TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በጋምቤላ ክልል #ከቅዳሜ ዕለት ጀምሮ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። የፀጥታ ሀይሎች እስካሁን ቢያንስ ስድስት ወጣቶችን ገድለዋል። በርካቶች ቆስለዋል። የሰልፉ ምክንያት በክልሉ አስተዳደራዊ ለውጥ እንዲደረግ የሚጠይቅ ነው። በጋምቤላ የኑዌርና አኙዋክ ጎሳ አባላት መካከል #የስልጣን መጋራት ውዝግብ ተደጋግሞ ይታያል። ከተማይቱ አሁንም በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ናት።

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ምን አሉ ? የተ/ም/ቤት አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፦ " ጠ/ሚ ዐቢይ ወደ መንበረ ስልጣን ከወጡበት ከመጋቢት 2010 ዓ/ም ጀምሮ እየተወሳሰቡ የሄዱት የሀገራችን ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች አሁን ላይ ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ መሸጋገራቸውን ማሸፋፈን ወደማይቻልበት ደረጃ ደርሰዋል። ብልፅግና መራሹ መንግስትዎ ፦ - የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የሚገባበት ፣ - ነጋዴው…
" አብኖች የት ነበራችሁ ? " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

የህ/ተ/ም/ቤት አባሉ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በሰሜኑ ክፍል ትግራይ ፣ አማራና አፋር ፋይዳ ባልነበረው ጦርነቱ መድቀቃቸውን ተናግረዋል።

ይህ ጦርነትም " #የብልፅግና እና #የህወሓት #የስልጣን ጦርነት " መሆኑን ገልጸው ነበር።

ይህ በተመለከተ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አጭር አስተያየት ሰጥተው አልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " እንደተባለው የTPLF እና የብልፅግና ችግር ከነበረ አብኖች (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ) የት ነበራችሁ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

እዚህ ላይ " ለምን አታስታርቁም ነበር የሚል ጥያቄም ይነሳል። " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " አስታራቂ ሲጠፋ ነው ግጭት የሚበዛው " ብለዋል።

" ድግሱን #ስናፋፋም ቆይተን አሁን ጉዳዩን ለተወሰነ ወገን መስጠት ተገቢ አይደለም " ያሉት ጠቅይላይ ሚኒስትሩ " ግጭቱን ማንም ይጀምረው ማንም ጥሩ አይደለም፤ ጥፋት ነው " ብሎ መቀበል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia