TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳዛኝ ዜና‼️

በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን #ያአበሎ_ወረዳ በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ ከ15 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለፀ።

የተሽከርካሪ አደጋው ያጋጠመው ከኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያአበሎ ከተማ ወደ ደቡብ ክልል #ኮንሶ ከተማ #ኮንትሮባንድ_ጭኖ በፍጥነት ሲጓዝ የነበረ ተሽርካሪ ከተቃራኒ አቅጣጫ ከሚመጣ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።

በያአበሎ ወረዳ ኛሮ ቀበሌ ኤላ ዲማ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰው የትራፊክ አደጋም ከ15 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን ከቦረና ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክተታል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኮንትሮባንድ

የመንግሥት ሆኑ ሌሎች በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ተቋማት ለኮንትሮባንድ ንግድ መቆም መፍትሔ ከመሆን ይልቅ፣ ሕገወጥ ንግድን የሚያባብሱ ሆነው አግኝተናቸዋል ሲሉ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኃላፊዎች ገለጹ፡፡

በየአካባቢው ያሉ ተቋማት በኮንትሮባንድ ዙሪያ የሚያከናውኑትን በሚመለከት ሲያስረዱ፣ ድርጊቱን በመቃወም አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የመንግሥትና ሌሎች አካላት እንዳሉ ሁሉ፣ " ከችግሩ ጋር አብረው የሚኖሩና የሚተገብሩም " እንዳሉ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ ተናግረዋል፡፡

የተቋማቱን ስምና አድራሻ ሳይገልጹ እነዚህ ተቋማት ምንም እንኳን ዕርምጃ እየተወሰደባቸው ቢሆንም፣ የኮንትሮባንዲስቶቹ አካልና ተባባሪ ሆነው እየሠሩ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡

" ሁኔታ የሚያመቻቹ፣ የሚያሳልፉ፣ መረጃ የሚሰጡ፣ ሕገወጦችን የሚከላከሉላቸው፣ የሚደብቁ፣ እንዳይያዙና እንዳይመረመሩ የሚያደርጉ፣ ዕቃዎቻቸውን በሽፋን የሚያሳልፉ፣ ሐሰተኛ ሰነድ በመሥራት የሚተባበሩ… " ሲሉ አቶ ደበሌ በሕገወጥ ንግድ ላይ " ቀላል ቁጥር የሌላቸው " ተቋማት እንዴት እንደሚሳተፉ አብራርተዋል፡፡

ስለኮንትሮባንድና ሕገወጥ ንግድ ሲነገር እነዚህ ችግሮች በበርካታ ተቋማት እንደሚፈጸሙ፣ ወደታችኛው የአስተዳደር አካል ሲወረድ ደግሞ ችግሮቹ " በጣም በከፍተኛ ደረጃ እየሰፉ ነው " ሲሉ ኮሚሽነሩ ይገልጻሉ፡፡

ችግሩን በመቃወም አስተዋጽኦ እያበረከቱ ካሉ ተቋማት መካከል፣ ከጉምሩክ ኮሚሽንና ከገቢዎች ሚኒስቴር በተጨማሪ የፌዴራል ፖሊስ፣ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ ዓቃቢያነ ሕጎች፣ የክልል የፀጥታ አካላትና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንደሚገኝበት አስረድተዋል፡፡

ኮንትሮባንዲስቶች ሊጠቀሙባቸው የሚችሏቸው በርካታ መንገዶች እንዳሉ ሁሉ፣ ከሁለት ሺሕ ኪሎ ሜትር በላይ የሚረዝመውን ከምሥራቅ ኢትዮጵያ ክፍል እስከ ኬንያ ድንበር ድረስ ያለውን ሥፍራም ለዝውውር እንደሚጠቀሙበት ተገልጿል፡፡

በችግሮቹ ግዝፈትና አስከፊነት ልክ አቅም ያላቸው ተቋማትን መገንባት አንደኛው ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ፣ እንደ ሕግ አስከባሪ ዓይነት ተቋማትንም በሚገባ ማደራጀት እንደሚያስፈልግ ኮሚሽነሩ አውስተዋል፡፡

አቅምን ከመገንባት ባለፈም የሚወሰደው ዕርምጃ ትልቅ ሊሆን እንደሚገባና ከዚህ በፊት የተወዱት ዕርምጃዎችም ጥሩ እንደሆኑ ሲገልጹ፣ በተጠናቀቀው ዓመት ብቻ እስከ 80 ቢሊዮን ብር የተገመቱ የተለያዩ የኮንትሮባንድ ቁሳቁሶች እንደተያዙ ገልጸዋል፡፡

" ይህ ቁጥር የሕገወጥነትን ጉልበት በልኩ የሚናገር፣ የተወሰደውን ዕርምጃ በልኩ የሚናገር፣ ቀጣይ ምን መሥራት እንደሚገባንም የሚናገር ነው " ሲሉ አቶ ደበሌ ቃበታ ከሰሞኑን መናገራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። #ሪፖርተር

@tikvahethiopia