TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የጀማል አስክሬን እንዲሟሟ ተደርጓል‼️

ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ከተገደለ በኋላ አስከሬኑ ተቆራርጦ #እንዲሟሟ ተደርጓል አሉ የፕሬዚዳንት #ኤርዶሃን ኣማካሪ።

የአሁኑ የአማካሪው መግለጫ “የጋዜጠኛው አስከሬን በአሲድ እንዲጠፋ ተደርጓል መባሉን ለማጣራት ምርመራ እየተካሄደ ነው” በማለት
አንድ ከፍተኛ የቱርክ ባለስልጣን ለዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ የሰጡትን መረጃ እውነትነት #ያረጋግጣል ተብሏል።

አማካሪው ያሲን አክታይ ቱርክ ውስጥ ለሚታተመው ሁርየት የተባለ ጋዜጣ እንደተናገሩት የካሾጊ አስከሬን ተቆራርጦ ብቻ ሳይሆን ሟሙቶ እንዲወገድ መደረጉን ነው ማወቅ የቻልነው ብለዋል።

እጃችን ላይ እንደደረሰው መረጃ ከሆነ ገዳዮቹ አስከሬኑን የቆራረጡት በቀላሉ ለማሟሟት እንዲመቻቸው ነው ብለዋል አማካሪው።

የቱርክ ዋና ዐቃቢ ህግ ባለፈው ረቡዕ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰጡት መግለጫ ካሾጊ ኢስታንቡል ወደሚገኘው የሳዑዲ ቆንስላ እንደገባ በተደራጀ ሁኔታ #ግድያ ተፈጽሞበት አስከሬኑም ተቆራርጦ እንዲወገድ መደረጉን አረጋግጠዋል።

“አንድም የሰውነቱ አካል እንዳይገኝ አልመው ያደረጉት ነገር ነው። ንጹህ ሰው መግደል አንድ ወንጀል ሆኖ ሳለ አስከሬኑ እንዲጠፋ የተደረገበት መንገድ ደግሞ ሌላ አስከፊ ወንጀል ነው ብለዋል ያሲን አክታይ።

ምንጭ፦ ARTS TV WORLD
@tsegabwolde @tikvahethiopia