TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ኦነግ ላይ #ተሰነዘረ ስለተባለው የአየር ጥቃት! #ጋዜጠኛ_ኤልያስ_መሰረት(AP) ሰሞኑን አንዳንድ የሀገር ውስጥ ሚድያዎች በኦነግ ማሰልጠኛ ካምፖች ላይ የአየር ጥቃት መድረሱን ሲዘግቡ ሰንብተዋል። አንድ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣን ትናንት ምሽት anonymously የነገሩኝ ግን ፈፅሞ የተለየ ነበር፦ "ያው እንደምታውቀው መከላከያ የራሱ ስርአት ስላለው እና እኔም ወታደር ስላልሆንኩ ዝም ብዬ በነሱ…
"የአየር ጥቃት ተፈፅሟል" ኦነግ‼️

ዕሁድ ጠዋት የሀገር መከላከያ በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙ የኦነግ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች ላይ የአየር ጥቃት ሰንዝሯል የሚል መረጃ በስፋት ተሰራጭቶ ነበር።

የምዕራብ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ #ገመቺስ_ተመስገን በጉዳዩ ላይ BBC የአማርኛው አገልግሎት አስተያየታቸውን ጠይቆ፤ ''ይህ መረጃ እስካሁን አልደረሰኝም። በምዕራብ ኦሮሚያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ይንቀሳቀሳል። በተለያዩ አጋጣሚዎችም ከኦነግ ሠራዊት ጋር የተኩስ ልውውጥ አድርጓል። ዕሁድ ዕለት የአየር ጥቃት ተሰንዝሯል ወይም #አልተሰነዘረም ማለት #አልችልም'' ብለዋል።

በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ የአየር ጥቃት የተፈጸመው በቤጊ እና ጊዳሚ ወረዳዎች አዋሳኝ ድንበር ላይ መሆኑ በስፋት ተነግሯል። ይሁን እንጂ BBC ያነጋገራቸው የአከባቢው ነዋሪዎች "የአየር ጥቃት ተፈጽሟል ሲባል ሰማን እንጂ ያየነው ነገር የለም" ይላሉ።

ነዋሪዎቹ እንደሚሉት፤ የአየር ጥቃት ሲፈጸም #ባይመለከቱም በአከባቢው የጦር ሄሊኮፕተሮች በብዛት ስለሚመላለሱ ከፍተኛ ስጋት ገብቷቸዋል።

#የኦነግ_ሸኔ የሥራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ #ሚካኤል_ቦረና ግን መንግሥት በቤጊ እና ጊዳሚ ወረዳዎች ውስጥ የአየር ጥቃት #እየሰነዘረ ነው ሕዝቡም እየተጎዳ ነው ብለዋል። አቶ ሚካኤል እንደሚናገሩት፤ የኦነግ ጦር የነበረበትን ስፍራ ሳይለቅ እራስን #የመከላከል እርምጃ እየወሰደ ነው።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia