TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"የፌደራል ስርዓት ጉዳይ ለድርድር አይቀርብም" --- ኦዲፒ
.
.
በፌደራል ስርዓቱ ላይ ከማንም ጋር #ለድርድር እንደማይቀመጥ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዲፒ) አስታወቀ። ፓርቲው በትናነትናው እለት ባወጣው መግለጫው፥ ኦዲፒ በአጀንዳነት ይዞ ከሚታገልባቸው ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛው የፌደራል ስርዓቱ ነው ብሏል።

ለፌደራል ስርዓቱ መምጣት ከፍተኛ ዋጋ ተከፍሎበታል ያለው ፓርቲው፥ ስርዓቱ ለድርድር የማይቀርብ መሆኑንም አስታውቋል በመግለጫው። በፌደራል ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ #የሀሰት_ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑንም ኦዲፒ በመግለጫው አስታውቋል።

በአሁኑ ወቅትም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የፌደራል ስርዓቱን ሊያፈርስ እንደሆነ እንዲሁም ህብረተሰቡ በፌደራል ስርዓት ላይ ያለውን እምነት እና ተስፋ እንዲቀንስ ከፍተኛ የሆነ የሀሰት ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑንም ገልጿል።

የሀሰት ዘመቻው ሁለት ዓላማ ያለው ነው ያለው ኦዲፒ፥ ከእነዚህም አንደኛው የኢትዮጵያ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሁን ያለውን ለውጥ በጥርጣሬ እንደሚመለከቱ ማድረግ ነው ብሏል።

በዚህም የራሳቸውን ባህል፣ ቋንቋ፣ ማንነት እና ታሪክ ማሳደግን በትግል እና በመስዋእትነት ያገኙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች የፌደራል ስርዓቱ ሊፈርስ ነው በሚል በጥርጣሬ ተቃውሞ እንዲያስነሱ ታስቦ የሚደረግ ሴራ መሆኑንም ገልጿል።

በተጨማሪም የኦሮሞን ህዝብ “ተጨማሪ መብት ማግኘትህ ቀርቶ ከዚህ ቀደም የተገኘውን መብት ልታጣ ነው” በሚል በማደናበር እርስ በርስ ለማጋጨት ያለመ መሆኑንም አስታውቋል።

የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዲፒ) የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄን ለመመለስ እንደሚሰራ በመግለጽ፥ የአዲስ አበባ እና የአፋን ኦሮሞ ጉዳይም እየተሰራበት ያለ መሆኑን ገልጿል።

ከፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጥያቄዎች ላይም ትኩረት በመስጠት እየሰራበት መሆኑን ፓርቲው በመግለጫው አስታውቋል።

ኦዲፒ ለተጨማሪ ድል ይሰራል እንጂ ከዚህ ቀደም የተገኙ ድሎችን አያከሽፍም ያለው ፓርቲው፥ በፌደራል ስርዓት ጉዳይ ላይ ከማንም ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥም ገልጿል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በየጊዜው ግድቡ ቆማል በሚል በግብፅና በተለያዩ አፍራሽ ኃይሎች የሚሰራጨውን #የሀሰት ፕሮፓጋንዳ በመያዝ አሉታዊ መልዕክት የሚያስተላልፉ አካላትን ውሸትና ሴራ የምናጋልጠው ግንባታውን በተግባር በማፋጠን ብቻ ነው።" ዶ/ር አብርሃም በላይ/የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ/

@tsegabwolde @tikvahethiopia