TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የጥለቻ ንግግር ወጊውን መልሶ #ይጎዳል!
(በሚራክል እውነቱ)

የጥላቻ ንግግር የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በፖለቲካዊ አመለካከት፣ በሚከተሉት እምነት፣ በዘር፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሃብት ደረጃ በቀለማቸው በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ከእኛ ሃሳብ ተቃራኒ ናቸው ብለን የምንፈርጃቸውን ሰዎች ስብእናቸውን በመጋፋት፣ ማንነታቸውን ጭምር በሚያሳንስና በሚያዋርድ መልኩ የሚሰነዝር ቃል ነው፡፡ አለፍ ሲልም ሰዎችን በማይሆን ፍረጃ ይገደል ይታሰር ይሰደድ የሚል ፍርድ በማሳለፍ ጭምር ሚዛናዊነትን የሚያስት ነው የጥላቻ ንግግር፡፡ እከሌ እንዲህ ካልሆነ፤ እክሌ ይሄ ፍርድ ይገባዋል፣ እክሌ ንፁህ ነው፤ ይሄኛው ደግሞ በደሉ ክልክ በላይ ሆኗል፤ ይሄ ወገን ይሄ ፍርድ ይገባዋልና መሰል የጥላቻ መርዞችን በመርጨት የሰዎችን አብሮ የመኖር እሴት እንዲሸረሸር የማድረግ አባዜ ነው፡፡

በግለሰቦች ላይ የሚሰነዘር የጥላቻ ንግግር የሰዎችን ስብዕና በመጋፋት ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ጠንካራ ስነልቦና ያለው ሰው እንኳን በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ ክብረ ነክ በሆኑ የጥላቻ ንግግሮች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል፡፡ የዚህን ትርፍና ኪሳራ መመዘን እንግዲህ የባለቤቱ ነው፡፡

ማንም ሰው ወደዚህ ምድር የመጣው በምክነያት ነው፡፡ እኔ የተፈጠርኩት በምክንያት ነው ብሎ ማመን ግድ ይላል፡፡ ያኔ እያንዳንዳችን በምንዘራው ልክ የምናጭድ መሆናችን ይገባናል፡፡ በጎ በጎውን ተናግሮ ተፅእኖ መፍጠርና የተሳሳተ አስተሳሰብ ማራመድና የጥላቻ ንግግር የሚያመጣውን መመዘን ይገባል፡፡

በመሆኑም በግለሰቦች ወይም በህዝቦች መካከል አለመግባባት፣ ብሎም #ግጭትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ የጥላቻና #አደገኛ ንግግሮች መባባስ የማህበራዊ ሚዲያዎች አሉታዊ አስተዋጽኦ በእጅጉ የጎላ መሆኑ እርግጥ ነው በመሆኑም የሚጠቅመውን መምረጥ ግድ ይላል ማለት ነው፡፡

ማህበራዊ ሚዲያዎች ማህበረሰቡን ለሚጎዱ መጥፎ ተግባራት ማራመጃነት እንዳይውሉ ይልቁንም ለአገር #ሰላምና የጋራ #መግባባት በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሁሉም ከራሱ ጀምሮ ከጥላቻ ንግግር ራሱን መቆጠብ ይገባዋል፡፡ መጨረሻው ለራስ የሚኖር ግምት ያነሰ እንዲሆን በማድረግ ራስን ጭምር ለማህበራዊ ቀውስ የሚከት ነውና፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጥለቻ ንግግር ወጊውን መልሶ #ይጎዳል!
(በሚራክል እውነቱ)

የጥላቻ ንግግር የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በፖለቲካዊ አመለካከት፣ በሚከተሉት እምነት፣ በዘር፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሃብት ደረጃ በቀለማቸው በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ከእኛ ሃሳብ ተቃራኒ ናቸው ብለን የምንፈርጃቸውን ሰዎች ስብእናቸውን በመጋፋት፣ ማንነታቸውን ጭምር በሚያሳንስና በሚያዋርድ መልኩ የሚሰነዝር ቃል ነው፡፡ አለፍ ሲልም ሰዎችን በማይሆን ፍረጃ ይገደል ይታሰር ይሰደድ የሚል ፍርድ በማሳለፍ ጭምር ሚዛናዊነትን የሚያስት ነው የጥላቻ ንግግር፡፡ እከሌ እንዲህ ካልሆነ፤ እክሌ ይሄ ፍርድ ይገባዋል፣ እክሌ ንፁህ ነው፤ ይሄኛው ደግሞ በደሉ ክልክ በላይ ሆኗል፤ ይሄ ወገን ይሄ ፍርድ ይገባዋልና መሰል የጥላቻ መርዞችን በመርጨት የሰዎችን አብሮ የመኖር እሴት እንዲሸረሸር የማድረግ አባዜ ነው፡፡

በግለሰቦች ላይ የሚሰነዘር የጥላቻ ንግግር የሰዎችን ስብዕና በመጋፋት ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ጠንካራ ስነልቦና ያለው ሰው እንኳን በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ ክብረ ነክ በሆኑ የጥላቻ ንግግሮች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል፡፡ የዚህን ትርፍና ኪሳራ መመዘን እንግዲህ የባለቤቱ ነው፡፡

ማንም ሰው ወደዚህ ምድር የመጣው በምክነያት ነው፡፡ እኔ የተፈጠርኩት በምክንያት ነው ብሎ ማመን ግድ ይላል፡፡ ያኔ እያንዳንዳችን በምንዘራው ልክ የምናጭድ መሆናችን ይገባናል፡፡ በጎ በጎውን ተናግሮ ተፅእኖ መፍጠርና የተሳሳተ አስተሳሰብ ማራመድና የጥላቻ ንግግር የሚያመጣውን መመዘን ይገባል፡፡

በመሆኑም በግለሰቦች ወይም በህዝቦች መካከል አለመግባባት፣ ብሎም #ግጭትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ የጥላቻና #አደገኛ ንግግሮች መባባስ የማህበራዊ ሚዲያዎች አሉታዊ አስተዋጽኦ በእጅጉ የጎላ መሆኑ እርግጥ ነው በመሆኑም የሚጠቅመውን መምረጥ ግድ ይላል ማለት ነው፡፡

ማህበራዊ ሚዲያዎች ማህበረሰቡን ለሚጎዱ መጥፎ ተግባራት ማራመጃነት እንዳይውሉ ይልቁንም ለአገር #ሰላምና የጋራ #መግባባት በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሁሉም ከራሱ ጀምሮ ከጥላቻ ንግግር ራሱን መቆጠብ ይገባዋል፡፡ መጨረሻው ለራስ የሚኖር ግምት ያነሰ እንዲሆን በማድረግ ራስን ጭምር ለማህበራዊ ቀውስ የሚከት ነውና፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia