TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የዩኒቨርሲቲዎች ዳሰሳ 2‼️

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በሃገሪቱ እየታየ ያለውን ሰላም ለማስቀጠል እና #ሁከትን ለመቀነስ ውይይት እያካሄዱ ነው፡፡

🔹ደብረ ማርቆስ ዩኒቭርስቲ

የመከላካያ ሚንሰትር ዴኤታ አምባሰደር ዘላለም ገብረ ዮሃንሰን ጨምሮ ከፌዴረል እና ከክልል የተወከሉ የመንግስት አካላት የምስራቅ ጎጃም ዞን እና የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር፣ የሃገረ ሽማግሌዎች ፣የሃማኖት አባቶች እና የጸጥታ አካላት በተገኙበት ምክክር አካሂዷል፡፡

🔹ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ

የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ #ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር ከተማሪዎች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው፡፡የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው የሚነሱ የግጭት መንስኤዎችን ለይቶ ቅድመ መከላከል ለመስራት እና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር ከተማሪዎች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው፡፡

🔹ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ

ከሕዳር 19 ጀምሮ የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ እና ተማሪዎች #በሰላማዊ የመማር ማስተማር ዙሪያ ከፌዴራል በተገኙ አወያዮች ምክክር አድርገዋል፡፡

‹‹የምንማረው ድህነትን በአንድነት ለማሸነፍ እንጂ ተፈጥሯዊ ስጦታዎቻችንን የልዩነት ምንጭ አድርጎ ለመራረቅ አይደለም፡፡›› የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተናገሩት...

‹‹በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን ኢትዮጵያዊነት ለአንድነታችን ማጠናከሪያ፤ ለቁርሾዎቻችን መታረቂያ ምክንያት እንዲሆኑ ጥያቄዎችን የመፍታት ባሕል ማድረግ አለብን፡፡›› አወያዮች ከተናገሩት የተወሰደ...

🔹ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ከአማራ ክልል መንግስት እና ከሌሎች አካላት የተወጣጣው የሰላም ኮሚቴ በባሕር ዳር ለ14 ቀናት የሚቆይ ከሰላም መስፈን ጋር የተያያዙ ተግባራትን እየተከታተለ እና እያገዘ መሆኑን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን እና ስታራቴጂክ ኮሚዩኒኬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ዶር. #ዘውዱ_እምሩ ገልጸዋል፡፡

የሰላም ኮሚቴው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደት እና አጠቃላይ በከተማው ያለውን የሰላም ሁኔታ ገምግሟል፡፡ በዚህም ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ተማሪዎችን በአግባቡ በመቀበል፣ መረጃ በመስጠት እና #የግጭት_ስጋቶችን በማስወገድ በጎ ስራ መስራቱን ተመላክቷል ነው ያሉት ዶር. ዘውዱ፡፡

‹‹ሰላም ቀላል የሚመስል ነገር ግን የሁላችንም እስትንፋስ ነው፡፡ ለሰላም የበኩላችንን እንወጣ››

‹‹ራሳቸውን አደራጅተው የአካባቢውን ጸጥታ የሚጠብቁ ወጣቶች የተማሪዎች ደህንነት የተጠበቀ እንዲሆን በጎ ስራ ሰርተዋል፡፡›› ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

.
.
©አማራ ብዙሀን መገናኛ ድርጅት
@tsegabwolde @tikvahethiopia