ኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡

ምክር ቤቱ በስብሰባው የ27ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔን መርምሮ አጽድቋል፡፡

የምክር ቤት አባላትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌደራል መንግስት የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Via HoPR

@tikvahethiopia