TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጊፋታ⬆️

የወላይታ ዘመን መለወጫ በዓል ጊፋታ!

የወላይታን ብሔር ከሀገራችንና ከደቡብ ክልል ብሔሮችና ብሔረሰቦች በተለየ መልኩ የሚገለጽባቸው በርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች ያሉት ሲሆን ከብሔሩ የማይዳስሱ #ሀብቶች መካከል የወላይታ ዘመን መለወጫ በዓል #ጊፋታ አንዱ ነው፡፡

ጊፋታ በብሄሩ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ታላቅ የዘመን መለወጫ በዓል ሲሆን ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የብሔሩ ማንነት መገለጫ የሆነ #የአሮጌው ዓመት ማብቅያና የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ የመሸጋገሪያ በዓል ነው፡፡

ጊፋታ ማለት ባይራ(ታላቅ)፣ መጀመሪያ እንደ ማለት ሲሆን በሌላ በኩል ጊፋታ ማለት መሻገር ማለት ነው፡፡ ይህም ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከጨለማ ወደ #ብርሃን መሻገር የሚለውን ይገልጻል፡፡ የወላይታ ብሔር የራሱ የሆነ የዘመን መቁጠሪያ(ካሌንደር) ያለው ሲሆን በወላይታ የዘመን አቆጣጠር ጊፋታ የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ስያሜ ነው፡፡

ወላይታዎች አስራ አንድ ወራት በስራ ካሳለፉ በኋላ የመጨረሻውን አንድ ወር ለበዓሉ ያውሉታል፡፡ 15 ቀን በበዓሉ ዝግጅት፣ አስራ አምስቱን ቀን ደግሞ በመዝናናትና በመጫወት ያሳልፋሉ፡፡

መስከረም ወር በገባ ከ14-20 መካከል በሚውለው እሁድ ዕለት አዲሱን ዓመት
ይቀበሉታል፡፡ በየዓመቱ ከመስከረም 14-20 ባሉት ቀናት መካከል የሚውለው እሁድ እለት የአዲስ ዓመት ቀን ይሆናል፡፡ ስሙም ሹሃ ወጋ /የእርድ እሁድ/ ይባላል፡፡
.
.
.
ጊፋታ የይቅርታ፤ የፍቅር እና የሰላም በዓል ነው!

ምንጭ፦ የወላይታ ዞን ባህል፣ ቱሪዝም እና መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጊፋታ_አዋርድ

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ “ጊፋታ አዋርድ” የተሰኘ የምስጋናና የዕዉቅና ሽልማት ተበረከተላቸዉ፡፡ በወላይታ ሶዶ “አርአያዎቻችን በረከቶቻችን ናቸው” በሚል መርህ ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ የምስጋናና ዕውቅና ስነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡ በስነ-ስርዓቱ ወቅት አቶ ኃይለማርያምን ጨምሮ በተለዩ አምስት ዘርፎች በሃገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጎ ተጽዕኖ የፈጠሩ 45 ግለሰቦች የምስጋናና የዕውቅና ሽልማትም ተበርክቶላቸዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-16-3

@tsegabwolde @tikvagethiopia
#ጊፋታ

የወላይታን የዘመን መለዋጫ የጊፋታ በዓል #በዩኔስኮ የማስመዝገብ ጥረት መጀመሩ ተገልጿል፡፡ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ እንደገለጹት፤ የጊፋታን በዓል በዩኔስኮ የማስመዝገብ እንቅስቃሴ በመካሄድ ላይ ነው ብለዋል፡፡ ከመስከረም 14 እስከ መስከረም 20 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበረው የወላይታ ዘመን መለዋጫ ትርጓሜ ታላቅና የመጀመሪያ ማለት እንደመሆኑ በበዓሉ ያለውን እውነታ በዩኔስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚደረውን ጥረት ከፍ እንደሚያደርገው አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

@tsegabwolde @tikvahethioia
#ጊፋታ

የወላይታ ዘመን መለወጫ በዓል ጊፋታ!

የወላይታን ብሔር ከሀገራችንና ከደቡብ ክልል ብሔሮችና ብሔረሰቦች በተለየ መልኩ የሚገለጽባቸው በርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች ያሉት ሲሆን ከብሔሩ የማይዳስሱ ሀብቶች መካከል የወላይታ ዘመን መለወጫ በዓል #ጊፋታ አንዱ ነው፡፡

ጊፋታ በብሄሩ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ታላቅ የዘመን መለወጫ በዓል ሲሆን ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የብሔሩ ማንነት መገለጫ የሆነ የአሮጌው ዓመት ማብቅያና የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ የመሸጋገሪያ በዓል ነው፡፡

ጊፋታ ማለት ባይራ(ታላቅ)፣ መጀመሪያ እንደ ማለት ሲሆን በሌላ በኩል ጊፋታ ማለት መሻገር ማለት ነው፡፡ ይህም ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሻገር የሚለውን ይገልጻል፡፡ የወላይታ ብሔር የራሱ የሆነ የዘመን መቁጠሪያ(ካሌንደር) ያለው ሲሆን በወላይታ የዘመን አቆጣጠር ጊፋታ የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ስያሜ ነው፡፡

ወላይታዎች አስራ አንድ ወራት በስራ ካሳለፉ በኋላ የመጨረሻውን አንድ ወር ለበዓሉ ያውሉታል፡፡ 15 ቀን በበዓሉ ዝግጅት፣ አስራ አምስቱን ቀን ደግሞ በመዝናናትና በመጫወት ያሳልፋሉ፡፡

መስከረም ወር በገባ ከ14-20 መካከል በሚውለው እሁድ ዕለት አዲሱን ዓመት ይቀበሉታል፡፡ በየዓመቱ ከመስከረም 14-20 ባሉት ቀናት መካከል የሚውለው እሁድ እለት የአዲስ ዓመት ቀን ይሆናል፡፡ ስሙም ሹሃ ወጋ /የእርድ እሁድ/ ይባላል፡፡

ጊፋታ የይቅርታ፤ የፍቅር እና የሰላም በዓል ነው!

ምንጭ፦ የወላይታ ዞን ባህል፣ ቱሪዝም እና መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ

@tsegabwolde @tikvahethiopia