TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል #ብርሃኑ_ጁላ

‹‹በውትድርና ዘመኔ በራስ ሕዝብ ላይ ጭካኔ የተሞላበት ዘግናኝ #ጥቃት ተፈጽሞ #ያየሁት በምዕራብ ወለጋ ነው››

‹‹ለረጅም ዓመታት በውትድርና አገልግያለሁ፣ እንዲህ ዓይነት #ጭካኔ በወለጋ ከተፈጸመው በስተቀር አይቼ #አላውቅም፤››

‹‹በምዕራብ ወለጋ የተፈጸመውን ጭካኔ በቅርቡ #በቪዲዮ ምሥል ጭምር #ታዩታላችሁ፤››

‹‹የመከላከያ ሠራዊቱ ወደ #ወለጋ ሲገባ ያገኘነው #ጉድ ዘግናኝ ነው፤››

https://telegra.ph/በውትድርና-ዘመኔ-በራስ-ሕዝብ-ላይ-ጭካኔ-የተሞላበት-ዘግናኝ-ጥቃት-ተፈጽሞ-ያየሁት-በምዕራብ-ወለጋ-ነው-01-09-2
እፀገነት አንተነህ⬆️

"የ27 አመቷ የአየር መንገድ ሒሳብ ሰራተኛ እፀገነት አንተነህ ትናንት ማክሰኞ ጠዋት ወደ ሰራ በምታመራበት ወቅት #ጭካኔ በተሞላበት ወንጀል አቃቂ መንገድ ላይ ተገድላ ተጥላ ተገኘች። ፓሊስ ምርመራ ላይ ነው። ቀብሯ ዛሬ ተፈፅሟል። ቀለበት አድርጋ ሰርግ ለመደገስ ዝግጅት ላይ ነበረች።" ጋዜጠኛ ተስፋዬ ጌትነት/#CAPITAL/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አምነስቲ ኢንተርናሽናል በሳዑዲ አረቢያ ስላሉት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ምን አለ ?

አምነስቲ ኢንትርናሽናል ከሰሞኑን በሳዑዲ አረቢያ ፤ ኢትዮጵያውያን ስላሉበት ሁኔታ አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

በዚህ ሪፖርቱ የገለፃቸው ፦

- " ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ናቸው " የተባሉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ (ከ30 ሺህ ይበልጣሉ) ኢትዮጵያውን ስደተኞች በተጨናነቁ እስር ቤቶች #በሰቆቃ ውስጥ ይገኛሉ።

- ወንዶች፣ ሴቶች እና ልጆች የሚገኙባቸው ስደተኞች በዘፈቀደ ተይዘው በእጅጉ በተጨናነቁት አል-ኻራጅ እና አል-ሹማይሲ በተባሉ እስር ቤቶች ይገኛሉ።

- የሳዑዲ ባለሥልጣናት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን #ኢሰብአዊ እና #ጭካኔ በተሞላበት አያያዝ ላልተገደበ ጊዜ በእስር ካቆዩ በኋላ በግድ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ይደርጋሉ።

- ኢትዮጵያውያን ሳዑዲ ውስጥ ለስቃይ የሚዳረጉት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የላቸውም በሚል ሲሆን ይህም ሁኔታ በ"ካፋላ" የሠራተኞች ቅጥር ሥርዓት ምክንያት የተባባሰ ነው።

- ባለፉት 5 ዓመታት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሳዑዲ አረቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ በማለፋቸው በርካቶች ለከባድ እና ለዘላቂ አካላዊ እና አእምሯዊ ችግሮች ተዳርገዋል። በአሁኑ ወቅት ከ30,000 በላይ ኢትዮጵያውያን በተመሳሳይ ሁኔታ ተይዘው ተመሳሳይ ዕጣ እየተጋፈጡ ነው።

- የሳዑዲ ባለሥልጣናት ባለፉት 2 ዓመታት በእስር ቤቶች በስደተኞች ላይ የተፈጸሙ ማሰቃየቶችን እንዲሁም ቢያንስ 10 ሞቶች ላይ ምርመራ ሊያካሂዱ ይገባል።

https://www.amnesty.org/en/latest/news/2022/12/saudi-arabia-ethiopian-migrants-forcibly-returned-after-detention-in-abhorrent-conditions/

#BBC

@tikvahethiopia