TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በምእራብ ወለጋ #የኦነግ ማሰልጠኛ ካምፕ ናቸው ተብለው በተጠረጠሩ ቦታዎች ላይ ዛሬ ጥዋት #የአየር_ጥቃት መፈፀም መጀመሩን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል።
.
.
የአዲስ ስታንዳርድ ዘገባ...

Ethiopia Defense Force begins #airstrike in western Oromia; says targets are OLF military training #camps. Ethiopian National Defense Force (ENDF) has began airstrikes in Qellem Wellega and its environs in western Oromia, a military source told Addis Standard. According to our source, the army’s targets are “military training camps run by OLA”, the armed group of the Oromo Liberation Front – Shane Group (OLF-SG). The airstrikes have began this morning; it is unclear how long the army will conduct the operation. It follow yesterday’s #bank_robbery of the state owned Commercial Bank of Ethiopia and the Cooperative Bank of Oromia.

©Addis Standard
@tsegabwolde @tikvahethiopi
የኦሮሚያ ክልል መንግስት‼️

በምእራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ዞኖች መንግስት #የአየር_ጥቃት ፈፅሟል በሚል የሚናፈሰው ወሬ #ከእውነት_የራቀ መሆኑን የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ።

የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሸን ጉዳዮች ቢሮ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፥ መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ላይ የሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ህዝቡን ለማደናገር ሙከራዎች እየተደረጉ ነው ብሏል።

የመንግስት ጦር በሰላማዊ ዜጎች ላይ እርምጃ እየወሰደ ነው የሚለው እና የአየር ጥቃት በመፈፀም ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው በሚል የተሰራጨው መረጃም ከእውነት የራቀ መሆኑን ቢሮው አስታውቋል።

በዚህ ዙሪያ ያለው ሀቅ መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር ስራውን በጥናት ላይ በመመስረት እና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ እያከናወነ መሆኑ ነው ብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአካባቢው ላይ ያለው የፀጥታ ችግር ይህን ያክል የአየር ጥቃት እስከመውሰድ የሚያደርስ አይደለም ሲልም ቢሮው አስታውቋል።

መንግስት አሁንም ቢሆን የህዝቡን ደህንነት ለማስጠበቅ ያለበትን ሀላፊነት እና ግዴታ ለመወጣት የጀመረውን ስራ ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የሚያስቀጥል በመሆኑ የአካባቢው ህዝብ ወንጀለኞችን አሳልፎ መስጠቱን እንዲቀጥል እና ለሰላም የሚያደርገውን ትብበር አጠናክሮ እንዲቀጥል የክልሉ መንግስት ጥሪውን አቅርቧል።

ምንጭ፦ FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አየር ሃይል‼️

‘በምዕራብ ኦሮሚያ በኦነግ ሸኔ ላይ በአየር ኃይል የታገዘ ጥቃት ተፈጽሟል’ ተብሎ በማህበራዊ ድረ-ገጾች የሚናፈሰው ወሬ #ሃሰተኛ መሆኑን የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል #ይልማ_መርደሳ ገለጹ።

ብርጋዴር ጄኔራሉ በምዕራብ ኦሮሚያ የጸጥታ ችግር መኖሩንና መንግስት ብዙ ትዕግስት ማሳየቱን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል።

መንግስት የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ እርምጃ መውሰድ የጀመረ ቢሆንም በማህበራዊ ድረ-ገጾች ‘በአየር ኃይል የታገዘ ጥቃት ተፈጽሟል’ ተብሎ የሚነዛው ወሬ ሃሰተኛ መሆኑን አስታውቀዋል።

በአካባቢው ከምድር ውጊያና የሰፈር ግጭት ያለፈና አውሮፕላን መጠቀም የሚያስገድድ ሁኔታ አለመኖሩንም ነው የገለጹት።

ምንጭ፦ ኢዜአ
.
.
.
ምንም እንኳን መንግስት የአየር ጥቃት አልተፈፀመም፤ የሚናፈሰው ወሬም ሀሰት ነው ቢልም ከቀናት በፊት ቢቢሲ ያነጋገራቸው #የኦነግ_ሸኔ የሥራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ #ሚካኤል_ቦረና መንግሥት በቤጊ እና ጊዳሚ ወረዳዎች ውስጥ #የአየር_ጥቃት እየሰነዘረ ነው ሕዝቡም #እየተጎዳ ነው ብለዋል። አቶ ሚካኤል እንደሚናገሩት፤ የኦነግ ጦር የነበረበትን ስፍራ ሳይለቅ እራስን #የመከላከል እርምጃ እየወሰደ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

በሊብያ ሙርዙቅ በደረሰው #የአየር_ጥቃት 42 ሰዎች ተገደሉ። የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንደገለፁት በደቡባዊ ምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው በጄነራል ከሃሊፋ ሃፍታር በሚመራ ሃይል በደረሰው የአየር ጥቃት የ42 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል።

መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ጥቃቱ የደረሰባቸው ሰዎች በሙርዙክ ከተማ የሰርግ ስነ-ስርዓት እየታደሙ ባሉበት ወቅት ነው። በምስራቃዊ ሊብያ ያለው የጄነራል ሃፍተር ሃይል እንደገለጸው እሁድ ማታ የደረሰው የአየር ጥቃት ሲቪል ሰዎችን አላማ ያደረገ አልነበረም፡፡

አገሪቷ እአአ ከ 2011 ከሙሃመድ ጋዳፊ ውድቀት በኋላ በጦርነት ላይ መሆኗም ተገልጿል። የአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት እንደሚያመለክተው ካለፈው ሚያዚያ ወር ወዲህ በሀገሪቱ በነበረው ግጭት የ1ሺህ ሰዎች ህይወት ጠፍቷል፡፡

ጥቃት የደረሰበት አካባቢ ከፍተኛ የነዳጅ ምርት ያላትና በፈረንጆቹ 2019 የመጀመሪያ ዓመት የተወሰነ አካባቢ በታጣቂ ቡድኑ ቁጥጥር ሥር የነበረ ቢሆንም በኋላ ግን ለቀው መውጣታቸውን የዘገበው ቢቢሲ ነው።

Via #bbc/ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ : ለወራት የቀጠለው የትጥቅ ግጭት ዐውድ እና አሉታዊ የሰብአዊ መብቶች እንድምታው " ተፋላሚ ኃይሎች ሲቪል ሰዎችንና ንብረቶችን፣ የሕዝብ አገልግሎቶችን እና መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ከማድረግ ሊቆጠቡ፣ መንግሥት የማኅበራዊ አገልግሎቶች እዲቀጥሉ አስቻይ ሁኔታ ሊፈጥር ይገባል። " በአማራ ክልል ጉዳይ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል። መግለጫው በክልሉ በተለያዩ…
#አማራ

በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ዛሬ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከተላከልን መግለጫ መረዳት ችለናል።

ከኢሰመኮ በደረሰን መግለጫ ፤ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል።

በተጨማሪም እነዚህ አካባቢዎችና ወረዳዎች በአንድ ወቅት ላይ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች በሌላ ወቅት ደግሞ በታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የትጥቅ ግጭቱ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ በከባድ መሣሪያ እና አልፎ አልፎ በአየር / ድሮን ድብደባ ጭምር የታገዘ ነው።

በግጭቱ ዐውድ ውስጥ #የአየር /#ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን ፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው ለመሸሽ ተገደዋል።

ለምሳሌ ፦

- በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በረኸት ወረዳ፣ ' መጥተህ ብላ ' ከተማ ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንድ ዓመት ከሰባት ወር ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች #ተገድለዋል፤ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

- በደብረ ማርቆስ ከተማ ጥቅምት 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት  ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

- በደንበጫ ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት ሲቪል ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ደርሷል።

ኮሚሽኑ እነዚህን መረጃዎች ያገኘው የአካባቢውን ነዋሪዎች እና የዓይን ምስክሮችን በማነጋገር ነው።

በአንዳንድ አካባቢዎች ጥቃትን አልያም ግጭትን በመሸሽ ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ ከቀያቸው ተፈናቅለው በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማረጋገጥ ተችሏል።

በምንጃር ወረዳ ውስጥ የአውራ ጎዳና ጎጥ ነዋሪዎች ከመስከረም 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ከቀያቸው ተፈናቀለው ቢያንስ 3ዐዐዐ የሚሆኑት አሞራ ቤቴ ቀበሌ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤትና ክፍት ሜዳ ላይ (በዛፍ ሥር) ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን፣ ሌሎች ቁጥራቸው ያልታወቀ መተሃራና አዋሽን ጨምሮ ወደ የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለዋል።

ለተፈናቃዮች የተወሰነ ድጋፍ በማኅበረሰቡና እና በአንድ ተራድዖ ድርጅት የተደረገ ቢሆንም፣ በቂ ባለመሆኑ በአሳሳቢ ሁኔታ እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል።

የነዋሪዎችን መፈናቀል ተከትሎ ሰብላቸው እንደወደመ፣ ንብረታቸው እንደተዘረፈ፣ የቤቶቻቸው ጣራያ እና በር እየተነቀለ እንደተወሰደ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ቤቶቻቸውን ከአጎራባች ክልል በመጡ ኃይሎች በኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ጭምር ማፍረስ እንደተጀመረ ኢሰመኮ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችና የመንግሥት ኃላፊዎች አስረድተዋል።

በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት የሚፈጸሙ ከሕግ ውጪ የሆኑ ግድያዎች አሁንም መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ተዓማኒ መረጃዎችን እየተቀበለ እንደሚገኝ ገልጿል።

ግጭቱ በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦

- " ፋኖን ትደግፋላችሁ "

- " ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ "

- " መሣሪያ አምጡ "


- " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ ግድያዎች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ተዓማኒ መረጃዎች ተገኝተዋል።

እንደማሳያ ፦

▪️በባሕር ዳር ሰባታሚት አካባቢ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2016 ዓ.ም. #ሦስት_ወንድማማቾችን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

▪️በሰሜን ጎጃም ዞን፣ አዴት ከተማ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ፍልሰታ ደብረ ማሪያም የሚኖሩ 12 የአብነት ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

▪️ በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ አማኑኤል ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች በቤት ለቤት ፍተሻ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።

▪️በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ፣ ግንደወይን ከተማ ሞጣ በር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ መስከረም 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አንድ በጥይት የቆሰለን ግለሰብ እናቱና እህቱ በባጃጅ አሳፍረው ወደ ሕክምና ተቋም በመውሰድ ላይ እያሉ፣ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ባጃጁን አስቁመው ሁሉንም ተሳፋሪዎች ካስወረዱ በኋላ " የቆሰለው እኛን ሲዋጋ ነው " በሚል ምክንያት የባጃጅ አሽከርካሪውን ጨምሮ አራቱን ሰዎች በጥይት እንደገደሏቸው ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች አስረድተዋል።

በባሕር ዳር፣ በፍኖተሰላም፣ በጎንደር እና በወልድያ ከተሞች በትጥቅ ግጭቱ ቆስለው ሕክምና ሲከታተሉ የነበሩ የተወሰኑ ሲቪል ሰዎች እና የታጣቂ ቡድኑ አባላት በመሆን በመንግሥት የጸጥታ አካላት የተጠረጠሩ ሰዎች ሕክምናቸው እዲቋረጥ ተደርጎ #ወዳልታወቀ_ስፍራ ከተወሰዱ በኋላ ፣ ከፊሎቹ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ወደ ሕክምና ተቋማቱ ሲመለሱ ቀሪዎቹ ያሉበት ሁኔታ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ማረጋገጥ አልተቻለም።
 
በሌላ በኩል በየደረጃው የሚገኙ ሲቪል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና እገታዎች በታጠቁ ኃይሎች ተፈጽመዋል።

ለምሳሌ ፦

መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ/ም የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከባሕር ዳር ወደ ደብረ ታቦር ሲሄዱ ' አለምበር ከተማ ' አካባቢ በታጣቂዎች ተገድለዋል።

በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጥቃት በመሰንዘር ታራሚዎችና ተጠርጣሪዎች እንዲያመልጡ ተደርጓል። 
 
ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል ፤ በተለይም ከመንግሥት ተቋማት ጭምር በሚደርሱት መረጃዎች መሠረት በግጭቱ ዐውድ የሚፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር ድርጊቶች በጣም አሳሳቢ እና በአፋጣኝ ተገቢው ምርመራ ተደረጎ አርምጃ ሊወሰድበት የሚገባው ነው፡፡

የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት በተለያዩ የጤና ተቋማት መድረስ የቻሉትን ተጎጂዎች ቁጥር ብቻ መሠረት በማድረግ ከሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ ቢያንስ #2ዐዐ_የአስገድዶ_መድፈር ተጎጂዎች በጤና ተቋማት ተመዝግበዋል፤ ከተጎጂዎች መካከልም የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ሴቶች እና የጤና ባለሞያ ሴቶች ጭምር ይገኙበታል።

ከትጥቅ ግጭቱ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ፦
🔹ሲቪል ሰዎች እና የሲቪል የንግድ እና የመሠረተ ልማት ተቋማት ላይ ዝርፊያ ተፈፅሟል።
🔹የማሳ ላይ ሰብል ውድመት ጨምሮ በሲቪል ሰዎች፣ በሕዝብ እና በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ደርሷል።
🔹ሕፃናት ከትምህርት ውጪ ሆነዋል በአንዳንድ አካባቢዎች የትምህርት ተቋማት ለወታደራዊ አገልግሎት ውለዋል። ይህ ደግሞ አፋጣኝ ትኩረት የሚሻ ነው።

በክልሉ ውስጥ በተለየ ሁኔታ ከተፈቀደላቸው ተቋማት በስተቀር ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ የኢንተርኔት አገልግሎት የተቋረጠ ሲሆን፣ በተለይም በግጭት ላይ ባሉ አካባቢዎች የስልክ አገልግሎትም ጨምሮ ተቋርጧል።

(ዛሬ ከ #ኢሰመኮ የተላከል ሙሉ መግለጫ በዚህ ታገኛላችሁ ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/82609?single)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ዛሬ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከተላከልን መግለጫ መረዳት ችለናል። ከኢሰመኮ በደረሰን መግለጫ ፤ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል። …
" ሪፖርቱ የመንግሥትን እንቅስቃሴ አውድ ከግምት ያላስገባ፣ በበቂ መረጃ ላይ ያልተመሠረተ እና ከእውነታ ያፈነገጠ ነው " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የአማራ ክልል የሰብዓዊ ሁኔታን በተመለከተ ያወጣውን መግለጫ " ከእውነታው ያፈነገጠና ሚዛናዊነት የጎደለው ነው " አለ።

ዛሬ መግለጫ የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አግልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ  ኢሰመኮ በአማራ ክልል ጉዳይ ያወጣው ሪፖርት የመንግሥትን እንቅስቃሴ አውድ ከግምት ያላስገባ፣ በበቂ መረጃ ላይ ያልተመሠረተ እና ከእውነታ ያፈነገጠ ነው ብለዋል።

በተጨማሪ ፤ መንግሥት ክልሉ ወደ ሰላማዊና መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለስ ያደረገውን ጥረት ከግምት ያላስገባ ነው ሲሉ ጠቁመዋል።

" መንግሥት ገለልተኛ ተቋማት እንዲኖሩ የሚፈልገው የተዛቡ መረጃዎች አንዲታረሙ እና ዴሞክራሲ እንዲጠናከር አስቦ ነው " ያሉት ሚኒስትሩ " ነገር ግን እነዚህ ገለልተኛ ተቋማት በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ ባሉ የተዛቡ መረጃዎች ከተጠለፉ የምንፈልገውን ዴሞክራሲ ልንገነባ አንችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ ፤ ኢሰመኮ የሚያወጣቸውን መረጃዎች ከትክክለኛ መንጭ በመረዳት እና ትክክለኛውን አውድ ከግምት ያስገባ መሆን እንሚገባው ገልጸዋል።

ከሰሞኑን ያወጣውን መግለጫም ቆም ብሎ እንዲገመግም አሳስበዋል።

መንግሥት በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት እና የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት ለማረጋገጥ ጥንቃቄ የተሞላባቸው እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ዶ/ር ለገሰ ቱሉ በዛሬው መግለጫቸው ወቅት ተናግረዋል።

ኢሰመኮ ከቀናት በፊት በላከልን መግለጫ ፤ በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ፣ እንዲሁም በመንግሥት ኃላፊዎች ላይ ግድያ መፈፀሙን አሳውቆ ነበር።

በተለይም #የአየር /#ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን ፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው መሸሻቸውን የኢሰመኮ መግለጫ ያስረዳል።

በተለይም በመጥተህ ብላ ከተማ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት የአንድ አመት ከ7 ወር ህፃንን ጨምሮ በርካቶች መገደላቸውን ፣ በደብረ ማርቆስ በተመሳሳይ በድሮን 8 ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን ፤ እንዲሁ በደንበጫ በከባድ መሳሪያ ሲቪሎች መገደላቸውን በመግለጫው አሳውቋል።

ኢሰመኮ በመግለጫው ላይ ቀጥሏል ባለው ከፍርድ ውጭ ግድያ ግጭት በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦ " ፋኖን ትደግፋላችሁ " ፤ " ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ " ፤ " መሣሪያ አምጡ "፤  " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ ግድያዎች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ተዓማኒ መረጃዎች መገኘታቸውን ገልጿል።

ከዚህ ባለፈ ፤ በየደረጃው የሚገኙ ሲቪል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና እገታዎች በታጠቁ ኃይሎች መፈፀማቸውን ኢሰመኮ በመግለጫ አሳውቆ ነበር።

ኢሰመኮ ልኮት የነበረው ሙሉ መግለጫ በዚህ ይገኛል፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/82610

@tikvahethiopia