TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በስልጤ ዞን ዛሬ ቢያንስ 2 ሰዎች የገደሉ‼️

በደቡብ ክልል ስልጤ ዞን ገርቤ በር ወረዳ ባሎቀሪሶ በተባለ ቦታ በዛሬው ዕለት በአካባቢው ነዋሪዎች እና በጸጥታ አስከባሪዎች መካከል በተቀሰቀሰ #ግጭት ቢያንስ ሁለት ሰዎች መገደላቸውን የዐይን ዕማኞች ተናገሩ። በግጭቱ የቆሰሉ ወደ ወራቤ ሆስፒታል ተወስደዋል። የጀርመን ራድዮ ያነጋገራቸው ሶስት የዐይን እማኞች እንደተናገሩት ሁለት ሰዎች የተገደሉት የጸጥታ አስከባሪዎች በተኮሱት ጥይት ነው። ግጭቱ ዛሬ ጠዋት አራት ሰዓት ገደማ መቀስቀሱን የተናገሩ የዐይን እማኝ "የሞተ ሁለት ነው። ግን በርካታ ቆስሏል። የቆሰለውን ይኸን ያህል አልለውም። በርካታ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

አንድ ሌላ የዐይን ዕማኝ የሟቾቹ ቁጥር ሁለት መሆኑን #አረጋግጠው የግጭቱ መነሾ ለኢንቨስትመንት የታጠረ ቦታ ሊሰጠን ይገባል የሚል ጥያቄ በወጣቶች በመቅረቡ እንደሆነ አስረድተዋል። የዐይን እማኙ የአካባቢው ወጣቶች ታጥሮ የተቀመጠን ቦታ ለማፅዳት ሲሞክሩ "ግብግብ ተፈጥሮ አንድ ሁለት ሰው ሞቷል" ብለዋል። "ከዚህ በፊት ለኢንቨስትመንት የተሰጠ መሬት ነበር። የተሰጠው ባለሐብት ሶስት አመት ሙሉ አጥሮት ነው ቁጭ ያለው። ምንም የሰራው ነገር የለም" የሚሉት የዐይን እማኝ የአካባቢው ወጣቶች በተደጋጋሚ ቦታው ሊሰጠን ይገባል የሚል ጥያቄ ከወረዳ እስከ ክልል አቅርበው ነበር ብለዋል።

"ጠዋት ሁለት ሰዎች ሞተዋል። ቤቶችም ተቃጥለዋል" ያሉ ሶስተኛ የዐይን እማኝ በበኩላቸው በግጭቱ የቆሰሉ ሰዎች ወደ #ወራቤ_ሆስፒታል መወሰዳቸውን ተናግረዋል። ከቆሰሉ መካከል የጸጥታ አስከባሪዎች ይገኙበታል ተብሏል። የዐይን ዕማኞቹ የጸጥታ ኃይሎች ወደ ከተማዋ ከገቡ በኋላ የመረጋጋት አዝማሚያ ይታያል ብለዋል።ወጣቱ ተጭኖ ተጭኖ እየሔደ ነው። ግጭት የተቀሰቀሰባት የገርቤ በር ወረዳ በስልጤ ዞን ከወራቤ ከተማ በ13 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ ትገኛለች።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Congratulations !

የተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዛሬ ተማሪዎቻቸውን አስመርቀዋል።

#ወላይታ_ሶዶ_ዩኒቨርሲቲ

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 5 ሺህ 726 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ለ13ኛ ጊዜ ባካሄደው የተማሪዎች ምረቃ ሥነ ስርዐት 5 ሺህ 726 ተማሪዎችን በመጀመሪያ፣ 2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ 448ቱ በ2ኛ ዲግሪ እንዲሁም ሰባቱ በ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆኑ ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 2 ሺህ 31ዱ ሴቶች ናቸው።

#ወራቤ_ዩኒቨርሲቲ

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 132 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው፡፡

#ኦዳቡልቱም_ዩኒቨርሲቲ

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 354 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ዛሬ ዩኒቨርሲቲው ባካሄደው 3ኛ ዙር የምረቃ ስነስርዐት የተመረቁ ተማሪዎች፤ በመደበኛ፣ በኤክስቴንሽን እና በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብሮች ስልጠናቸውን የተከታተሉ ናቸው።

#ሰላሌ_ዩኒቨርሲቲ

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 54 ተማሪዎች አስመርቋል።

3ኛ ዙር ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲው አራት ኮሌጆች በመጀመሪያ ዲግሪ በመደበኛና ኤክስቴንሽን መርሃ ግብሮች ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ናቸው። ዛሬ ከተመረቁት ተማሪዎች 428ቱ ሴቶች ናቸው።

በሌላ በኩል ፦

የተለያዩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች አስመርቀዋል።

ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፣ ኩዊንስ ኮሌጅ፣ ግሬት ኮሌጅና ኤልኤም ኢንተርናሽናል የሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ተቋማት ያስተማሯቸውን ተማሪዎች አስመርቀዋል።

Source : @tikvahuniversity
#ትኩረት

#ከዳሎቻ ወደ #ወራቤ ያለው መንገድ በአፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠው ነዋሪዎች ጠይቀዋል።

ከላይ በምስሉ ላይ የምትታየው እናት ምጥ ይዟት ከዳሎቻ ወደ ወራቤ ሆስፒታል ብትላክም በመንገዱ ብልሽት ምክንያት አንቡላንሷ በጭቃ ተይዛ እናትም በጭቃ መሃል እንድትወልድ ተገዳለች።

ከዚህ ባለፈ ከዳሎቻ ወደ ወራቤ ሆስፒታል ሪፈር የተፃፈላት ህፃን በመንገዱ ብልሽት ምክንያት አንቡላንሱ መሃል መንገድ ደርሶ ማለፍ ባለመቻሉ የህፃኗ ህይወት ልያልፍ ችሏል።

መንገዱ ከዳሎቻ ከተማ ጫፍ እስከ ወራቤ ከተማ ጫፍ ቡታጅራ መውጫ የተዘረጋና ርቀቱም ከአስር ኪሎ ሜትር ያነሰ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በከፍተኛ ሁናቴ ተበላሽቶ ይገኛል። 

በተጨማሪም መንገዱ እጅግ በጣም ጠባብ ፣ በየቦታው የተቆፋፈረ፣ በክረምት ወራት ከባድ ጭቃ፣ በበጋ ጊዜያት አስቸጋሪ አቧራ ያሚበዛበት ሲሆን በተደጋጋሚ የሚጠቀሙት መንገደኞች ላይ ከፍተኛ የጤና መታወክም ሲያደርስ ቆይቷል።

ይህም መንገድ በክልል ገጠር መንገድ በኩል በጠጠር መንገድ ደረጃ ተሰርቶ እያገለገለ ቆይቶ  በየ ጊዜው የተወሰነ ጥገና እየተደረገለት እስካሁን ቢደርስም አሁን ላይ የጉዳቱ መጠን እጅግ ከፍ ያለ ደረጃ መድረሱ ከክረምቱ ወቅት ዝናብ ጋር ተዳምሮ የመስመሩን ጉዞ እጅግ ፈታኝ አድርጎታል።

ስለሆነም የሚመለከተው አካል የመንገዱን አሁናዊ ሁኔታ ተመልክቶ አፈጠኝ ምለሽ ሊሰጠን  ይገባል ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ጠይቀዋል።

(ሰይፈዲን ሉንጫ ከወራቤ)

@tikvahethiopia