TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኮሎኔል_ገመቹ_አያና

➡️ " ኮሎኔል ገመቹ አያናን ከኦሮሚያ ፖሊስ በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ በስማቸው የለንም ፤... ኮለኔል ገመቹን ይዘን ወደ ኦሮሚያ ፖሊስ በመሔድ ተረከቡን ብለን ስንጠይቅ ኦሮሚያ ፖሊስ እኛ ጋር ጉዳይ የለውም የሚል ምላሽ ሰጥቶናል " - ኮማንደር ኤርትሮ ኦቦ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን

➡️ " ኮ/ል ገመቹ መታሰራቸውን አንፈልግም ቢለቀቁ አልቃወምም " - አቃቤ ህግ

➡️ " ፍርድ ቤት ነጻ እንዳለኝ ሁሉ በነጻ እንድፈታ እፈልጋለሁ "  - ኮሎኔል ገመቹ አያና

ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮ/ል ገመቹ አያናን ከኦሮሚያ ፖሊስ በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ በስማቸው እንደሌለው ገልጿል።

የኦነግ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ኮሎኔል ገመቹ አያና ባለፈው ዓመት ግንቦት 9/ 2013 ዓ/ም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና ህገመንግስታዊ ወንጀል ችሎት ከተከሰሱበት የሽብር ወንጀል በነጻ መሰናበታቸው ይታወሳል።

ሆኖም በነጻ ከተሰናበቱ በኋላ በነጋታው ግንቦት 10 ቀን 2013 ዓ/ም ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሲወጡ በር ላይ በኦሮሚያ ፖሊስ ተይዘው መወሰዳቸውን እና 6 ወር በገላን ፖሊስ ጣቢያ እና ወታደራዊ ካንፕ እንዲሁም በአዋሽ መልካሳ በአንድ ጄነራል ዶሮ እርባታ ውስጥ ታስረው እንደነበር እና ከህዳር 16 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ለፌደራል ፖሊስ ተላልፈው እንደተሰጡና እንደታሰሩ ተገልጾ ነበር።

ያንብቡ ; https://telegra.ph/Tarik-Adugna-05-19

Credit : ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia