TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"ከየትኛዉም ጊዜ በላይ #ወንድማዊ ትስስራችሁን አጥብቃችሁ ተረጋግታችሁ የትምህርታችሁን ጊዜ በአግባቡ እንድትጠቀሙ ቤተሰባዊ ምክራችንን እንለግሳለን!" - ጅማ ዩኒቨርሲቲ

መላዉ የጅማ የኒቨርሲቲ ማህበረሰብና ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተከሰተዉ ግጭት ህይወታቸዉን ላጡና የአካል እና መንፈስ ጉዳት ለደረሰበቸዉ ተማሪዎች የተሰማዉን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ በእነዚህ በምንሳሳላቸዉ ልጆቻችን ላይ የደረሰዉ ጉዳት በዬትኛዉም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለዉና ሰብአዊነትን ያልተላበሰ በመሆኑ በከፍተኛ ደረጃ እናወግዛለን፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የሚመለከታቸዉ የመንግስት አካላት ሁሉ የችግሩን አሳሳቢነት በመገንዘብ በሙሉ ሃይላቸዉ ተንቀሳቅሰዉ በዚህ አስነዋሪ ድርጊት ዉስጥ የተሳተፉ አካላት ላይ በአፋጣኝ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡

የዩኒቨርሲቲያችን ተማሪዎችም ከዬትኛዉም ጊዜ በላይ ወንድማዊ ትስስራችሁን አጥብቃችሁ ተረጋግታችሁ የትምህርታችሁን ጊዜ በአግባቡ እንድትጠቀሙ ቤተሰባዊ ምክራችንን እየለገስን የዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብና የበላይ አስተዳደር አካላት ከመቼዉም ጊዜ በበለጠ ከጎናችሁ መሆናችንና እያነሳችሁ የምትገኙትን ጥያቄ ለሚመለከታቸዉ የመንግስት አካላት በማቅረብ ተገቢዉን ምላሽ እንድታገኙ የበኩላችንን ጥረት ሁሉ እንደምናደርግ ልንገልጽላችሁ እንወዳለን፡፡

ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን!

#JimmaUniversity

@tsegabwolde @tikvahethiopia